es
Feedback
Eotc Task Force

Eotc Task Force

Ir al canal en Telegram

ወቅታዊ ጉዳይ

Mostrar más
7 367
Suscriptores
+224 horas
+2157 días
+33930 días
Archivo de publicaciones
ይኽች ሀገር የተለያዩ እምነቶች የሚኖሩባት ሀገር ናት ዋጋ ከፍላ ያቆየቻት ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ናት።እውነታው ይኽነው ቢመርህም ዋጠው።ሌላው እኮ አንዴ ከቱርክ አንዴ ከግብፅ አንዴ ከደርቡሽ አንዴ ከጣሊያን ጋር አንዴ ከዝያድ ባሬ ጋር ተሰልፎ ሲዋጋ የነበረ ነው

የቤተ ክህነቱ ሚዲያ ሠራዊት(ፋርሴ ቡላዎች)
+1
የቤተ ክህነቱ ሚዲያ ሠራዊት(ፋርሴ ቡላዎች)

የዚህ ሚዲያ ነገር በጣም የሚገርም እኮ ነው።ኦርቶዶክሱ በየቀኑ እንደ ቅጠል በሚረግፍበት ሀገር ላይ የጳጳስ እናት መታሰቢያ እያለ ያላዝናል።ደግሞ comment መስጫውን ቆልፈውታል።
+1
የዚህ ሚዲያ ነገር በጣም የሚገርም እኮ ነው።ኦርቶዶክሱ በየቀኑ እንደ ቅጠል በሚረግፍበት ሀገር ላይ የጳጳስ እናት መታሰቢያ እያለ ያላዝናል።ደግሞ comment መስጫውን ቆልፈውታል።

ያለሽ መስሎሻል ተበልተሽ አልቀሻል

እውነት እውነቷን እንነጋገር እኛ ያቃለልነውን ሞታችንን ማን እንዲናገርልን ነው የምንፈልገው? የሚያስገድለን የመንግሥት መዋቅር መሆኑን እያወቅን፣የሚታደገን ስለሞታችን የሚገደው ሲኖዶስ እንደሌለን እያወቅን ፣ከእግዚአብሔርና ከኦርቶዶክሳዊ ኅብረታችን በቀር ሊታደገን የሚችል ኀይል እንደሌለ እያወቅን አሁንም በጥልቅ ድንዛዜ ውስጥ ነን።አንድ በጣም የሚያበሳጨኝ ነገር ልንገራችሁ እኛ ዋጋ ከፍለን የምናቀርባቸውን መረጃዎችን እንኳ ተቀባብሎ በየሚዲያ የማጋራት ልምዱ እንኳ የለንም።ከ2 ቀን በፊት በአርሲ ምድር በስድስት ወራት ውስጥ የተፈጸሙ ጥቃቶችን ሪፖርት ናሙና(sample) አቅርበናል ነገር ግን ከ4 አራት ሰው በቀር fb ላይ የለጠፈ አይላየሁም።እንደዚህ ዓይነት መረጃዎችን ካላጋራን ምን ላናጋራ ነው? ሀገር መራለሁ የሚል ጠቅላይ ሚንስትር ሳይቀር ኦርቶዶክስ አልሞተም እያለ ሲዘባበት እኛ የሚቀርቡ መረጃዎችናን ማስረጃዎችን ለማጋራት ለምን ሰነፍን? በጥቂቱ ካልታመንን እንዴት ነው ዋጋ ከፍለን ቤተ ክርስቲያንን ከፍለን ማሻገር የምንችለው? የሆነ አስተዋጽዖ ካላበረከትን በቻናሉ ውስጥ በመኖራችን ምንድን ነው ጥቅሙ? እኛ እኮ የወሬ ሱስ ኖሮብን አይደለም ወገን ቢያንስ በጥቂቱም ቢሆን የድርሻችንን እንወጣ ብለን እንጂ።እውነቴን ነው የምላችሁ እዚህ ቻናል ውስጥ ወይ መረጃ በማምጣት ሊሆን ይችላል፣ወይ እዚህ ላይ የሚለጠፉ ጽሑፎችን ሊሆን ይችላል፣ወይ ጠቃሚ ኮሜንቶችን መስጠት ሊሆን ይችላል የራሱን ድርሻ የማይወጣ ሰው ሊኖር አይገባውም ምክንያቱም እኛ የሰው ብዛት ሱስ የለብንምና ።ከማይሠራ 7ሺ ሰው የሚሠራ አንድ ሰው ይበልጣልና።እስኪ ሳንዋሽ ራሳችንን እንጠይቅ እዚህ የሚለቀቁ ጽሑፎችን፦ 👉በFb እናጋራዋለን? 👉በ ቲክቶክና በዩቲዩብ ቪድዮ እንሠራለን(ከዚህ በፊት የመሥራት ልምድ ያለን) 👉 በቻናላችን ወይም በግሩፓችን ላይ እናጋራዋለን(ቻናል ወይም ግሩፕ ያለን) 👉ኦሮሚኛ መናገር የምትችሉ ወደ ኦሮሚኛ በመተርጎም ወይም ደግሞ የተተርጎሙትን ለሕዝባችሀ እንዲደርስ ታደርጋላችሁ? 👉ወይስ ዝምብላችሁ ነው ያላችሁት? በጥቂቱ ያልታመነ በብዙ አይሾምም https://t.me/EotcTaskForce

ምዕራብ ሐረርጌ አንጫር ወረዳ ያላችሁ ኦርቶዶክሳውያን ምን አዲስ ነገር አለ መረጃ አድርሱን

በኢትዮጵያ ምድር በመደበኛ ሠራዊት የሚደረገው ጦርነት ይሁን በኢመበደኛ ታጣቂዎች በሚፈጸመው ጥቃት የጥቃት ዒላማ የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ናት እያለቁ ያሉትም ልጆችዋ ናቸው

ይኽ ሁሉ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሲፈጸም እረኞቹ ምን ያደርጉ ነበር? 1) የገዳዩቹን ምንነትና ማንነት የማይገልጽ፣መንግሥት ኦርቶዶክሳውያንን መጠበቅ ግዴታው መሆኑን የማይገልጽ  ከ" እናዝናለን"ያላለፈ፣ኦርቶዶክሳውያንን መታደግ  የስላቅ መግለጫ ያወጡ ነበር 👉አጣሪ ኮሚቴ አቋቁመናል ፣ከመንግሥት ጋር እየተወያየን ነው፣ከሰላም ሚንስትር ጋር ተወያይተናል፣ተቻችሎ መኖር ወዘተ....እያሉ ኦርቶዶክሳውያንን ያደነዘዙ ነበር 👉 አንዳንዶቹ  በስውር ከመንግሥት ጋር  እየተወያዩ እልቂታችን እንዳይሰማ ሲዶልቱ ጠንካራ ኦርቶዶክሳውያንን ያሳስሩ ነበር 👉  መሠረት ድንጋይ ስለ ማስቀመጥ፣ስለ ህንጻ ምርቃቴ ፣ስለ በዓል ድምቀት፣ስለ ደሞዝ ጭማሪ፣ስለ ሀገራዊ   ምርጫ ፣ስለ ኮሪደር ልማት፣ስለ መናፈሻ እያወሩ  ሞታችንን ያፍኑት ነበር 👉የጠቅላይ ቤተ ክህነቱና የሀገረ ስብከት ሚዲያዎች" ከመንግሥት ጋር አታጣሉን" እያሉ ስለሞታችን እንዳይዘግቡ ይከለክሉ ነበር 👉 ሞት ብርቅ አይደለም በእኛም አልተጀመረም እያሉ ሕዝቡ ሞትን እተላመደ እንዲኖር ያደርጉ ነበር(አቡን ሲዊሮስ ኮዬ ፈጬ በዓል ለማክበር በተሰበሰበ  ሕዝትፊት የተናገሩት ነው) 👉የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አባ ኤልሳዕ ስለ ልጆቻቸው እንዳይናገሩ አንዳንዶቹ ይቆጡ ነበር ሀገረ ስብከቱስ ምን ያደርግ ነበር? 👉 ከሽርካ ከሦስት ቀበሌዎች ተፈናቅለው ቦቆጂ ከተማ የተጠለሉት የተወሰኑት እንዲመለሱ ጥቂት ጥረት አድርጓል ከዚያ ውውጭ ምንም የለም 👉የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ፍጅቱ ሃይማኖታዊ አይደለም እያለ  በሞታችን ይቀልድ ነበር 👉የሀገረ ስብከቱ   ሚዲያ የካቲት 19/2018  ግንቦት 23 በቀር በየቀኑ የሚፈጸሙ ፍጅቶችን አይዘግብም 👉ሀገረ ስብከቱን በተለያየ ውስጥ በተለያየ ሀላፊነት ላይ ያሉ ሰዎች ስለ ቋንቋና ስለ ስለዘር እያወሩ ደጋፊ እያደራጁ ኦርቶዶክሳውያንን ይከፋፍሉ ነበር የመንግሥት  መዋቅር ምን ያደርግ ነበር? 👉 ለአአክራሪ እስልምና ታጣቂዎች ትጥቅና ስንቅ ያቀርብ ነበር 👉ከአክራሪ ቡድኑ ግድያ የተረፉ ኦርቶዶክሳውያን ራሳቸውን ለማዳን እንዳይወጡ የጸጥታ አካላቱ ይከለክሉአቸው ነበር 👉 የወረዳ ባለሥልጣናት መከላከያ ጭፍጨፋው ወደሚፈጸምበት ስፍራ ሄዶ ኦርቶዶክሳውያንን እንዳይታደግ በሬ እያረዱላቸው ያዘገዩአቸው ነበር 👉ከኦርቶዶክሳውያን የተዘረፈውን ህብት ንብረት ከአክራሪ ቡድኑ ጋር ይካፈላሉ 👉ጥቃቱ ሃይማኖታዊ አይደለም እያሉ ያስተባብላሉ(ከወረዳው እስከ ፌዴራል መንግሥት) 👉ኦርቶዶክሳውያን ካህናትንና ሽማግሎችን እያስፈራሩ ፣ሐሰተኛ የሙስሊም ሽማግሎችና አባገዳዎችን አ ወደ ሚዳያ አውጥተው "ፍጅቱ ሃይማኖታዊ አይደለም"እንዲሉ ያደርጋል 👉 ከኦርቶዶክሳውያን የጸዱ አከባቢዎች ሙስሊሞች እንዲሰፍሩ ያደርጋሉ 👉ኦርቶዶክሳውያንን  ትጥቅና ጥይት እንግዛላችሁ እያሉ ብር ተቀብለው እጃቸው ባዶ እንዲሆን ካደረጉ በኋላ  አክራሪዎች መጥተው እንዲመቷቸው ያደርጋሉ 👉 ሀብት ንብረታቸውን ሸጠው የታጠቁ ኦርቶዶክሳውያንን ትጥቅ መቀማት 👉መረጃ እንዳይወጣ ማድረግ ፣በየቤቱ እየዞሩ መረጃ ብታወጡ እንፈጃችኋለን እያሉ ማስፈራራት

ክፍል_ሁለት በምሥራቅ አርሲ  ዞን ከየካቲት 16/2018ዓ.ም እስከ ሐምሌ 03/2018ዓ.ም በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶች  ለናሙና የቀረበ ሪፖርት ማሳሰቢያ፦ ጥቃቶቹ ለናሙና የቀረቡ ናቸው እንጂ የተፈጸሙት እነዚህ ብቻ ናቸል ማለት አይደለም 👉29/09/2018 በመርቲ ወረዳ ፈንቀሳ ቀበሌ በሕመም ምክንያት ከአዲስ አበባ ከሥራው አቋርጦ ጸበል ቆይቶ ወደ  ቤተሰቡ ቄኤ የተመለሰው አንድ ዶክተር የወረዳው ባለሥልጣናት በከተማ ውስጥ በኅቡዕ ባደራጃቸው አክራሪ የእስልምና ወጣቶች ጥቃት ተከፍቶበት ራሱን በመከላከሉ የመንግሥት ጸጥታ ኀይሎች ወደ ጫካ ወሰደው በአሰቃቂ ሁኔታ ከረሸኑ በኋላ እሬሳውን ሰውረውታል ቤተሰቦቹም እርማቸውን እንዳይወጡ ተከልክለዋል 👉15/10/ በሽርካ ወረዳ ሶሌ ዲገሉ ጉና ቀበሌ ደነቀ ለማ የተባለ ኦርቶዶክሳዊ ተገድሏል በዚሁ ቀን ሃይማኖታቸው ኦርቶዶክስ የሆኑ 2 ሚሊሾችና 4 የመከላከያ ኀይሎች በወረዳው ባለሥልጣናት በተቀነባበረ ሴራ ተገለዋል 6 ከፍተኛ አካላዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል 👉17/10/አሰኮ ወረዳ ሐሮ ቀበሌ ልዩ ቦታው ላፍቶታ አቶ ለገሠ ደምሴ የተባለ ኦርቶዶክሳዊ ሥራ ላይ እያለ በገጁራ ተቆራርጦ በተጥይት ተረሽኖ ተገድሏል 👉19/10/2018ዓ.ም   በሽርካ ወረዳ ቢርቦና ጮሌ ቀበሌ ልዩ ቦታው ጮሌ የሚባል አከባቢ ከ2ጥማድ(ገመድ) በላይ የሚሆን የኦርቶዶክሳውያን በርበሬ ተጨፍጭፎ ከጥቅም ውጭ እንዲሆን ተደርጓል 👉18/10/2018ዓ.ም በመርቲ ወረዳ  በሞለሞ ቀበሌ አቶ ደጀኔ ሩፌ የተበለ ኦርቶዶክሳዊ  በአሰቃቃ ሁኔታ ተገድሎ በጫካ ከተጣለ በኋላ እሬሳው በጅብ ተበልቶ ጭንቅላቱ ብቻ ተቀብሯል 👉በ24/10/2018ዓ.ም ጉና ወረዳ  ሬኤ አምባ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጦሴ መ/ር ተሾመ አጋ(የ42 ዓመት)እና ሚሚ ግርማ(24ዓመትና የ2 ልጆች እናት)ተገድለዋል፣መ/ር ብርሃኑ ለማ(የ52ዓመት) በጥይት ተመቶ ሆስፒታል ገብቷል እንዲሁም 3 ኦርቶዶክሳውያን ታግተው ተወስደዋል 👉24/10/2018ዓ.ም ሌሊት  በመርቲ ወረዳ ፈረንቀሳ ጃዊ ቀበሌ ልዩ ስሙ ሳጉሬ ቀርሳ  አቶ አባይ ታደሰ የተባሉ ኦርቶዶክሳውያን የተገደሉ ሲሆን ፣የቀሲስ ደምሰው ሰለሞን ሴት ልጃቸው ምሕረት ደምሰው፣ግርማ ገረሱ እና ሀና ገዛኸኝ የምትባል እናት ያለ አባት ያሳደገችው  የ12ዓመት ልጇን አግተው ወስደዋል እንዲሁም አቶ ካሣሁን ጃንካ የተባሉ ኦርቶዶክሳዊ ከብቶቻቸው በሙሉ  ተወስደውባቸዋል 👉 26/10/2018ዓ.ም  በሮቤ ወረዳ ሰዲቃ ቀርሳ ቀበሌ መ/ር ዘነበ ጌታቸው ይልማ እና አረጋኸኝ ላንዱ ይልማ የተባሉ ሁለት ኦርቶዶክሳውያን ወንድማማቾች ታግተው ተወስደዋል 👉ሰኔ 30/2018 ዓ.ም. በአርሲ ሀገረ ስብከት ሮቤ ወረዳ የሲቤ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ቄስ ጥላሁን ማሞ ከአንዲት እናት ጋር ታግተው ተወስደው ያሉበት አይታወቅም። 👉ሰኔ 30/2018ዓ.ም  በአሰኮ ወረዳ ቄስ ይስሙ የተባሉ አባት  ጨፌ ዩሚባል ቦታ ላይ የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸዋል 👉ሐምሌ 01/ 2018ዓ.ም በአሰኮ ወረዳ 4 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል 👉03/11/2018ዓ.ም በጢቾ ወረዳ   በሶሌ ምርጥ ቀበሌ ቡርቂቱ የሚባል አከባቢ 5 ኦርቶዶክሳውያን ከ25 የቀንድ ከብቶች ጋር ታግተው ተወሰደዋል

በምሥራቅ አርሲ  ዞን ከየካቲት 16/2018ዓ.ም እስከ ሐምሌ 03/2018ዓ.ም በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶች  ለናሙና የቀረበ ሪፖርት ማሳሰቢያ፦ ጥቃቶቹ ለናሙና የቀረቡ ናቸው እንጂ የተፈጸሙት እነዚህ ብቻ ናቸል ማለት አይደለም 👉በ16/07/2018  ሌሊት በሮቤ ወረዳ እንደቶ ቀበሌ የ67 ዓመት አዛውንት አቶ ፍቅረ ገብረመድኅን  የተባሉ ግለሰብ ተገድለዋል ፣6ከብቶቻቸው ተወስደዋል 👉በ21/07/2018ዓ.ም በመርቲ ወረዳ ከቢሮ ኮኛ ቀበሌ ከ80 ዓመት በላይ የሆኑት  አቶ በጋሻው ገብረሕይወት ተገድለዋል ✍ በ27/07/2018 ዓ.ም ቦሌ ከተማ ከሚካኤል ቤተክርስቲያን ሆሳናን ለማክበር ቤተክርስትያን አድረው ሲያስቀድሱ የነበሩትን እናቶች , ካህናትንና ህፃናት ከ1 አመት ጀምሮ ከ30 ሰው በላይ ኦርቶዶክሳውያን ታግተዋል። 👉መጋቢት28/2018ዓ.ም  ከአዳማ ወደ ጉና በመኪና ሲጓዙ የነበሩ 35 ኦርቶዶክሳውያንን ታግተው ወደ አርጀአኦ ጨካ ተወስደዋል 👉መጋቢት 26/2018ዓ.ም ከጉና ወረዳ ጎሎልቻ የሚሠሩ  80 መንገደኞች ኦርቶዶክሳውያን በአሰኮ ላይ ታግተዋል 👉መጋቢት26/2018ዓ.ም በመርቲ ወረዳ ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል 👉መጋቢት28/2018ዓ.ም ዲገሉና ጢጆ 2 ርቶዶክሳውያን ተገድለዋል ኦርቶዶክሳውያን የሚበዙባቸው ቀበሌዎች ላይ ከፍተኛ ተኩስ ተከፍቶባቸው  ጫካ ውስጥ እንዲቅበዘበዙ ተደርገዋል 👉መጋቢት 30 /2018ዓ.ም በአሰኮ ወረዳ ዲማ አሰኮ  ይልማ ገብረ መስቀል የተባሉ የ80 ዓመት አዛውንት በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ልጃቸውም የአካል ጉዳት ደርሶበታል።አዛውንቱን ከተገደሏቸው በኋላ አንገታቸውን ገዝግዘው ሆዳቸውን ቀደው ነው ጥሎአቸው የሄዱት 👉በ05/08/2018ዓ.ም በአሰኮ ወረዳ ዲማ አሰኮ በኦርቶዶክሳውያን ሌሊት ከፍተኛ ተኩስ ተከፍቶባቸው ከቤታቸር እንዳያድሩ ተደርገዋል 👉ሚያዝያ 12/2018ዓ.ም  ሌሊት በሮቤ ዲደዓ ወረዳ የጄና መብረቆ እግዚአብሔር አገልጋይ  ሙሌ  ፍሰሐ ከሁለት ወንድማማቾች ተገድለዋል የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑትን መምህር መሊዮን ገለቱን ጨምሮ ሦስት ኦርቶዶክሳውያን ታግተዋል 👉በ18/08/2018ዓ.ም በሽርካ ወረዳ ቢርቦና ጮሌ ቀበሌ የ80ዓመት አዛውንት አቶ ጀማነህ በላይሁን እና በግብርና ሲያገለግላቸው የነበረ ወጣት ዳግም አለማየሁ  ከቀኑ 10:00 ወደ መስክ የተሰማሩ ከብቶችን ሉማየት እንደወጡ ተገድለዋል 👉በ26/08/2018ዓ.ም  በሮቤ ዲደዓ ገደምሳ ቀበሌ ቦታ አየለ ጣሶየሚባል ኦርቶዶክሳዊ  እርሻ ላይ እያለ ተተኩሶበት ያመለጠ ሲሆን በሮቹ ተወስደውበታል ✍️በ06/08/2018ዓ.ም በሮቤ ዲደዓ ገደምሳ እርሻ ና ከብት ጥበቃ ላይ የነበሩ 8 ኦርቶዶክሳውያን ከ22 ከብቶች ጋር ተወስደዋል የተወሰዱት: 1. ተካልኝ እሼቱ 2. አቢቲ አበራ 3. ሚሊዮን ጂማ 4. ካሲዬ ፈለቅ 5. መብራቱ ታደሰ 6. አዲስ አባይነህ 7. መለሰ ጸጋዬ 8. አስናቀ አባይነህ 👉በወርኃ የካቲት ሮቤ ወረዳ 5 አምስት ኦርቶዶክሳውያን ተገድሏል 👉የካቲት 17 2018ዓ.ም በመርቲ ወረዳ ፈረቀሳ ቀበሌ 3 ኦርቶዶክሳውያን ተገድሉዋል 👉በ19/06/2018ዓ.ም በሽርካ ወረዳ ጃዊ ዋጬ ቀበሌ 21ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል 👉በ 20/06/2018ዓ.ም በሽርካ ወረዳ ጃዊ ዋጬ ቀበሌ 8ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል( ቤት ል) 👉በ 22/06/2018 በሽርካ ወረዳ ጢጆ ለቡ ቀበሌ አቶ ታደሰ (72ዓመት)እና በለጠ(70ዓመት) ተገድለዋል 👉በ23/06/2018ዓ.ም በጢቾ ወረዳ ቆሬ የሚባል ቦታ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ጥቃት ተፈጽሟል 👉በ14/07/2018ዓ.ም በጢቾ ወረዳ በሶሌ መደሮ ቀበሌ በመደሮ ታዳጊ ከተማ አቶ መኩራያ ዉቤ የተባለ ኦርቶዶክሳዊ ተገድሏል 👉በ19/07/2018ዓ.ም  በዲገሉና ጢጆ ወረዳ 16 ኦርቶዶክሳውያን ታግተው ተወስደዋል                                                                                                                                                                                                   1 ዘላለም እንግዳ አሰፋ 2.ተሻገር እንግዳ አሰፋ 3.ከተማ ከበደ ኦዳ 4.ከበበ ከበደ ኦዳ 5.ንጉስ በልሁ አስፋው 6.ሺፈራው በልሁ አሰፋው 7.ተፈሪ ሽመልስ 8.ሀብተሚካኤል 9.ለገሰ ተሾመ ማመጫ 10.አበራ ጠጋ አፍራሴ ከልጆቹ ማሞ አበራና ለማ አበራ ጋር 11.ተገኑ አበራ ጠጋ 12.አንድ የኅይማኖት አባት ከነሚስታቸው ነው የታገቱት 👉በ29/08/2018ዓ.ም በሽርካ ወረዳ  ሶሌ ነጌሌ ቀበሌ ሊዩ ስሙ ቱሉ ሪፌንሳ ሌሊት 5 ኦርቶዶክሳውያን ታግተዋል 👉 በ23/09/2018ዓ.ም በሽርካ ወረዳ በሚታና ዋጂ ቀበሌ ሌሊት በሦስት ወንድማቾች ላይ በተከፈተ ጥቃት ገነነ ጥላሁን እና ሙርቴሣ ጥላሁን በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ሲሆን ታግቶ ተወስዷል።ገነነ በቢለዋ የታረደ ሙርቴሣ በጥይት የተረሸነ። 👉 በ23/09/2018.ም በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ በሥልጣና ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ አቶ ንጉሤ ማንደፍሮና በቀለ ኃይሉሚካኤል የተባሉ 2 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል 👉በ23/09/2018ዓ.ም በአሰኮ ወረዳ ከ13 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል ከ280 በላይ ቤቶች ወድመዋል ከ 2800 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ተሰደዋል፣የ101ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረው የጠለታ ቅዱስ ደብርኤል ቤተ ክርስቲያን ተቃጥሏል የካራ ኩፍቴና መድኅንዓለም ቤተ ክርስቲያን ጉዳት ደርሶበታል 👉በ23/09/2018ዓ.ም በቀርሳ ሙኔሳ 2 ሁለት ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል 👉ሰኔ 1/2018ዓ.ም በመርቲ ወረዳ በጋዶ ቀበሌ በሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የተቀናጀ ተኩስ በከፍቶባቸው ሁብታቸው ተዘርፏል ለስደትም ተዳርገዋል 👉በ02/10/2018ዓ.ም በሆንቆሎ ዋቤ  ኦርቶዶክሳውያን ወንድማማቾች በእርሻ ላይ እንዳሉ ታግተው ተወስደዋል 👉ሰኔ 4/2018ዓ.ም ጳጳሳት ወደ አሰኮ እየሄዱ እያሉ በመርቲ ወረዳ ጋዶ  ከሚባል አከባቢ ተመልሰውዋል 👉ሰኔ 4/2018ዓ.ም በሽርካ ወረዳ በሶሌ ጉና ቀበሌ ከረፋዱ 4:00 እስከ ቀኑ 10:00 የተቀናጀ ተኩስ ተከፍቶባቸው ኦርቶዶክሱ ሊያጠፋው የመጣን ጠላት መክቶ መልሷል።ይኽ ሲፈጸም የመንግሥት የጸጥታ ኀይል ከ7ኪ.ሜ ርቀት ላይ ሆነው ይከታተሉ ነበር። 👉በ05/10/2018ዓ.ም በሽርካ ወረዳ በጃዊ ዋጬ ቀበሌ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት ተከፍቶባቸው ደሳለኝ ነጋሽ የሚባል ሰው ሲገደል 50 የቀንድ ከብቶች ተዘርፈዋል 👉ሰኔ 6/2018ዓ.ም ከመርቲ ወረዳ ተነስቶ ወደ አሰኮ  ወረዳ እየተጓዘ ባለው የሕዝብ ማመላለሻ  መኪና ላይ ጋዶ የሚባል አከባቢ  በተከፈተ የተከስ እሩምታ በመኪናው ውስጥ ያሉ ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ታግተው የተወሰዱ ሲሆን  2ዓመት የማይሞላት ህጻን ብቻቸዋን መኪና ውስጥ ቀርታለች 👉ሰኔ 08/2018ዓ .ም በሽርካ ወረዳ በሚታና ጋዶ ቀበሌ የመንበረ ስብሐት የጋዶ ማርያም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ቄስ አባይነህ ጠብቄ በእርሻ ላይ እያሉ ከእነ በሮቻቸው ከታገቱ በኋላ በ 10/10/2018ዓ.ም በአሰቃቂ ሁኔታ  ተገድለው በማያገለግሉበት ቤተ ክርስቲያን ላይ ተጥለው ተገኝተዋል 👉ሰኔ1እና 2/2018ዓ.ም በአርሲ አሳሳ ወረዳ ልዩ ቦታው ሻሼ  የሚባል ቦታ 33 ኦርቶዶክሳውያን የሚሊሻ ኀይሎች  በሴራ እንዲገደሉ ተደርጓል። ይቀጥላል......

አርሲ አሰኮ የኦርቶዶክሳውያን ግድያ በምስራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ሰምቦ ቀበሌ ዳኛም የለው በሚባል ቦታ ትናንት ሐምሌ 04/2018ዓ.ም ቅዳሜ ምሽት 12:00 ለይ አቶ ተፈራ ካሳዬ የ 87 ዓመት
+1
አርሲ አሰኮ የኦርቶዶክሳውያን ግድያ በምስራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ሰምቦ ቀበሌ ዳኛም የለው በሚባል ቦታ ትናንት ሐምሌ 04/2018ዓ.ም  ቅዳሜ ምሽት 12:00 ለይ አቶ ተፈራ ካሳዬ የ 87 ዓመት አዛውንት  በ አክራሪ የእስልምና ታጣቂዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ይህ በኦርቶዶክሳዊያን ጥላቻ የታወረ ቡድን እንደዚህ ያለ ዘግናኝ እና ፍፁም አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ላለፉት ስምንት አመታት በነጥሎ ማጥቃት እንደዚሁም በጅምላ ግድያ  ቤተክርስቲያን እንደ ጧፍ በማቃጠል የኦርቶዶክሳዊን ቤት እና ንብረት በመዝረፍ በማዉደም እገታ በመፈፀም አግቶ ሚሊዮን ብሮችን በመጠየቅ እንደዚሁም ሴት እህቶቻችን እናቶችንን በጅምላ በመድፈር የሰው ልጅ አይደለም ሊያደርገዉ ይቅርና ለማሰብ እንኳን የሚከብድ ዘግናኝ እልቂት በአርሲ ምድር መቋጫ በሌለው መልኩ እየተካሄደ ነው።ይኽ ሁሉ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሚፈጸመው በመንግሥት መዋቅር ነው።

አርሲ አሰኮ የኦርቶዶክሳውያን ግድያ በምስራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ሰምቦ ቀበሌ ዳኛም የለው በሚባል ቦታ ትናንት ሐምሌ 04/2018ዓ.ም ቅዳሜ ምሽት 12:00 ለይ አቶ ተፈራ ካሳዬ የ 87 ዓመት
+1
አርሲ አሰኮ የኦርቶዶክሳውያን ግድያ በምስራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ሰምቦ ቀበሌ ዳኛም የለው በሚባል ቦታ ትናንት ሐምሌ 04/2018ዓ.ም  ቅዳሜ ምሽት 12:00 ለይ አቶ ተፈራ ካሳዬ የ 87 ዓመት አዛውንት በ አክራሪ የእስልምና ታጣቂዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ይህ በኦርቶዶክሳዊያን ጥላቻ የታወረ ቡድን እንደዚህ ያለ ዘግናኝ እና ፍፁም አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ላለፉት ስምንት አመታት በነጥሎ ማጥቃት እንደዚሁም በጅምላ ግድያ  ቤተክርስቲያን እንደ ጧፍ በማቃጠል የኦርቶዶክሳዊን ቤት እና ንብረት በመዝረፍ በማዉደም እገታ በመፈፀም አግቶ ሚሊዮን ብሮችን በመጠየቅ እንደዚሁም ሴት እህቶቻችን እናቶችንን በጅምላ በመድፈር የሰው ልጅ አይደለም ሊያደርገዉ ይቅርና ለማሰብ እንኳን የሚከብድ ዘግናኝ እልቂት በአርሲ ምድር መቋጫ በሌለው መልኩ እየተካሄደ ነው።ይኽ ሁሉ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሚፈጸመው በመንግሥት መዋቅር ነው።

አርሲ አሰኮ የኦርቶዶክሳውያን ግድያ በምስራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ሰምቦ ቀበሌ ዳኛም የለው በሚባል ቦታ ትናንት ሐምሌ 04/2018ዓ.ም ቅዳሜ ምሽት 12:00 ለይ አቶ ተፈራ ካሳዬ የ 87 ዓመት
+1
አርሲ አሰኮ የኦርቶዶክሳውያን ግድያ በምስራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ሰምቦ ቀበሌ ዳኛም የለው በሚባል ቦታ ትናንት ሐምሌ 04/2018ዓ.ም  ቅዳሜ ምሽት 12:00 ለይ አቶ ተፈራ ካሳዬ የ 87 ዓመት በመኖሪያ ቤቱ በመምጣት በደም መጣጩ እና በደም አፍሳሹ ስብስብ ኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ይህ በኦርቶዶክሳዊያን ጥላቻ የታወረ ቡድን እንደዚህ ያለ ዘግናኝ እና ፍፁም አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ላለፉት ስምንት አመታት በነጥሎ ማጥቃት እንደዚሁም በጅምላ ግድያ  ቤተክርስቲያን እንደ ጧፍ በማቃጠል የኦርቶዶክሳዊን ቤት እና ንብረት በመዝረፍ በማዉደም እገታ በመፈፀም አግቶ ሚሊዮን ብሮችን በመጠየቅ እንደዚሁም ሴት እህቶቻችን እናቶችንን በጅምላ በመድፈር የሰው ልጅ አይደለም ሊያደርገዉ ይቅርና ለማሰብ እንኳን የሚከብድ ዘግናኝ እልቂት በአርሲ ምድር መቋጫ በሌለው መልኩ እየተካሄደ ነው።ይኽ ሁሉ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሚፈጸመው በመንግሥት መዋቅር ነው።

ዛሬ ስለ ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ይሰብካል ተጋድሎአቸው ይገራል ይዘመራል ነገር ግን፦ 👉ጴጥሮስ ወጳውሎስ የሞቱላት ቅድስት ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ስደት ላይ ናት፣ 👉ጴጥሮስ ወጳውሎስ የሰበኩት
ዛሬ  ስለ ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ይሰብካል ተጋድሎአቸው ይገራል  ይዘመራል  ነገር ግን፦ 👉ጴጥሮስ ወጳውሎስ የሞቱላት ቅድስት ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ስደት ላይ ናት፣ 👉ጴጥሮስ ወጳውሎስ  የሰበኩት ወንጌል  ተሰዶ ገንዘብ በ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነግሷል 👉ጴጥሮስ ወጳውሎስ የቆሙበት ዓውደምሕረት ቧልትና አድርባይነት የሚንጸባረቅበት ሆኑአል 👉የጴጥሮስ ወጳውሎስ ሥልጣነ ክህነት በስሑታን ሰዎች እጅ ላይ ወድቆ የእንጀራ መብያ፣የመኪና መግዣ፣የፎቅ መሥሪያ፣የጸረ ኦርቶዶክስ ፖለቲከኞች ማወደሻ ሆኑአል 👉ጴጥሮስ ወጳውሎስ በአደባባይ፣ በነገሥታት እና በአሕዝብ ፊት የመሰከሯት እውነት ከ ቤተ ክርስቲያን ተሰዳለች( በ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆኖ ስለ ቤተ ክርስቲያን መናገር ወንጀል ሆኑአል) 👉የጴጥሮስ ወጳውሎስን አሰረፍኖተ የተከተሉ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ካህናት እና ምዕመናን  እንደ ቤተ ክርስቲያን ጠላት ተቆጥረው ወደ እስርቤት እየተወረወሩ ነው፣ከሀገር ወጥተው እየተሰደዱ ነው፣ከሀገር መውጣት ያልቻሉት በየጫካው በመንከራተት ላይ ናቸው ስልታዊ በመሆነ መንገድ የሚገደሉም አሉ 👉ጴጥሮስ ወጳውሎስ  በወንጌል አንድ ያደረጉት ሕዝብ በስሑት ፖለቲከኞችና ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተሰገሰጉ ዘረኞች ና ጎጠኞች እየተከፋፈለ እየተገዳደለ ነው እግዚአብሔር በምሕረቱ ይመልከተን

#ቅዱስ_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ ሐምሌ ፭ ቀን የዓበይት ሐዋርያት የቅዱስ ጴጥሮስንና የቅዱስ ጳውሎስን የሰማዕትነት ዕረፍት መታሰቢያ ቤተ ክርስቲያናችን በታላቅ ክብር ታከብራለች። #ቅዱስ_ጴጥሮስ ከቤተ ሳይዳ
#ቅዱስ_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ ሐምሌ ፭ ቀን የዓበይት ሐዋርያት የቅዱስ ጴጥሮስንና የቅዱስ ጳውሎስን የሰማዕትነት ዕረፍት መታሰቢያ ቤተ ክርስቲያናችን በታላቅ ክብር ታከብራለች። #ቅዱስ_ጴጥሮስ ከቤተ ሳይዳ ዓሣ አጥማጅነት ተጠርቶ የሐዋርያት አለቃና የቤተ ክርስቲያን መሠረት የሆነው ቅዱስ ጴጥሮስ፣ የመንግሥተ ሰማያትን መክፈቻ ቁልፍ የተቀበለ ታላቅ አባት ነው። በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተሞልቶ በልዩ ልዩ ሀገራትና በሮም አደባባይ ወንጌልን ሲሰብክ፣ ሙታንን በማስነሣት፣ ድውያንን በመፈወስና የጥፋት አገልጋይ የነበረውን ስምዖንን በማሳፈር አስደናቂ ተአምራትን አድርጓል። በመጨረሻም በንጉሥ ኔሮን ትእዛዝ የሞት ፍርድ ሲፈረድበት፣ "እንደ ጌታዬ ቀጥ ብዬ ልሰቀል አይገባኝም" በማለት በትሕትና ቁልቁል በመሰቀል የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጅቷል። #ቅዱስ_ጳውሎስ የቤተ ክርስቲያን መብራት የተባለው ቅዱስ ጳውሎስ አስቀድሞ ምእመናንን አሳዳጅ የነበረ ቢሆንም፣ በደማስቆ መንገድ በተገለጠለት የጌታችን ጥሪ ምርጥ እቃ የተባለ ሐዋርያ ለመሆን በቅቷል። በብዙ አገራት እየተዘዋወረ በሚያስተምርበት ወቅት መገረፍን፣ መታሠርንና በእሳት መቃጠልን የመሳሰሉ ጽኑ መከራዎችን በጸጋ በመቀበል፣ ድንቅ ተአምራትን በማድረግና ዐሥራ አራት መልእክታትን በመጻፍ ለክርስቲያኖች የሃይማኖት መሠረት ጥሏል። እርሱም በንጉሥ ኔሮን ትእዛዝ አንገቱን በሰይፍ ተቆርጦ የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጅቷል። የእነዚህ የሁለቱ ቅዱሳን ሐዋርያት ሕይወት፣ ትምህርትና ተጋድሎ እስከ ዘላለም ድረስ ለምእመናን የጽናት፣ የእምነትና የድኅነት መንገድ ሆኖ ይኖራል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳት ሐዋርያት ጸሎት ይማረን በረከታቸው የቅዱሳት ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።

አብዛኞቻችን የሚዲያውን ጦርነት ደተረዳን አይመስለኝም

አርሲ1.pdf1.67 KB

የአርሲው ጥቃት (ናሙና የቀረበ) 👉ጥናቱ በ10 ወረዳዎች የተፈጸሙ ጥቃቶችን ያካትታል 👉 ከየካቲት 16/2018ዓ.ም እስከ ሐምሌ 03/2018ዓ.ም ድረስ ያለውን ጊዜ የሚዳስስ ነው ፦ 👉46 ጊዜ
+4
የአርሲው ጥቃት (ናሙና የቀረበ) 👉ጥናቱ በ10 ወረዳዎች የተፈጸሙ ጥቃቶችን ያካትታል 👉 ከየካቲት 16/2018ዓ.ም እስከ ሐምሌ 03/2018ዓ.ም ድረስ ያለውን ጊዜ የሚዳስስ ነው ፦ 👉46 ጊዜ ጥቃት ተፈጽሟል 👉 25 ጊዜ የግድያ ጥቃቶች ተፈጽመዋል 👉ከ 121 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል 👉13 ጊዜ የእገታ ጥቃት ተፈጽሟል