ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Ir al canal en Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Mostrar más2 936
Suscriptores
+1424 horas
+3877 días
+38530 días
Archivo de publicaciones
ሰበር የድል ዜና 👊👊👊
74ኛ ክ/ጦር የአባይ ሸለቆ ተርቦች ሻለቃ መሪውን ከሙሉ ሀይሉ ጋር በመደምሰስ ዲሽቃ፣ብሬን እና በርካታ የነፍስ ወከፍ መሳሪያወች መማረክ ችለዋል።
===============================
......ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም
ከንጋት11:00 ሰዓት አካባቢ የጀመረው የአባይ ሸለቆ ተርቦች በተጠና እና በተደራጀ መንገድ ሻለቃ አመራሩን እና አባላቱን በመደምሰስ ከቡድን መሳሪያ እስከ ነፍስ ወከፍ መሳሪያ በመማረክ እጅግ ድንቅ ኦፕሬሽን መስራት የተቻለ ሲሆን የወረዳው ጊዚያዊ መንግስት የፀጥታ ሀይል(የገበሬው ጦር) 01ብሬንና በርካታ ክላሽ በመማረክ ታሪክ ተሰርቷል።
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር የአባይ ሸለቆ ተርቦች ዛሬም የብልፅግናውን እንክርዳድ ሰራዊት እንደ አመጣጡ ተገቢውን ቅጣት በመስጠት በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ሰኞ ገበያ ንዑስ ወረዳ እና ዲቦ ንዑስ ወረዳ ዲቦ ከተማ ተከማችቶ በነበረው የሚሊሻና አድማበትን እንዲሁም ፖሊስ ላይ የሸለቆው አዳኞች ጠላት ባልጠበቀው መልኩ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም ሙትና ቁስለኛ ያደረጉት ሲሆን በዚህም ሻለቃ መሪውን ጨምሮ 61አድማ በትን እና 08ፖሊስ ሲደመሰስ 50አለቃ ታደሰ የተባለ የሚሊሻ ሀላፊን ጨምሮ በርካታ ሚሊሻ ወደ ላይኛው የተሸኙ ሲሆን 8 ሚሊሻም ቆስሎ ሆስፒታል ነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ ላይ መሆናቸውን አረጋግጠናል።
➺➺➺➺በዛሬው እለት የተገኙ ምርኮዎች
►ዲሽቃ_01
►ብሬን_02
► ክላሽ_79 ከእስቶር ጭምር የተገኘ
► መገናኛ ሬዲዮ_05
► የድሽቃ ሸንሸል_02
►አስቃጥላ ጥይት_05
►የብሬን እና የክላሽ እንዲሁም የዲሽቃ ጥይት
►fsr መኪና ሙሉ ሎጀስቲኩን ገቢ ተደርጓል።
በዛሬው እለትም የተሰናበቱት ባንዳዎች ውስጥም፦
◍ኢ/ር ወርቁ ------አድማ ሻለቃ አዛዥ
◍ኢ/ር ማሞ....መርማሪ ፓሊስ
◍ኢ/ር አስናቀ...የፓሊስ ሀላፊ
◍ነጋሽ.............ድሽቃ ተኳሽ
◍ ጀማል ኡመር......አድማ ጋንታ መሪ
◍ውዱ...........ፖሊስ
◍ደሴ............-ትራፊክ ፖሊስ ሲሆኑ
➺➺➺➺➺የቆሰሉት ደግሞ
👉ወንዱ ይፍሩህ
👉 ዩሀንስ ጎበዜ
👉 የሹ ይዘዘው
👉 አስማረ ተስፋው የተባሉ ሲሆኑ ከዚህ ትምህርት በመውሰድ ሌሎቻቹህ አሁንም ወደ ትክክለኛ ማንነታቹህ እንድትመለሱ ጥሪያችን እያቀረብንላቹህ ሲሆን አብይ አህመድ ባዘጋጀው የሞት ድግስ ውስጥ እየገባችሁ የምትማገዱ የብልፅግና ዙፋን አስጠባቂወች ይቅርባቹህ እያልን የአማራ ፋኖ ድርጅታችን ይቅር ባይ ነውና በይቅርታ ወደ ቤተሰባችሁ ተቀላቀሉ።
ተወደደም ተጠላም መሸሻ የላቹህም መዳኛቹህ ወደ ትክክለኛ ማንነታቹህ ወደ ህዝባቹህ ተመለሱ እራሳቹህን ታድኑ ዘንድ ጥሪያችን እናስተላልፋለን።
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የበላይ ዕዝ፦ በእሳት የተፈተኑ የጽናት እና የድል አበጋዞች!
የጎንደር ተራሮችና ገደላማ ሸንተረሮች የጀግኖችን እግር ያውቃሉ። ደጋውና ቁልቁለቱ፣ ቁሩና እሳቱ ሳይበግራቸው፣ በእሳት እቶን ውስጥ አልፈው እንደ ወርቅ ተፈትነው የወጡት የጎንደር ጀግና ልጆች የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ዛሬም የታሪካቸውን ገጽ በወርቃማ ቀለም እያደሱ ይገኛሉ። የአሸናፊነትን ምስጢር ተላብሰው፣ የጽናትን ትጥቅ ታጥቀው፣ አንድነታቸውን እንደ ብረት አጠናክረው ወደ ተስፋዋ ማለዳ እየገሰገሱ ነው።
በውስጥ ደግሞ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይበቀል የሚለው የጠባብነትና የከንቱ ሥልጣን ጥም ታሪክ ይዞት የሚያልፍ አቧራ እንጂ በእነሱ ዘንድ ስፍራ የለውም። የየለቱ እርምጃቸውና የትግላቸው መርህ አንድና ግልጽ ነው፦ እኛ እግራችን የተተከለው፣ ደማችን የሚፈሰውና የምንታገለው የአማራን ህዝብ ከቀንበር አውጥተን ነፃ ለማውጣት እንጂ፣ በከንቱ ለሥልጣን ወንበርና ለጊዜያዊ አክሊል አይደለም!
ዛሬ በሀገር ውስጥ በጽናት የሚኖሩትም ሆኑ፣ በመላው ዓለም ማዕዘናት የሚገኙት የህዝብ ልጆች፣ የበላይ ዕዝ በቅርቡ ባሳየው የውጊያ ጥበብ፣ የማይናወጥ ዲሲፕሊን እና የብረት ያህል ጠንካራ የአንድነት ግድግዳ ልባቸው በኩራት ተሞልቷል! ይህ ጥንካሬ የጨለማው ዘመን ማክተሚያና የአዲሱ ማለዳ ብርሃን ማብሰሪያ መሆኑን አምነዋል። በሰማዕታት ስም የታሰረ የማይበጠስ ቃል ኪዳን! በየትኛውም የዓለም ማዕዘን የምንገኝ የሀገር ልጆች፣ ስለ ህዝባቸው ነፃነት ደማቸውን አፍስሰው ለወደቁት ሰማዕቶቻችን ቃል እንገባለን። ሕዝባችን ሙሉ በሙሉ ነፃነቱን ተቀዳጅቶ፣ በክብርና በሰላም እስካልተወጣ ድረስ ትግላችንን ለአንድ ሰከንድ እንኳ አናቆምም፤ ወደ ኋላም አንልም! አንድነታችን የማይበገር ምሽጋችን ነው! አንድነታችን የማሸነፋችንና የነፃነታችን ብቸኛው ታላቅ ምልክት ነው!
ድል ለአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ!
ቴወድሮስ እዝ 201ኛ ኮር፣ 74 ኛ ክፍለ ጦር ዓባይ ሸለቆ ሻለቃ አስደናቂ ጀብዱ ፈፅማለች።
ዛሬ በቀን 22/11/2018 ዓ.ም ንጋት11:00 ሰዓት አካባቢ የአባይ ሸለቆ ተርቦች ሻለቃ መሪውን ከሙሉ ሀይሉ ጋር በመደምሰስ ዲሽቃ፣ ብሬንና በርካታ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ በመማረክ እጅግ ድንቅ ስራ ሰርተዋል። በዚህ የአፋብን የወረዳው ጊዜያዊ መንግስት የፀጥታ ሀይልም ጭምር በተሳተፈበት ድንቅ ኦፕሬሽን በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ሰኞ ገበያ ንዑስ ወረዳ እና ዲቦ ንዑስ ወረዳ ዲቦ ከተማ ተከማችቶ በነበረው የሚሊሻና አድማ በትን እንዲሁም ፖሊስ ላይ የሸለቆው አዳኞች ባልጠበቀው መልኩ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።
በዚህም ሻለቃ መሪውን ጨምሮ 61አድማ ብተና ኃይል፣ 08 ፖሊሶች ሲገደሉ 50 አለቃ ታደሰ የተባለ የሚሊሻ ሀላፊን ጨምሮ በርካታ ሚሊሻ ወደ ላይኛው ተሸኝቷል። 08 ሚሊሻም ቆስሎ ሆስፒታል ገብቷል።
👉በኦፕሬሽኑ የተገኙ ምርኮዎች:-
1) አንድ ዲሽቃ
2) ሁለት ብሬን
3) 79 ክላሽ
4) 05 መገናኛ ሬዲዮ
5) 02 የድሽቃ ሸንሸል
6) 05 ሳጥን የዲሽቃ ተተኳሽ
7) በርካታ የብሬንና የክላሽ
8) አንድ FSR መኪና ሙሉ ሎጀስቲክ እንደጫነ
ከተገደሉት መካከል:-
• ኢ/ር አስናቀ የፖሊስ ፅ/ቤት ኃላፊ፣
• ኢ/ር ወርቁ ------አድማ ብተና ሻለቃ አዛዥ፣
• ነጋሽ-----ድሽቃ ተኳሽ
• ጀማል ኡመር ----አድማ ብተና ጋንታ መሪ
• ኢንስፔክተር ውዱ -------የፖሊስ አመራር
• ኢንስፔክተር ማሞ ----የፖሊስ አመራር ይገኙበታል።
ይቀጥላል...
ይህ ከመከላከያ አባል እንደወርደ በውስጥ የደረስኝ ቴክስት ነው!!!
ሰላም ወንድሜ #Dave #Amhara እኛ ደህና ነን፤ አንተ እንዴት ነህ? አሁን የምልክልህ ቪዲዮ የመጨረሻ የህይወት ምስክርነቴ ሊሆን ይችላል... ነገር ግን ይህ መልዕክት ለመላው የመከላከያ አባል እንዲደርስልኝ አጥብቄ እፈልጋለሁ። እኔ የመከላከያ ሰራዊት አባል ነኝ።በቅርቡ ከሰሜን ዕዝ ከኮሎኔል መሐመድ ተሰማ ጋር ወደ ጎጃም ምድር ከገቡት ወታደሮች አንዱ ነኝ። እውነቱን ለመናገር አሁን ያለው መከላከያ በከፍተኛ ጭንቅ፣ በጥበት እና በውታረ ግራ መጋባት ውስጥ ነው የሚገኘው!
ከፋኖ ጋር መዋጋት እጅግ በጣም ከባድ ሆኖብናል። ከየት በኩል መጥተው እንደሚመቱን፣ እንዴት እንደሚያጠቁን እንኳን ማወቅ አንችልም። አጠገባችን ያለው ጓደኛችን በጥይት ተመቶ ሲወድቅ ብቻ ነው የምናየው... ስርዓቱ እና አሰራሩ በሙሉ ፈርሷል!
እኛም በቅርቡ ከዚህ ስርዓት እንወጣለን! ለመሆኑ ለማንስ ብለን ነው የምንዋጋው?! ለምንስ ብለን ነው ለአንድ ሰው ወንበር ማስጠበቂያ ህይወታችንን የምንገብረው?! የነሱ ልጆች በአሜሪካ እና በአውሮፓ እየተማሩ፣ በደስታ እና በሰላም እየኖሩ... እኛ ማናችን እና ነው ውድ ነፍሳችንን በእጃችን አስይዘን የምንዋጋው? #Dave #Amhara ... ሁሌም ስለ አንድነት የምትፅፈው ጽሑፍ እጅግ የሚያበበረታ እና የልብ ድፍረት የሚሰጥ ነው። በርታ! እኛም ወደ ወንድሞቻችን ወደ አማራ ልጅ ፋኖዎች እንቀላቀላለን!
ሆኖም ስሜን መግለጽ አልፈልግም። ነገር ግን ይህ መልዕክት በስርዓቱ ውስጥ ላሉት የመከላከያ አባላት ይድረስ! ሚሊሻውም ሆነ አድማ መከላከል ይሄን ይወቁ የውሻ ሞት ነው እየሞቱ ያሉት!
የሚገርምህ ዘመነ ካሴ በተናገረ ቁጥር በመከላከያ እና በስርዓቱ ውስጥ ያለው ጭንቀትና ፍርሃት ወሰን የለውም። አይዞአችሁ ከእናንተ ጋር ለመዋጋት የሚፈልግ አንድም የመከላከያ አባል አይኖርም። ከዚህ ስርዓት ወጥተን እስክንገናኝ ሰላም ሁን... ካልተገናኘንም በሰላም ቆይ። በአቋምህ ፅና, #Dave #Amhara ይህ የገለጽነው መልዕክት የሚያይ መከላከያ በሰራዊቱ ውስጥ ያለውን ጥልቅ እውነት እና የውስጥ ስሜት የሚያሳይ ነው። በየቀኑ በውጊያ መስመር የሚወድቁ ወጣቶች ህይወት እና የሰራዊቱ ጥያቄ አሁንም ምላሽ ይፈልጋል።
ይህ ድምፅ ለሁሉም እንዲደርስ እና እውነቱ እንዲታወቅ ቪዲዮውን LIKE፣ SHARE እና SUBSCRIBE በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ አድረግልኝ። ሰላም እና አንድነት ለህዝባችን ይሁን! ስሜን መግለፅ የማልፈልግ የመከላከያ አባል ነኝ!! እኔም አመስግናለሁ ኑልን ብያለሁ
+1
የብልፅግና ጀነራሎች የሰበሰቡት እግረኛ በመድፍ፣ በሮኬት፣ በድሮን ታጅቦ ወደ አራት አቅጣጫ ያለ ዒላማ ያለ ውጊያ እየተኮሰ የአርሶ አደር መንደሮችን እየደበደበ ጮቄን መርገጡን እንደተዓምር ሲያወሩት እያዬን ፈገግ እንላለን።
የማረኩት መሳሪያ የለም፣ የማረኩት ሰራዊት የለም፣ የደመሰሱት አሃድ የለም። በቃ ከደጋ ቆላ መንገላታታቸውን እንደ ድል እያከበሩት ነው። በአንዱ ጥግ ዞረው ሲያልፉ በሌላኛው የጮቄ ጥግ ደግሞ ልክ እንደ መዝገቡ፣ ልክ እንደ መንበሩ ኮሎኔሎቻቸውን ከነ ማዕረጋቸው ጨብጦ የሚያሳይ ኃይል እያስመረቅን ነው።
እነኝህ ከቀናት በኋላ ከጠላት ማርከው እንዲታጠቁ የተዘዘጋጁ፤ በትላንትናው ዕለት የተመረቁት የ201ኛ ኮር፣ 54ኛ ክፍለ ጦር የሰራዊት አባላት ናቸው።
አርበኛ አስረስ ማረ
የአፋብን የህ/ግ/መምሪያ
ድል እንደ ሰማይ የራቀው የአገዛዙ ዙፋን አስጠባቂ የግል ሰራዊት አመራሮች የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ሲጋለጥ!
ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም
" 'ድል ማለት' ፕሮፓጋንዳ ሲደመር መረጃ ነው" ብሎ የሚያስተምረውን የአባታቸውን አንባገነን አማራ ጠሉ የአብይ አህመድን አስተምሮ ይዞ ወደ ጀግኖቹ መንደር በሸዋ ቀጠና ግንባር የገባው የብልፅግናው 103ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር እንደ ሰማይ የራቀውን ድል በሐሰተኛ ፕሮፓጋንዳ ለመቀልበስ መሞከሩን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አጋልጧል።
በአገዛዙ አየር ወለድና ኮማንዶ ክፍለ ጦር እጅግ የሚፈራው የአፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነውን ጀግናው የራንቦ ክፍለ ጦር አባላትና አመራሮችን ስርዓቱ በሚዲያ ሚሊሾቹ አማካኝነት ደምስሼ ፣ ከፍተኛ የዕዝ አመራር አቁስያለሁ ማለቱን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ፍፅም ሀሰት መሆኑንና እርምጃ ተወሰደባቸው የተባሉ አመራሮችም በሙሉ ጤንነት በመደበኛ የስምሪት ስራቸው ላይ መሆናቸውን ኮሩ ባደረገላቸው ቃለ መጠይቅ አረጋግጧል።
በአመሻሽ ዕድሜው ላይ የሚገኘው የጦር ወንጀለኛው የብልፅግና አገዛዝ በአውደ ውጊያ የራቀውን ድል በፕሮፓጋንዳ ለማካካስ ቀን ከሌት እየሰራ መሆኑን መላው የፋኖ ሰራዊታችንና ህዝባችን እውነቱን ተረድቶ ከመሰል አሳሳች መረጃዎች እራሱን እንዲቆጥብ ኮሩ ማሳሰብ ይወዳል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል
+1
ወታደራዊ መስመር ማዕረግተኞች መገናኛ ራድዮንና ጥቁር ክላሽ በመያዝ አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የ106ኛ ኮር 34ኛ ክፍለጦርን ተቀላቀሉ!!!
በማንኛውም ቀጠና የአገዛዙ ሰራዊት በየሰከንዶቹ ሽርፍራፊ እየፈራረሰ መገኘቱን የተረዱ የጠላት ወታደሮች ከአገዛዙ ጭቆና እራሳቸውን ነፃ በማውጣት የ106ኛ ኮር 34ኛ ክፍሀጦርን ተቀላቅለዋል። የፋኖን ጫና እና የማጥቃት እርምጃ መቋቋም የተሳነው አገዛዙ ከምርኮኛ በአሻገር ከማዕከላቸው እየፈረሱ ወደ ፋኖ የሚቀላቀሉ የአገዛዙ ሰራዊት አባላቶች ዛሬም ወደ ፋኖ የትግል መስመር እያቀኑ ይገኛሉ!!
የመስመር መኮንን ማዕረግተኛ የሆኑት የቀድሞቹ የአገዛዙ ሰራዊት ወደ ፋኖ ሲቀላቀሉ የ34ኛ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን፡የአገዛዙን ወቅታዊ የመፈራረስና የመንኮትኮት መዋቅራዊ ሁኔታ ተረድተው ሌሎች ወታደሮች ህይዎታቸውን እንድያተርፉ መልክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን አገዛዙ የሲዖል አፋፍ ላይ መድረሱን ጠቁመዋል ሲል የ106ኛ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ መረጃውን አድርሷል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
ሀምሌ 22/2018 ዓ/ም
በታሪክ ውስጥ አንዳንድ አጋጣሚዎች ይመጣሉ፤ ብዙዎች ሁኔታዎችን በዝምታና በፍርሃት በሚታዘቡበት፣ ማንም በየሰፈሩ መደራጀትና እጁን ማንሳት ባልደፈረበት በዚያ ፈታኝ ወቅት ነበር የነፃነት ጥሪ የታሰበው።
የአማራ ልጅ ፋኖ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ! የዛሬ ስምንት ዓመት፣ መንገዱ በስጋትና በችግር በተከበበበት ቅጽበት፣ ቁርጠኝነቱን በመያዝ እስከ ጎንደር መተማ ድረስ ዘለቀ።
እዚያ በርሃ ላይ ከጀግኖቹ ወንድሞቹ ጋር በመቀላቀል፣ በአራቱም ማዕዘን ለተበተኑትና ዛሬ ድምፃቸው ተחנוቆ ለማይሰማው በርካታ የአማራ ልጆች መከታና ድምፅ በመሆን ሸዋን ወከለ።
ይህ ታሪካዊ ጉዞና ውሳኔ፣ የአማራ የመኖርና የነፃነት ህልውና እንዲረጋገጥ ከተደረጉት የትግል ምዕራፎች መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን፣ አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ በዚያ ታሪክ ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ በመውሰድ ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል።"
"ዛሬም ቢሆን ያ የፅናትና የጀግንነት ጉዞ አልቆመም። የትግሉ መሪ፣ የነፃነት አርማና የአማራ ልጅ ፋኖ ድምቀት ከሆኑት ውስጥ አንዱ የሆነው አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ በርታልን! Dave Amhara
ትላንት ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀነራል ብርሃኑ ጥላሁን ጮቄ ላይ ባደረግነው ዘመቻ በአካባቢው የሚንቀሳቀሰዉን የፋኖ ኃይል ሽፍታ አድርገነዋል ሲል ደነፋ።
ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም አነጋግ ላይ ደግሞ የቴወድሮስ እዝ 201ኛ ኮር፣ 74ኛ ክፍለ ጦር ዓባይ ሸለቆ ሻለቃ ድል ተቀዳጅታለች።
ዲሽቃ ከነ ሙሉ ተተኳሹ ተማርኳል።
ብሬን እና በርካታ የነፍስ ወከፍ መሳሪያወች ከብዙ ወታደራዊ ቁሳቁስ ጋር ገቢ ተደርጓል።
እኛ እነሱ እንዲህ ነን እኛም እናዝረከርካቸዋለን፤ እነሱም እስከመጨረሻዋ ህቅታቸው መዋሸታቸው አይቀርም። አስርስ ማር
የነፃነት ነበልባል ከአንኮበር ተራሮች፦ የደጃዝማች አበባየሁ እና የደጃዝማች አየለ ብርጌዶች ታሪካዊ የምርቃት ስነ-ስርዓት በታላቅ የትግል ወኔ ተከበረ!!
ሀምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም
የህዝብን መራር ብሶት ወደ አልበገሬነት የትግል ወኔ የለወጠው የፋኖ የነፃነት እሳት፣ ታሪካዊቷና የቆራጥ አባቶች ምድር በሆነችው በአንኮበር ተራሮች ላይ በደማቅ ሁኔታ እንደገና ተቀጣጥሏል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚንቀሳቀሱት ሁለቱ የትግል አምዶች ማለትም ደጃዝማች አበባየሁ ብርጌድ እና ደጃዝማች አየለ ብርጌድ በተደረገላቸው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠና እና የትግል ዝግጅት ታላቅ የምርቃት በዓላቸውን በስኬት አጠናቀዋል።
ይህ በደማቅ የታጠቁ አርበኞች ህብረ ዝማሬና ድምቀት የታጀበው ታሪካዊ መርሃ-ግብር፤ የህዝብን ደህንነትና መብት ለማስከበር በሚደረገው የትጥቅ ትግል ውስጥ ወኔ ቀስቃሽነትን ያበሰረ ሆኗል።
በዝግጅቱ ላይ የትግሉን ፖለቲካዊና ወታደራዊ አቅጣጫን ያስቀመጡ የድርጅት፣ የዕዝ፣ የኮርና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን፣ የትግሉ ጠንካራ መሠረት የሆኑት የአገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በመገኘት ለሰራዊቱ ምርቃታቸውን እና አጋርነታቸውን ሰጥተዋል።
በወቅቱ ከፍተኛ አመራሮች ባደረጉት ቀስቃሽና ማጠቃለያ ንግግር፦ ወቅታዊ ሁኔታና የትግሉ ደረጃ፦ የአሁኑ የትግል ምዕራፍ በጽናትና በጥራት የሚመራበት መድረክ ላይ መድረሱ ተብራርቷል።
የአርበኞች ጦር አደረጃጀት፦ የወታደራዊ አደረጃጀቱና የትግል ስልቱ ከጊዜው ጋር በተጣጣመ መልኩ ይበልጥ የተቀናጀና ዘመናዊ እየሆነ መምጣቱ ተገልጿል። የቀጣይ አቅጣጫ፦ የህዝብን ነፃነት ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ የሚደረገው ፍልሚያ ባልተናወጠ ወኔና ቁርጠኝነት እንደሚቀጥል ጥብቅ የትግል አቅጣጫ ተሰጥቷል።
በትግሉ ግንባር ቀደም ሆነው ላገለገሉ፣ ሰራዊቱን ላደራጁና የህዝቡን ደጋፊነት አስተባብረው በቁርጠኝነት ህዝባቸውን ላገለገሉ አርበኞች የሞራልና የትግል ማበረታቻ ስጦታዎች ተበርክተዋል። በዚሁ መሠረት፦
✔ለክላስተር መሪዎች፣
✔ለብርጌድ መሪዎች፣ እና
✔ለቀበሌ አመራሮች፣
የጀግንነት ምልክት የሆነውን የአርበኞች ምስል እና የፅናት ምስክር የሆነው የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል። ይህ ከአንኮበር ተራሮች የተሰማው የምርቃት ብስራትና የደስታ አየር፣ በትጥቅ ትግሉ ጉዞ ላይ አዲስ ጉልበትና ወታደራዊ ግርማ የፈጠረ ሲሆን፤ ጥሪያቸውን አድሰው የተመረቁት ብርጌዶችም የተሰጣቸውን ህዝባዊ አደራ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
"አንድነታችን የህልውናችን መሰረት ነው!"
የተከበራችሁ የኮር እና የክፍለ ጦሩ አዛዦች፣ ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች፣ እና ከሁሉ በላይ ለወራት ሲሰጣችሁ የቆየውን አስቸጋሪ ስልጠና አጠናቅቃችሁ ዛሬ ለምረቃ የበቃችሁ የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ የ201ኛ ኮር፣ የ54ኛ ክፍለ ጦር ተመራቂ አባላት፤
እንኳን ለዚህ ታላቅ እና የክብር ቀን አበቃችሁ!
ላፉት በርካታ ወራት በየቀኑ በነበረው ጠንካራ አካላዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና ታክቲካዊ ስልጠና ውስጥ አልፋችኋል። ፈተናዎችን ታግሳችሁ፣ ብርዱንና ሐሩሩን ችላችሁ፣ ድካምን አሸንፋችሁ ዛሬ በዚህ የቆማችሁበት ደረጃ ላይ መድረሳችሁ የጽናታችሁ እና ለድርጅታችን ያላችሁ ታማኝነት ማረጋገጫ ነው። ዛሬ የምታደርጉት ይህ የምረቃ ስነ-ስርዓት የስልጠና ማብቂያ ብቻ ሳይሆን፣ የተጣለባችሁን ታላቅ ኃላፊነት የመረከቢያችሁ መነሻ ነው።
ዛሬ ወደ አዲሱ ግዴታችሁ ስትሰማሩ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች በልባችሁ እንድትይዙ አጥብቄ አሳስባችኋለሁ።
1. ወታደራዊ ጥንካሬ መሰረቱ መሳርያ ወይም ቁጥር ሳይሆን ዲሲፕሊን ነው። በስልጠና ወቅት ያገኛችሁትን ወታደራዊ ስነ-ምግባር፣ የታዛዥነት እና የትእዛዝ ሰንሰለትን የማክበር ባህል በስራ ቦታችሁ ሁሉ ተግባራዊ ማድረግ አለባችሁ። ያለ ዲሲፕሊን የሚገኝ ድል የለም።
2. በ54ኛ ክፍለ ጦር ስር በነበራችሁ ቆይታ አንዱ ለሌላው የደገፈበትን እና የተረዳዳበትን መንፈስ አዳብራችኋል። ይህ አብሮነት እና የወንድማማችነት ገመድ በተግባራዊ ስራችሁም ሊጠነክር ይገባል። በውጊያም ሆነ በመደበኛ አገልግሎት ስኬታችሁ የሚያዝዘው በጋራ ጥረታችሁ እና በአንድነታችሁ ላይ ነው።
3. እናንተ የዚህ ድርጅት ጋሻ እና መከታ ናችሁ። የተጣለባችሁን ተልዕኮ በብቃት የመወጣት፣ ድርጅቱን እና የሚወክለውን ዓላማ የማስከበር ታላቅ አደራ አለባችሁ። በየትኛውም ቦታ እና ሁኔታ ውስጥ ብትሆኑ የታማኝነት እና የቁርጠኝነት ምሳሌ ልትሆኑ ይገባል።
4. ስልጠናው ዛሬቢያበቃም፣ ትምህርት ግን አያበቃም። የአካል እና የብቃት ዝግጁነታችሁን በየቀኑ ማሳደግ፣ አዳዲስ አሰራሮችን ማወቅ እና ወታደራዊ ክህሎታችሁን ሁልጊዜ ዝግጁ ማድረግ ይጠበቅባችኋል።
በመጨረሻም:-
የማንኛውም ጠንካራ ተቋም፣ ህዝባዊ ትግል እና አላማ አሸናፊነት የሚወሰነው በአባላቱ ወጥ የሆነ አንድነት፣ እውነተኛ ወንድማማችነት እና በወል አላማው ላይ ባለው ቁርጠኝነት ላይ ነው። በአሁኑ ወቅት በአደረጃጀታችን ውስጥ መጠራጣርን፣ ክፍፍልን እና የውስጥ ልዩነትን ለመፍጠር የሚደረጉ ጥረቶች ተቋሙን ከማዳከም ባለፈ ለቆምንለት ታላቅ አላማ ትልቅ እንቅፋት ናቸው።
ስለሆነም ይህንን አፍራሽ መንገድ ለምትከተሉ አካላት የሚከተሉትን ነጥቦች በግልጽ ማሳወቅ እወዳለሁ፦
• በውስጣችን የሚፈጠር ማንኛውም መጠራጣር እና መጠላለፍ የሚጠቅመው የታገላቸውን ጠላቶች ብቻ ነው። አላማችንን እና ህዝባችንን ከውጭ ከሚመጣ ፈተና በላይ የሚጎዳው የውስጥ ክፍፍል መሆኑን ልትገነዘቡ ይገባል።
• በማንኛውም ድርጅት ውስጥ የአስተሳሰብ ወይም የአሰራር ልዩነቶች ሊኖሩ ይችላሉ። ነገር ግን እነዚህን ልዩነቶች በተቋማዊ ህግ፣ በግልጽ ውይይት እና በወንድማማችነት መንፈስ ከመፍታት ይልቅ ከጀርባ መጠማመድና ሰዎችን በከፊል-በከፊል መክፈል የወታደራዊና ድርጅታዊ ስነ-ምግባር ውድቀት ነው።
• ይህ ተቋም የተገነባው በብዙዎች መስዋዕትነት፣ ጽናት እና በህዝብ ተስፋ ላይ ነው። አደረጃጀቱን ለግል ወይም ለቡድን ስሜት ሲባል ለመከፋፈል መሞከር የሰማዕታቱን ደም እና የህዝቡን አደራ እንደመካድ ይቆጠራል።
• ተቋሙ የውስጥ አንድነቱን፣ ዲሲፕሊኑን እና የትእዛዝ ሰንሰለቱን ለማስከበር ምንም አይነት ድርድር አያደርግም። ክፍፍልን እና ሀሰተኛ ወሬዎችን የሚያሰራጩ፣ አባላትን እርስ በርስ የሚያጋጩ እና ስርዓት አልበኝነትን የሚያስፋፉ አካላት ከዚህ ድርጊታቸው ባልተቆጠቡ አሰራሩ በሚፈቅደው መመሪያ መሰረት ተጠያቂ ይሆናሉ።
• ማህበራዊ ሚድያ ላይ እየተፈጠረ ያለው ጎራ የለየ መነታረክ እና ብሽሽቅ እንደሚባለው በቀጣሪና በተቀጣሪ የተፈጠረ ሆኖ ሳይሆን የራስን የግል ስሜት በሌሎች ላይ ለመትፋት የሚደረግ የጠላትነት አደገኛ አዠንዳ ነው። በዚህ ትግል ውስጥ እያለፍን ያለን አመራሮችም ሆነ አባላት በሙገሳ የምንረካ በስድብ የምንኮሰምን ፍጥረቶች አይደለንም። እንደግል ማንም እንዲያሞግሰኝ ፍላጎትም ምኞትም የለኝም። ይሄ በክፉም በጥሩም የሚነሳ ስም የክቲቪስት አድቨርት የሚያስፈልገው አይደለም። ስድብም፣ ሀሜትም፣ ፕሮፖጋንዳም የሚያሸማቅቀኝ ድንጉጥ ሰውም አይደለሁም።
• ከዚህ በፊት የነበሩ በዕዛችን ውስጥ የተስተዋሉ የትግላችንን እና የቀጠናውን ገፅታ ያበላሹ አላስፈላጊ ንትርኮች እንዲቆሙ ከሌሎች ጎዶች ጋር በመሆን እታገላለሁ።
• ከዚህ በኋላ እኔን ደግፎ ሌለኛውን የሚነቅፍ በደጋፊ ስም የተደበቀ ጥቁር ጠላት ሃላፊነቱን ራሱ እና ራሱ የሚወስድ ይሆናል። ከዚህ በፊትም ቢሆን ማንም በማንም ላይ እንዲዘምት የሰጠሁት ፈቃድም ሆነ ይሉኝታ በፍፁም ያልነበረ መሆኑን የተከበረው ህዝብ እና ድርጅቱ እንዲያውቀው እፈልጋለሁ። በትግል ውስጥ ችግር ይኖራል፣ ይፈጠራል፣ በህግና በአሰራር እናርማለን። ማንኛውም የድርጅታችን አባላትና አመራር ከህዝብ እና ከድርጅት በታች መሆኑን እንዲያምንበት ይደረጋል።
• የግዙፉን የቴዎድሮስን ዕዝ ለመምራት የተመደባችሁ አመራሮች መልካም የትግል ጊዜ እንዲሆንላችሁ እየተመኘሁ ይህን ትግል መምራት ክብርንም ስምንም የሚያወርድ የመጥፎ ምላሰኞችን የእሳት ወላፈን መቋቋምን የሚጠይቅ በእጅጉ መረጋጋትን እና መፅናትን የሚፈልግ ተግዳሮት የበዛበት ስለሆነ ከወዲሁ የስነ ልቦና ትጥቅ እንድታስሩ እመክራለሁ።
ዛሬ ከማንኛውም ጊዜ በላይ አንድነታችን፣ ብረት የመሰለው ዲሲፕሊናችን እና ለታላቁ አላማችን ያለን ታማኝነት የሚፈተንበት ወቅት ነው። በመሆኑም በግልጽም ሆነ በስውር ልዩነት ለመፍጠር የምትሰሩ አካላት ከዚህ አጥፊ መንገድታችሁ ተመልሳችሁ፣ ጊዜያችሁን እና እውቀታችሁን ተቋሙን ለማጠናከር እና አንድነታችንን ለማስጠበቅ እንድታውሉ እመክራለሁ።
" ከልክ ያለፈ የስልጣን ፍላጎት፡ ከልክ ያለፈ የገንዘብ ፍቅር ልብስ ያስጥላል"
የአፋብን ሊቀመንበር አርበኛ ዘመነ ካሴ
የጋራ አላማችን የሚያሸንፈው በጥበብ፣ በጽናት እና በአንድነታችን ብቻ ነው! እንፅና !!!
አሳዛኝ ዜና !
በምስራቅ ጎጃም አነደድ ወረዳ ከምሽቱ 12:15 በተከታታይ በተፈፀመ የመድፍ ጥቃት ወ/ሮ እቴኔሽ ደምል የተባለች ነፍሰጡር እናት ሕይወቷን አጣለች።
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
==================================
ከምሽቱ 12:15 ገደማ በአነደድ ወረዳ ጨንደፎ ቀበሌ በንፁሐን መንደሮች ላይ በተፈፀመ የመድፍ ጥቃት ወ/ሮ እቴነሽ ደምል የተባለችው ነፍሰጡር እናት ህይወቷን ስታጣ የቤት እንስሳት ተገድለዋል መኗሪያ ቤቶች ወድመዋል።
በደብረ ማርቆስ ከተማ የምስራቅ ጎጃም ካድሬዎችን ሰብስቦ "ፋኖን ሽፍታ አድርጊዋለሁ "ሲል የዋለው ሜጄር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን የንፁሐን መንደር በመድፍ ሲያወድም ውሏል። አገዛዙ በህዝብ ላይ በከፈተው የሜካናይዝድ ጥቃት በ ረቡዕ ገበያ፣ ሰዴ፣ ሁለት እጁ እነሴ፣ ጎንቻ ሲሶ እነሴ እና እናርጅ እናውጋ ወረዳዎች በዛሬው ዕለት ብቻ በ6ኛ ዕዝ 35 የመድፍ ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
