ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Ir al canal en Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Mostrar más2 955
Suscriptores
+1424 horas
+247 días
+38330 días
Archivo de publicaciones
64ኛ ክ/ጦር ቃኝና መሃንዲስ የሰረጎ ገብ ጥቃት ሰነዘረ!
64ኛ ክ/ጦር ግንቦት 27/2018 ዓ.ም
~~~~~~~~
በእነማይ ወረዳ ማህበረ_ብረሃን ቀበሌ የትኖራ ጎጥ በሚገኘው የአገዛዙ ሰራዊት ካንፕ ላይ 64ኛ ክ/ጦር ቃኝና መሃንዲስ ሰርጎ በመግባት በወሰደው F1 ቦንብ ጥቃት በማህበረብረሃን ቀበሌ ህዝብን ያሰቃይ የነበረው #እያሱ አበበ የተባለ ቅጥርኛ ሚሊሻ ቁርጭምጭምቱን ተመቶ ቢቸና የመጀመረያ ደረጃ ሆሲፒታል ከባድ ቁስለኛ መሆኑ ተረጋግጦል።
በተሰነዘረው የሰረጎ ገብ የቦንብ ጥቃት እና የተኩስ ልውውጥ ለግዜው ስማቸው ማወቅ ያልቻልናቸው የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ሙት እና ቁስለኛ ሆነዋል።
በዚህ ጥቃት ጉዳት ያስተናገደው የአገዛዙ ሰራዊት አባላት የአካባቢው ማህበረሰብን ላይ ከባድ ድብደባ እና ህገወጥ ፍተሻ በማካሄድ ዘረፋ ፈፅሟል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ግንቦት27/2018 ዓ.ም
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
መሪ ቃል፦ “የአማራ ማንነት የህልውናችን መሰረት ነው፤ ግፉ ይበቃል!”
ከለንደን ፋኖ የተሰጠ መግልጫ
ግንቦት 27/2018
በአርሲ ዞን በንጹሃን የአማራ ተወላጆች እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ። በአርሲ ምድር በንጹሃን ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ እና የቤተክርስቲያን መቃጠል፣ ግልጽ የሆነ የአማራን ማንነት የማጥፋትና የእምነት ተቋማትን የማዳከም ስልታዊ ጥቃት አካል ነው። ለንደን ፋኖ ይህንን ግፍ በጽኑ እየኮነነ የሚከተለውን መግለጫ ያወጣል፦
፩. ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት በአርሲ የተፈጸመው ጥቃት ተራ ወንጀል ሳይሆን፣ የአማራን ማንነት እና የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነትን ኢላማ ያደረገ የዘር ማጥፋት (GENOCIDE) ሙከራ ነው። አማራ በመሆኑ ብቻ በገዛ ሀገሩ የሚታረደው ወገናችን ስቃይ የሁላችንም ስቃይ ነው። ይህ ግፍ የአማራን ህዝብ ለዘመናት ከኖረበት ቀየው የማፈናቀል ሰፊ ሴራ አካል መሆኑን እንገነዘባለን።
፪. ጥልቅ ሀዘንና የቁጭት መግለጫ በግፍ የታረዱ እናቶችን፣ ህጻናትንና አረጋውያንን እያሰብን ልባችን በሀዘን ተሰብሯል። ለተገደሉት ቤተሰቦች በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን። ሆኖም ግን ሀዘናችን በዝምታ የሚታለፍ ሳይሆን፣ ለፍትህና ለህልውና የምናደርገውን ትግል ይበልጥ የሚያበረታ ቁጭት መሆኑን እናውጃለን።
፫. የዝምታው ግብረ-አበሮች ንጹሃን የአማራ ተወላጆች በማንነታቸው ምክንያት እየተለዩ በሚታረዱበት፣ ቤታቸውና የእምነት ተቋሞቻቸው በሚቃጠሉበት በዚህ ወቅት መንግስታዊ ዝምታ የጥቃቱ ተባባሪነት ማረጋገጫ ነው። የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና ሁሉም የህሊና ሰዎች ይህን ግልጽ የዘር ማጥፋት ድርጊት እንዲያወግዙና ለተጎጂዎች ድምጽ እንዲሆኑ እንጠይቃለን።
፬. ለአማራ ህዝብና ለደጋፊዎቻችን የቀረበ ጥሪ በእንግሊዝ እና በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን እና የአማራ ልጆች፦
፬.፩. የማንነት ጥቃቱን ማጋለጥ፦ በአርሲ የተፈጸመው ግፍ የአማራ ማንነት ላይ የተሰነዘረ ጥቃት መሆኑን ለዓለም አቀፍ ተቋማትና ለመገናኛ ብዙሃን እንድታሳውቁ::
፬.፪. አጋርነት፦ በታላላቅ የጸሎት፣ የሻማ ማብራት እና የሰላማዊ ሰልፍ መርሃ-ግብሮች ከተጎጂዎች ጋር ያላችሁን አጋርነት እንድታሳዩ::
፬.፫. ድጋፍ፦ ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ወገኖቻችን አስፈላጊውን ሰብአዊ ድጋፍ በማሰባሰብ እንድትረዱ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
፭. የለንደን ፋኖ ቁርጠኝነት የለንደን ፋኖ ከአማራ ማንነቱና ከእምነቱ የተነሳ መከራ ለሚቀበለው ህዝባችን መከታ ሆኖ ይቆማል። የአማራን ህልውና፣ ክብር እና ሰላም ለማስጠበቅ የሚደረገውን ትግል በሁሉም አቅጣጫ እንደምናጠናክር ቃል እንገባለን። ተጎጂዎች አይረሱም፤ የግፈኞች እጅም ከፍትህ አያመልጥም! ::
ማጠቃለያ ፈጣሪ ለተገደሉት ዘላለማዊ እረፍትን፣ ለተጎዱት መጽናናትን፣ ለህዝባችን ጥንካሬንና አንድነትን ይስጥ።
ለንደን ፋኖ (LONDON FANO)
ድምጽ ለድምጽ አልባዎች!
ድል ለአማራ ህዝብ!
© ወርቁ ተሾመ
የለንደን ፋኖ ሰብሳቢ
የአገዛዙ ሰራዊት በየቀኑ እየፈረሰ ፋኖን እየተቀላቀለ ነው‼️
ግንቦት 27/2018 ዓ/ም የአገዛዙ 9/ዘጠኝ/ የሰራዊት አባላት 105ኛ ኮር 66ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል።
አብይ አህመድ እና ጭፍሮቹ የስልጣን ወንበራቸውን ለማስጠበቅ በርካታ የድሃ ልጆችን ወደ ጦርነት እየማገዱ በየቀኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ የብልፅግና ሰራዊት አባላት እንደ ቅጠል በዱር በገደሉ እየረገፉ ይገኛሉ።
አላማ በሌለው ጦርነት ህይወታቸውን መሠዋት ያልፈለጉ የሠራዉት አባላት ከደቅ ከተማ ከመሸገው ጨፍ*ጫፊ ሰራዊት በመኮብለል ከእነ ሙሉ ትጥቃቸዉ የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክ/ጦርን ተቀላቅለዋል። ክፍለጰጦሩን የተቀላቀሉ የአድማ ብተና አባላት :-
1.ይበልጣል መላኩ= አድማ በትን
2.ይመር አያና= አድማ ብተና
3.ሀብቴ ዘሪሁን=አድማ ብተና
4.ፈንታሁን ድረስ=አድማ ብተና
5.አበዉ ደሴ= አድማ ብተና
6.እንዳልክ=መከላከያ-ከፓዊ
7.ወርቁ አዲሱ= አድማ ብተና
8.አለኸኝ ግፉ=አድማ በተና
9.አስር አለቃ ሰለሞን አስማማዉ= መከላከያ _ከጃዊ ፈንድቃ
አንድ የአድማ በተናን አባል ብቻዉን 3 ክላሽንኮቭ ይዞ በመዉጣት ከታሪክ ሰሪው የፋኖ ሰራዊት ጋር በመቀላቀል ታሪክ ሰርቷል ሲል የ66ኛ ክፍለ ጦር ከስፍራው ዘግቦታል።
አፍብን ቴዎድሮስ ዕዝ የ105ኛ ኮር ሕ/ግንኙነት
በተሰራ ልዩ ኦፕሬሽን 11 የሚሊሻ አባላት ሲማረኩ አንድ የአገዛዙ 112ኛ አየር ወለድ ክፍለጦር አባል ዘመናዊ ስናይፐር በመያዝ የራስ አበበ አረጋይ ከፍለጦርን ተቀላቅሏል።
ግንቦት 27/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለጦር በመርሀቤቴ አውራጃ ሬማ ከተማ ዙሪያ በአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት ላይ በተቀናጀ መልኩ የተጠና እርምጃ እየወሰደ ሲሆን የአፄ ዳዊት ክፍለጦር የፋኖ ሰራዊት ትላንት አመሻሹን ባደረጉት ልዩ ኦፕሬሽን 9 የሚሊሻ አባላት በክፍለጦሩ ታደለ ጠና ሻለቃ የተማረኩ ሲሆን ሁለት የሚልሻ አባላት ዛሬ አዳራቸውን ከተጠረነፉበት ካምፕ በማምለጥ በፈቃዳቸው ፋኖን ተቀላቅለዋል:: በጥቅሉ የአገዛዙ ቀኝ እጅ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ 11 የሚሊሻ አባላትን ከብልፅግናው ጥምር ጦር ትዕዛዝ ውጭ ማድረግ ተችሏል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ የብልፅግናው 112ኛ አየር ወለድ ክፍለጦር 4ኛ ሻለቃ አባል የሆነው ፲ አለቃ ገመቹ ፈይሳ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አካል የሆነውን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር የራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦርን አንድ ዘመናዊ ስናይፐር ከነ ሙሉ ትጥቁ በመያዝ ፋኖን ተቀላቀለ::
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
ድል ለአማራ ሕዝብ!
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ
+3
የመከላከያ ምክትል ሻንበል መሪው እና አባላቱ በዛሬው እለት ከደበረወርቅ እና ከሞጣ ከተማ በመውጣት ፋኖን ተቀላቅለዋል።
ግንቦት 26/2018 ዓ.ም
በዛሬው እለት ወደ 201ኛ ኮር 74ኛእና 54ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት
1ኛ.መኳንንት መኩሪያው.....ፓራ ኮማንዶ ወደ 74ኛክ/ጦር
2ኛ.ሞላልኝ ላመስግን......አድማ ብተና ወደ 74ኛክ/ጦር
3ኛ.ሐብታሙ ታደሰ....መከላከያ 54ኛክ/ጦር የተቀላቀሉ ሲሆን በክፍለ ጦር አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የአብይ አህመድ ስርዓት በአማራ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለው የጅምላ ጭፍጨፋ እና የአረብ አገር ድሮኖች የዕለት ተዕለት እሳት፣ ለአለም ህዝብ ግልጽ የሆነ የምድር ሀቅ ነው። ይህ ስልታዊ ጥፋት የአማራን ህዝብ ብቻ ሳይሆን መላዋን ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተወጠነ ነው።
ይህንን አምባገነናዊ እና አረመኔያዊ ስርዓት ለመቀልበስ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድነትና በነቂስ ወጥቶ መቃወም ይኖርበታል።
👉 ይህ ምርጫ አይደለም — የህልውና ግዴታ ነው!
📌 ዛሬ ለአማራ ወገንህ ካልቆምክ፣ ነገ ተራው የአንተ ነው!#Dawit Amhara ከንጉሶች መንደር!
#StopAmaraGenocide #Ethiopia #StandTogether #Unity Is Strength
የአማራ ፋኖ በጎንደር፡ የደጀን እዝ ወሳኝ ድል – በደበቻ ከተማ የተደረገው የተሳካ የደፈጣ ጥቃት
ጎንደር፤ ሰሜን ቀጠና — የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አ ፋ ብ ሐ) ስር የሚገኘው የሰሜን ቀጠና የ“በላይ ዘለቀ እዝ”፤ “ታድሎ ብርሃን ክፍለ ጦር” በጠላት ኃይሎች ላይ የደፈጣ ጥቃት በመሰንዘር ታላቅ ድል ተቀዳጅቷል።
እንደ እዙ የህዝብ ግንኙነት መረጃ ከሆነ፤ ጥቃቱ የተፈጸመው ከአዘዞ ወደ አይባ መስመር በመጓዝ ላይ በነበረው የጠላት ሚኒሻ ኃይል ላይ ነው። የፋኖ ጀግኖች አባላት ባደረጉት ጥንቃቄ የተሞላበት የደፈጣ ስልት፣ የጠላት ኃይል በደበቻ አካባቢ ሲደርስ አስደንጋጭ ጥቃት በመክፈት ሙሉ በሙሉ እንዲንበረከክ ተደርጓል።
የዘመቻው ዋና ዋና ነጥቦች፡
ስልታዊ ጥቃት፡ የፋኖ ክፍለ ጦሩ ጠላትን ባልጠበቀው ሰዓትና ቦታ መታው። የተፈጠረው ድንገተኛ ጥቃት የጠላት ኃይል የመከላከል አቅም እንዳይኖረው በማድረግ፣ እንዲደናገጥና መውጫ እንዲያጣ አድርጎታል።
የታጠቁ ኃይሎች እጅ መስጠት፡ በጥቃቱ የተመታው ሚኒሻ፣ የፋኖን ብርቱ ምት መቋቋም በማይችልበት ደረጃ በመደረሱ፤ የነበረውን ሙሉ ትጥቅና መሳሪያ ይዞ እጅ ለመስጠት ተገዷል።
የአካባቢው ቁጥጥር፡ በዚህ ወሳኝ ድል አማካኝነት በደበቻ አካባቢ የተደረገው የደፈጣ ጥቃት፣ የፋኖን የመከላከልና የማጥቃት አቅም በግልጽ ያሳየ ሲሆን፤ አካባቢው በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የበላይ ዘለቀ እዝ የ“ታድሎ ብርሃን ክፍለ ጦር” አባላት፣ አሁንም በየአቅጣጫው የሚደረገውን የጠላት እንቅስቃሴ በንቃት እየተከታተሉ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። ይህ ድል በፋኖ ጀግኖች መካከል ከፍተኛ የሞራል መነሳሳትን የፈጠረ ሲሆን፤ ህዝቡም ለፋኖ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።
ይህ ዘገባ የፋኖ ኃይሎች በየአካባቢው እየሰነዘሩት ያለው የማጥቃት እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን የሚያሳይ ሌላኛው ማሳያ ነው።
ግንቦት 26/2018 ዓ/ም አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ106ኛ ኮር 22ኛ ክፍለጦር ክንዱ በአሻግሬ ሻለቃ በተደረገ ደፈጣ በርካታ የጥላት ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ተደረገ!
ከጋሸና እና ፍላቂት በዙ-23 ታጅቦ ሬሽን ሊቀባበል በመጣ የጥላት ሰራዊት ላይ መቄት ወረዳ አንቺም ኪዳነ ምህረት ከተባለ ቦታ ላይ በክንዱ አሻግሬ ሻለቃ በተደረገ ደፈጣ ከ07(ሰባት)በላይ ሲደመሰሱ፤በርካቶች ቁስለኛ ተደርገው ጋሸና ጤና ጣቢያ የገቡ ሲሆን፤ሬሽን አጅቦ የመጣው ዙ-23 በፋኖዎች በተተኮሰ ብሬን ተመቶ ከጥቅም ውጭ ሲደረግ ጥላት ያለ የለለውን ሀይል ተጠቅሞ የተመታውን ዙ-23 እና ሙት አስከሬኑን አንስቶ ወደ ጋሸና ፈርጥጧል።
በቀኝአዝማች ጨለፍ ተስፋው እየማሉ ጠላትን ምድር ላይ የሚያነጥፉት የመቄቶቹ አናብስቶች ሞት የጠራውን የብርሀኑ ጁላን ስልብ ሰራዊት በመጣበት ቋንቋ ያነጋገሩት ሲሆን የጥላትን ሰራዊት ቅስም የሚሰብር የደፈጣ ጥቃትን ሙሉ በሙሉ የአሸናፊነት አቅም ማጥቃት ተችሏልል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የ106ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 26/2016 ዓ/ም
+3
የመከላከያ ምክትል ሻንበል መሪው እና አባላቱ በዛሬው እለት ከደበረወርቅ እና ከሞጣ ከተማ በመውጣት ፋኖን ተቀላቅለዋል።
►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
.......ግንቦት 26/2018 ዓ.ም
በዛሬው እለት ወደ 201ኛ ኮር 74ኛእና 54ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት፦
1ኛ.መኳንንት መኩሪያው.....ፓራ ኮማንዶ ወደ 74ኛክ/ጦር
2ኛ.ሞላልኝ ላመስግን......አድማ ብተና ወደ 74ኛክ/ጦር
3ኛ.ሐብታሙ ታደሰ....መከላከያ 54ኛክ/ጦር የተቀላቀሉ ሲሆን በክፍለ ጦር አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
በምንጀር ሸንኮራ ወረዳ በተደረገ ውጊያ የአገዛዙ ሀይል ከፍተኛ ጉዳት አስተናግዷል።
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ምንጀር ሸንኮራ ወረዳ በሸ/ጠ/ግ/ አሳምነው ዕዝ ከሰም ኮር ነበልባል ክ/ጦር እና በአባት አርበኞች ጦር በትናንትናው ዕለት በነበረ ከፍተኛ የደፈጣ ጥቃት፣ በአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት መድረሱን የኮሩ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታወቀ።
ይህ የተሳካ ኦፕሬሽን የተፈፀመው በትናንትናው ዕለት ግንቦት 25 /2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡15 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 1፡30 ሰዓት ድረስ ለረጅም ሰዓታት በቆየ ከባድ ውጊያ ሲሆን በውጊያውም በአገዛዙ ሀይል ላይ ከፍተኛ ቁሳዊና ሰብአዊ ኪሳራ ማድረስ ተችሏል። ይኸው ወታደራዊ እርምጃ የተወሰደው በአሞራቤት ቀበሌ መልካጅሎ የምርጫ ጣቢያ የተሰበሰበውን የምርጫ ኮረጆ ይዞ ሲመለስ በነበረው የብልፅግና ጥምር ጦር ላይ እንደሆነ ተገልጿል።
የተወሰደውን እርምጃ በከስም 2ኛ ኮር የነበልባል ክፍለ ጦር ሻለቃ ፋኖዎች እና በአባት አርበኛ ፋኖ ጥምረት የተከናወነ ሲሆን፣ ጥቃቱ የተፈጸመው በጨሌ ቀበሌ ልዩ ስማቸው «ጁምድር» እና «አጉጭ» በተባሉ አካባቢዎች ላይ በተደረገ የተቀናጀ የደፈጣ ውጊያ ነው።
በዚህ ለሰዓታት በቆየው የተኩስ ልውውጥ በአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ ከፍተኛ ጉዳት በመድረሱ በእውር ድንብር ሽፋን በመሰጣጠት አስከሬኑን ሳይሰበስብ የወጣ ቢሆንም የፋኖ ኃይል ላይ ግን ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰም።
የመረጃ ምንጭ- የኮሩ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ክብርና ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት⚠️
በጋውና ዙሪያ የድሮን ቅኝት እየተደረገ ይገኛል❗️
ከረፋዱ 3:55 ጀምሮ...
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም
በአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጭፍጨፋ አስመልክቶ ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምስራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኙ ወረዳወች ነዋሪ የሆኑ የቤተ ክህነቷ ታላላቅ አባቶች፣ ካህናት እና ምዕመናን ላይ በደረሰባቸው ጭፍጨፋ ከፍተኛ ሀዘን የተሰማው መሆኑን ይገልፃል።
የምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት እንዳሳወቀው ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ:ም ጀምሮ በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ ወረዳ፣ በሺርካ ወረዳ እና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ በርካታ ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ የ101 ዓመት እድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።
የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል።
በተጨማሪ በአሰኮ ወረዳ ከ280 ሰው በላይ ተፈናቅለዋል። ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በሃይማኖታቸው ብቻ ቤታቸው እየተለየ ተቃጥሏል፤ ንብረታቸውና ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል። ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎችም ይዘውት የሸሹት እምነታቸውንና ማንነታቸውን ብቻ በመሆኑ አሁን ላይ ሜዳ ላይ ወድቀው ይገኛሉ።
አርሲን ጨምሮ የእምነት፣ የቋንቋ እና የማንነት ብዝሃነት ባለባቸው አካባቢወች ላይ ኢ-መደበኛ ኃይሎችን በማደራጀት በዜጎች ላይ ሽብር የሚፈፅመው የብልፅግና አገዛዝ መሰል የዘር ማጥፋት ወንጀልን በግልፅ እና በስውር ሲፈፅም ይህ የመጀመሪያዉ አይደለም። በዚህ ዓመት በምስራቅ አርሲ ዞን በብዙ መቶወች የሚቆጠሩ ኦርቶዶክሳውያን በተመሳሳይ መንገድ ተገድለዋል። በርካታ ምዕመናንም የደረሱበት አይታወቅም።
በመሆኑም ይህ ጉዳይ ለህዝብ ጀሮ እንዲደርስ ያደረጉ የሚዲያ አካላትን እና የተፈፀመውን የሽብር ተግባር ያወገዙ የፖለቲካ ኃይሎችን እያመሰገንን፤ ጨፍጫፊውን የብልፅግና ስርዓት ለማስወገድ እየታገላችሁ ያላችሁ የኦሮሞ የፖለቲካ ኃይሎችና ተፅዕኖ ፈጣሪ ፖለቲከኞች መሬት የወረደ ትግል በማድረግ በኦሮሚያ ክልል የሚኖረው አማራ ህዝብ ህልውናው እንዲከበር የበኩላችሁን እንድታደርጉ ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የሀገር ውስጥ እና ዓለም ዓቀፍ ሰብዓዊ መብት ማንነትን እና ሃይማኖትን መሰረት ያደረገውን መንግስት መር ጭፍጨፋ በዝምታ ማየታችሁ ከመተባበር ተለይቶ የማይታይ በመሆኑ የአሁኑን ጨምሮ ከዚህ በፊት የተፈፀሙት የሽብር ተግባራት ተጣርተው በአገዛዙ ላይ ዲፕሎማሲያዊ እርምጃ እንዲወሰድ ግፊት እንድታደርጉ እንጠይቃለን።
በመጨረሻም ይህንን ብሔር እና ኃይማኖትን መሰረት ያደረገ መንግስታዊ ግድያ አዳዲስ ገዳይ ዩኒቶችን በማቋቋም የሚፈፅመው እና የሚያስፈፅመውን የብልፅግና አገዛዝ በማስወገድ ሀገራችንን ከቀውስ እና ከሽብር አገዛዝ እንድናላቅቅ ለመላው ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ጥሪ እናቀርባለን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ
ለመለው አማራ ህዝብ እና ብልፅግናን እየታገላችሁ ያላችሁ መለው ኢትዮጵያዊ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ይሄ አረመኔ ስርአት ብልፅግና አማራ ክልል ላይ ያሰበው ምርጫ በዚህ ልክ ከሽፎበታል ማንኘውም መግስትን የምትቃወሙ ድርጅቶች ፣ሚዲያዎች እና ተፅኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ምርጨው እዳልተካሄደ ለአለም ህዝብ ማሳወቅ አለባችሁ ።
የሽዋ ክፍለሀገር የምርጫ ጣቢያ ብዛት ፣ ያልተካሄደባቸው ፣የተጓጎለበት እና ያስመረጠበት ትክክለኛ መረጃ ስለሆነ ይሄንን መነሻ አድርጋችሁ ሞግቱ ይሄን አረመኔ ስርአት የሰውን ልጅ በግፍ የገደለ ፣ያፈናቀለ ፣የዘረፈ ስለሆነ ከስሩ ነቅለን እደቃጫ ስር ካልጣልነው መቼም አናርፈም ስለሆነም ሁሉም በአቅሙ መታገል አለበት።
ተወደደም ተጠላም ብልፅግና ለማንኘውም ብሄር ስለማይጠቅም መግስት ሆኖ ህዝብ የማስተዳደር አቅምም ልዕልናም የለውም ደም መጣጭ ነው አሁን ሰኔ ወር ደረሰ የቅርቡን ሰው ይገላል ( ይበላል) ስቱን ገደለው ይሄ አረመኔ ስርአት ባለው ቆይታ አማራን ፣አፋርን ፣ኦሮሞን እና ትግሬን ምን ያክል በኢኮኖሚ በማህበራዊ እና ስቱን የሰው ሂወት ቀጠፈው ሌሎች ብሄሮችን ስቱን ገደለው በኑሮ ውድነት ጠበሰው የብልፅግና ክፋት ተዘርዝሮ አያልቅም አንድም መልካም ስራ ነቅሶ ለማውጣት የሚከብድ ስርአት ስለሆነ ሆድ ሲውቅ ዶሮ ማታ ይባላል በፍርፋሪ የምትደለል አሽከሮች ከድርጊታችሁ ተቆጥባችሁ ወደ ትክክለኘው አቋም ጎን ተሰለፍ ላጠፋችሁት ጥፋት ከብልፅግና ጎን ሆናችሁ በየምነታችሁ ይቅር በለን ብላችሁ ከበደላችሁት ህዝባችሁ ጎን ተሰለፉ።
ጀግና ክፉ ቀን አልፎ ደግ ቀን ሲደርስ ነው
ለውነት እየሞትክ ለውሸት የምትኖር ተጠቀቅ
የሽዋ የብልፅግና 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ መረጃ እውነታው ይሄ ነው።
