የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
رفتن به کانال در Telegram
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
514
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
ይህን ያውቁ ኖሯል።
ሁለቱን አህጉራት ያገናኘ ደብዳቤ
የሸዋው ንጉስ ሣህለ ስላሴ ለእንግሊዟ ንግስት የፃፉት ደብዳቤ በቀደምት የስልጣኔ ሀገር በኢትዮጵያና በኃያላኗ የአውሮፓ ሀገር በእንግሊዝ መካከል ስለነበረው ቀደምት መስተጋብር ለመመስከር ብርቅዬ ድርሻን ይወስዳል፡፡ በጥር ወር 1735 ዓ.ም በአንኮበር ሰማይ ስር ደብተራ ወልደ ዜና ማርቆስ የተባሉ ሰው የንጉሱን ሀሳብ በደብዳቤ ሰንደዋቸዋል።
“አቺ፡አቺ፡ደህና፡ነሾይ፡እኔም፡ደህና፡ነኝ….” ደብዳቤው ይጀምራል፡፡ ንጉሱ በእርሱ ግዛት ስር ክፉውንም ደጉንም እያዩ የቆዩት የእንግሊዝ ዜጎች ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እንደፈለጉ ባወቀ ጊዜ ባዶ እጃቸውን ሊሸኛቸው አልወደደም፡፡ በአባታዊ ልብ የሀገሩን ውድ የባህል ጌጣጌጦች ከጓዛቸው ጋር ይዘው እንዲሄዱ በስጦታ አበርክቷል፡፡ እነዚህን ስጦታዎች “በኛ፡ባገራችን፡ጌጣችንም፡ይኸ፡ነው፡የኛ፡ባገራችን፡የምንችለው፡ነገር፡ይኸ፡ነው“ በማለት የሚያኮራ የባህል ማንነት መገለጫውን ባሕር ማዶ አሻግሯል፡፡
የደብዳቤው ይዘት ለዘመናዊው የሀገራት ግንኙነት መሰረት የሚጥል ነው፡፡ ንጉሱ በዙፋናቸው መካከል ያለውን ሰፊ ርቀት በመገንዘብ “እስበርሳችን፡ባንተያይ፡እኔም፡ደብዳቤ፡መላኬ፡አንችም፡ደብዳቤ፡መላክሺ፡ስለመተያየት፡ነው“ በማለት ደብዳቤዎቻቸውን አይነተኛ የግንኙነት መንገድ አድርገው ያስቀምጧቸዋል፡፡
ለሁለት ሀገራት ግንኙነት መጠናከር አንድ የሚያደርጉ የጋራ ጉዳዮች ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳላቸው “ለእግዚአብሔር፡እኔም፡አንችም፡ለርሱም፡የምንሰግድለት፡ለኢየሱስ፡ክርስቶስ፡እርሱ፡ላንቺ፡ይጠብቅሽ፡ አሜን፡አሜን“ ብለው የጋራ እምነታቸውን ካንጸባረቁበት ሃሳብም መረዳት እንችላለን፡፡
በዚህ ሁሉ ግን ደብዳቤው አለማችን አሁን ድረስ የሚያስፈልጋትን ድምጽ ደመቅ አድርጎ ያስተጋባል፡፡ ፍቅርና ወዳጅነት!
የአለም አቀፍ ግንኙነቶችን ለመረዳት፣ የአፍሪካን ቀንድ የፖለቲካ ምህዳር ለማጥናት፣ ስለ አንግሎ-ኢትዮጵያ ግንኙነት የታሪክ አውድ ለመቃኘት ፣ ለዲፕሎማሲም ሆነ ለነገስታት ግንኙነት ለማወቅ ዝንባሌ ላለው ሁሉ ይህ ደብዳቤ የሚያወራው ይኖረዋል፡፡
የሸዋው ንጉስ ሣህለ ስላሴ ለእንግሊዟ ንግስት የጻፉት ደብዳቤ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ድርጅት (UNESCO) ኢትዮጵያ ካስመዘገበቻቸው 12 የጽሑፍ ቅርሶች መካከል አንዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ማይክሮፊልም ቤተመጻሕፍት ክፍል ተጠብቆ ይገኛል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢፌዲሪ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ክብረት ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ "በእውነቱ በዛሬው ዕለት በዚህ ከልጅነቴ ጀምሮ በማውቀው ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መጥቼ ይህንን ተአምራዊ ስራ ለማየት በመቻሌ በጣም ነው ደስ ያለኝ!" በማለት ገለጹ።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የህዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን
ታህሳስ 30/2018 ዓ.ም
የኢፌዲሪ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና የኢፌዴሪ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ክቡር ሙላቱ ተሾመ ባለቤት ክብርት መአዛ አብርሃም ታህሳስ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።
በጉብኝታቸውም ተቋሙ የሚሰጠው አገልግሎትን በሚመለከት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰርፀ ፍሬስብሐት እና የየክፍሉ ስራ አስፈጻሚዎች ገለጻ አድርገውላቸዋል።
ከጉብኝቱም በኋላ ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ "ድሮ እማርበት ከነበረው ሊሴ ገ/ማርያም ት/ቤት ወደ ለገሀር ስንሄድ ማለፊያው ነውና ጎራ እንላለን።
በጥልቀት ስለ ተግባሩ ባላውቅም ራስን ለማሳደግና ለማነጽ የሚያግዝ እና ወጣቶች እንዲመጡበት የሚጋብዝ ነበር። በዚህ ደረጃ አድጎ በማየቴ ደስ ብሎኛል" በማለት ተቋሙን በሚመለከት ያላቸውን ትዝታ አካፍለዋል።
ክብርት ሳህለወርቅ፤ "ሀገራችን ታሪኳ ብዙ ውጣውረድ ያለው ነው። እዚህ ባለው ስብስብ ለኢትዮጵያ ያለ ሀሳብ፣ ምክር፣ለኢትዮጵያ ያለ ቁጭት ተቀምጧል። ጃንሆይም ይህንን ተቋም ሲመሰርቱ ታሪኳን አቆይታ ለትውልድ የማታስተላልፈው ለምንድነው? በሚል መነሻ ነው። ስለዚህም ይህንን ሰው ማየት አለበት።" በሚል የተቋሙን ሀገራዊ ፋይዳ ተናግረዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የኢፌዲሪ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ክብረት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና የኢፌዴሪ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ክቡር ሙላቱ ተሾመ ባለቤት ክብርት መአዛ አብርሃም ተቋሙ ለትውልድ እና ለሀገር የታሪክ ባለቤትነትን እና የጥናት እና ምርምር ማዕከልነትን ለማስቀጠል ዜጎች የመረጃ ሀብቶች የሆኑትን የጽሑፍ ሰነዶች፣መዛግብትና የታተሙ እና ያልታተሙ ስራዎችን እንዲሁም ቀረጸ ምስልና ድምጽ ለኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) እንዲያበረክቱ፤ በዚህም የዜግነት ግዴታቸውን በመወጣት ታሪክን እንዲያስቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን፣ ለመድኅኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደርሳችሁ ይላል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተካሔደ፡፡
ታህሣሥ 28/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
========
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በ2018 በመጀመሪያው የበጀት ዓመት ያካናወናቸውን ተግባራት ከተቋሙ ፈጻሚዎችና አስፈጻሚ ጋር ዛሬ ታህሣሥ 28/2018 ዓ.ም በጥልቀት ገምግሟል፡፡
የተቋሙን የ2018 የመጀመሪያውን የግማሽ ዓመት ዕቅድ ክንውን የተቋሙ የስታራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ (ተወካይ) አቶ አህመድ እስማኤል እና በምስል የተደገፈውን ክንውን ደግሞ በተቋሙ ሥራ አመራር በአቶ አብነት አበራ ለውይይት ቀርቧል፡፡
ለውይይት በቀረበው የ2018 የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ዕቅድ ክንውን ከሰራተኛው ሃሳብ፣ አስተያየትና ጥያቄዎች ተነስተው ከተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ከአቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት እና ከሚመለከታቸው የስራ ክፍል ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸው የእቅድ ክንውን ገምገማው ተጠናቋል፡፡
ለመላው የተቋሙ አመራሮችና ስራተኞች በክብር ተጋብዛችኅል።
መግቢያ በነጻ
