es
Feedback
እፎይ እና ጰላድዮስ እውነት አላቸው

እፎይ እና ጰላድዮስ እውነት አላቸው

Ir al canal en Telegram
5 467
Suscriptores
+224 horas
-117 días
-8030 días
Archivo de publicaciones
Repost from እፎይ
እጅግ ያስደነቀኝን ዘመኑን የዋጀ አንድ የወንድማችን ጰላዲዮስ palladius bible study የተሰኘ አፕልኬሽን ላስተዋውቃችሁ በውስጡ እያንዳንዷን መፅሀፍ ቅዱስ ጥቅስ ከነትርጓሜው አባቶች ምን ብ
እጅግ ያስደነቀኝን ዘመኑን የዋጀ አንድ የወንድማችን ጰላዲዮስ palladius bible study የተሰኘ አፕልኬሽን ላስተዋውቃችሁ በውስጡ እያንዳንዷን መፅሀፍ ቅዱስ ጥቅስ ከነትርጓሜው አባቶች ምን ብለው ፈቱት የሚለውን ጭምር 5ቱን የቤተክርስትያን ትርጓሜ የያዘ በተጨማሪ መፅሀፈ ቅዳሴ ስንክሳርና እና መሰል በተለይ ንፅፅር ለሚሰሩ ልጆች እንዲሁም ለአዲስ ክርስትያኖች መፅሀፍ ቅዱስ ግር እንዳይሰኛቸው እያንዳንዷን ጥቅስ ከነ ትርጉሙ የሚያሳይ በ5 ቋንቋዎች ማለትም ግእዝ አማርኛ ትግርኛና በአፍን ኦሮሞ እንዲሁም በእንግሊዘኛ የተዘጋጀ እጅግ የሚደንቅ አፕልኬሽን ሰርቷል የምትፈልጉ @palladiusofficial ላይ ማናገር ትችላላችሁ በተጨማሪም ላይ ታገኛላችሁ አበረታቱት ዘመን ማይሽረውን የፅድቅ ስራ ነው የሰራው እጅግ ስለገረመኝ ነው ያጋራዋችሁ በዚ ልክ የተሰራ አፕልኬሽን ስለሌለ

የማስረጃ ያለኽ…😁 ተከሳሽ እንዲኽ ሲለምን አይታችኹ ታውቃላችኹ?😭😂 ወይ ተአምር እንደውኮ!

እሺ ሌቦቹ ተገኝተዋል… 1.Viki 2.Palladius 3.Dave እሺ ሸጋዳ ወንድማችን እነዚኽ ሦስት ሰዎች በአደባባይ ሌቦች ብለኽ እንደ ከሠስካች በአደባባይ ሌብነታችን የሚያጋልጥ ጠንካራ ማስረጃ ላ
እሺ ሌቦቹ ተገኝተዋል… 1.Viki 2.Palladius 3.Dave እሺ ሸጋዳ ወንድማችን እነዚኽ ሦስት ሰዎች በአደባባይ ሌቦች ብለኽ እንደ ከሠስካች በአደባባይ ሌብነታችን የሚያጋልጥ ጠንካራ ማስረጃ ላክልን! ቃሌ ነው እነዚኽን ሦስት ሰዎች ሌቦች ብለኽ የምትልክልን እውነተኛ እና ጠንካራ ማሥረጃኽን ለሕዝብ በተለያዩ channeሎች እና የMas media ገጾች እንዲለቀቅ በማደረግ ሌበነታቸውን አጋልጣለኹ! ክርስቲያኖች እንዲኽ ዓይነት ክሦች ሲመጡ ወንድሞችን ስለሚያጠነክሩ በእርጋታ ተከታተሉ እንጅ አትናወጡ!🙏

ፈተናችንኮ በዛ ወገን…ትላንት ማሕበር ለመኾን ዕቅድ ይዘናል ማለታችንን ተከትሎ በውስጥ እንዲኽ ዓይነት መልእክት ደረሰን! ለጠቅላላ መረጃ ያክል ማሕበር እንኹን የሚለውን ሐሳብ ያፈለቀው ወንድም “ጓ”
+1
ፈተናችንኮ በዛ ወገን…ትላንት ማሕበር ለመኾን ዕቅድ ይዘናል ማለታችንን ተከትሎ በውስጥ እንዲኽ ዓይነት መልእክት ደረሰን! ለጠቅላላ መረጃ ያክል ማሕበር እንኹን የሚለውን ሐሳብ ያፈለቀው ወንድም “ጓ” ነው! ከዚኽ ባሻገር ግን ሥራ ለመሥራት አንድ እርምጃ በተንቀሳቀስን ቁጥር የኛው ልጆች ክርስቲያኖች ፈተና ይኾኑብናል። ከዚኽ ቀደምም ዓረብ አገር ከሚሠሩ ሴቶች ብር ዘርፈዋል ብዙ ሴቶችን ጎደተዋል ተብሎ እዚኹ ግሩፕ ላይ ክስ ያለው እንዲከሰን ሜዳ እንሰጣዋለን ምንም የምነዘጋበት በርም የለም በይፋ የደረሰበትን ለሕዝብ መናገር ይችላል ብለን ነበር ግን ከሳሹ አልተገኘም። አኹንም ማሕበር እንኹን ማለታችንን ተከትሎ ማሕብር የሚለው ቃል በ መዝገበ ቃል የሰዋስው ግስ ሕግ መሠረት የኔ ነው የሚለን ሰው ያለ ይመስላል!😁 ተመሳሳይ መልእክት ለኹላችንም እየደረሰን ነበር…ስንት ዓይነት ሰው አለ በሥላሴ! ለማንኛውም ልባችኹ ክፋት : ተንኮል : ርኩሰት እና መሰል ሐጢአቶችን የቶሞላ ሰዎች ጌታ ይድረስላችኹ!🙏

ሕዝባችን እኼ ቀልድ ነው ሳቅ ካላልከውኮ አይገባውም ሲረስ አድርገውት ከየትኛው ጎን ይላለ! 😭😂

እፎይ እና አክሊል በመባል የሚታወቁ ኹለት ግለ ሰብኦች በእኛ ላይ አላስፈላጊ የጾታዊ ትንኮሳ ቃላት ውርወራቸውን ተከትሎ ማሕበራችን ምክክር አድርጎ ለተለየ ዓላማ አቋቁሞት የነበረውን የሕግ ክፍል መሬት ላይ ወርዶ በሕግ እንደሚይዘው ለሕዝብ ማሳወቅ እንፈልጋለን! ከጎድናችን ስለ ምትኾኑ እናመሰግናለን!

አይ ሳላሕ መጽሐፍ ሙሉ ከነ ሕዳጉ copy paste አደረጋት በቃ ወይ እቺ ዓለም!😁 ከዛ ሐጸፊ ኡስታዝ ሳላሕ!

ከዚኽ ቀደም ኡስታዝ ሳላሕ እና ጭፍን ተከታዮቹ “Viki” መጽሐፍ ጻፈ የሚለውን ሰምተው ሲሳለቁ ነበር…የሚገርመው ነገር እሱ ትላንት በነበረው ውይይት መጽሐፉ ምሉ ጽፎ አንድም ዐዲስ ነገር ከመጽሐፉ ይዞ በማምጣት አላሳየም! መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዟል ብሎ ለማሳየት ሲያመጣቸው የነበሩ ማስረጃዎች ከ5 ዓመት ያነሱት የነበረውን ማስረጃ ነው። መጽሐፉን ለምን አልተጠቀመም? ምክንያቱም የሐሰት ጥናታዊ ዓይነት ከበይነ መረብ ተጠራቅሞ የተሰበሰበ መጽሐፍ መኾኑ ነው። የሚያሳዝነው ነገር ከነሕዳጉ መኮረጁ ነው! እግዞ። እኔ በሥራዬ አልኩራራም ከንቱ መኾኔን አምናለኹ ግን ይቅርታ አርጉልኝና ድንጋዩን አላህ ከሚያመልክ ሰው በ100 እጥፍ እበልጣለኹ። መጽሐፌን ያነበባችኹት ሰዎች በዛ ዙርያ ውይይት ቢገባ ምን ያክል ዲባቅ ሊመቱ እንደሚችሉ አስቡት እናንተ ምስክር ናችኹ…ከሀ እስከፐ ሙግትና ማስረጃ ነው የሞላው አሕመዲያ የሚባሉ የእስልምና ክፍል እንኳን ዒሳ ሙቷል ይላሉ የሚል ዓረፍተ ነገር አላስገባሁበትም ምክንያቱም ክርክሬ እስልምና ዒሳ ሙቷል ይላል ስለኾነ ሙግትና ማስረጃ ለማቅረብ እነሱን ከማንሳት ጊዜ አላገኘሁም እነሱን ሳላነሳና የሚያነሱትን ሙግት ሳልጠቀም ነበር እርእሱን ለዓራት ከፍዬ የቀጠቀጥኩት። ኡስታዝ ወሒድ በመጽሐፍ ቅዱስ ዒሳ አልተሰቀለም ብሎ እየዘለለ ጥቅስ ይቆራርጣል ግን ለአንባቢዎች ሙሉ እውቀትን አይሰጥም እሱ የሚፈልጋቸውን ጥቅሶች ያስቀምጣል እንጅ እኛ ተሰቀለ ለማለት የምናነሳቸውን ጥቅሶች አይበራራም። እኔ ግን ያደረግኩት መጀመሪያ ለ4 ምዕራፍ ከፈልኩት። ምዕራፍ 1 የዒሳ መሰቀል በቁርዓን ምዕራፍ 2 ዘመናዊ ዳዒዎች ለዒሳ አለመሰቀል የሚያነሱት ምጉት ምዕራፍ 3 የዒሳ መሰቀል በሐዲስ ምዕራፍ 4 ዘመናዊ ዳዒዎች ለዒሳ አለመሰቀል በሐዲስት የሚያነሱት ምጉት መጽሐፉ አልቆ ከገበያ ጠፍቷል ግን ማንበብ የምትፈልጉ ይጠቅመናል ያላችሁ ከየትም ፈክጋቹ እንድታነቡት እጋብዛቹኋል።

ኧረ ሳዊሮስ የተባለውን ድሩዬ የኾነ ነገር አድርጉልን…

አስደናቂው የወንጌል ትምህርት ለሀብታሞች። እንደው ገንዘብ ግን እማያስደርገን የለ…
አስደናቂው የወንጌል ትምህርት ለሀብታሞች። እንደው ገንዘብ ግን እማያስደርገን የለ…

እስቲ እንመካከር… ይኽ የክፉዎች ዓለም ጥላ የሌለው ቅርንጫፍ ነው ዘወር በል ሌላ መጥልያ ፈልግ! ደግሞም በመንገድኽ ምስጢርኽን ወዳጄ ነው ብለኽ ለማንም አታካፍል እሱም ወዳጅ አለው። ሳልሰራልኽ…ፈረሶቹ እየሮጡ ነው ረግጠው እንዳያደቁኽ ቢደክምኽም ለማረፍ ዕንዳታስብ ወንድሜ። አቶ ደንቆሮ!

እማምላክን አሳዘናችኹኝ ማለቴ ከኛ የተሻለ ሰው ይኖራል ብለን አስበን ብንጠይቅ ክርስቲያኑ ኹሉ መናጢ ደኃ እንደኛ ነው…ማንም ዝር አላለምኮ🥲 የምርም ሰስታችኹ ሳይኾን ከእኛ የባሳችኹ ኹናችኹ ከኾነ ዝም ያላችኹት በቃ እኛ ከእናንተ ተሽለናል በልጠናል ማለት ነው ስለዚህ ካሉን አስቀድመን ከገዛናቸው አንድ ኹለቱን ለተቸገረ እንሰጣለን😁 ቀልድ አይደለም ቁምነገር ነው ምክንያቱም ዝም ካላችኹ ከኛ ትብሳላችኹ ማለት ነው ከኾነ ደግሞ እኛ እንረዳችኹ ዘንድ ግድ ይላል።🥰

መጻሕፍቱን ራሳችን መግዛት እንችላለን እናንተ መርጣችኹ እኔ የዚኽን ያክል እችላለኹ ማለት ትችላላችኹ!

ማሳሰቢያ መጻሕፍት መደበር ያላቹ ከዚህ የተሻለ ዋጋ የንግሸጥሉን አናግሩን እኛ እስካሁን ከዚህ የተሻለ ዋጋ አላገኘንም። 1. ጊዮርጊስ ወልደ አሚድ = ትልቁ 3000 በትንሿ 1500 2. ጽንዐ ተዋሕዶ (በአማን ነጸረ)= 1500 3. ዕቅበተ እምነት በነገረ ድኅነት (ዳዊት አብርሃም)= 400 4. መጽሐፈ ሰዓታት ንባቡና ትርጓሜው (መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ)= 600 5. ነገረ ክርስቶስ ክፍል አንድ (መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ)= 700 6. የአንቀጸ ብርሃን አንድምታ ትርጓሜ (መ/ር ኃይለ ማርያም ዘውዱ)= 550 7. ትቤ ተዋሕዶ (መምህር መዝገበ ቃል ገብረ ሕይወት)= 200 8. አራቱ ኃያላን (ዲያቆን ዳንኤል ክብረት) = 2000 9. ፍኖተ ሊቃውንት ቅጽ 1 (ዲ/ን አሻግሬ አምጤ)= 780 10. ነቅዓ መጻሕፍት (ቀሲስ ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ)= 1500 11. ጸያሔ ፍኖት (አባ ገብረ ኪዳን ግርማ)= 1000 12. መጽሐፈ ቅዳሴ (ከቀድሞ አባቶች ሲወርድ ሲወራረድ የመጣው ንባቡና ትርጓሜው)= 3000 13. መጽሐፈ መነኮሳት = ባለ 3500 እና ባለ 2500 (የምንፈልገው አንዱን ነው) 14. መጽሐፈ ቅኔ (መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ) ቅጽ አንድ እና ሁለት 2000 15. ትርጓሜ አርባዕቱ ወንጌላት ግዕዝ በግዕዝ 2000 16.ነገረ ማርያም (ይህ ሁሉም ሰው ከሚያውቀው ነገረ ማርያም የተለየ ከቀድሞ አባቶች ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው ትልቅ መጽሐፍ ነው። 10,000

እሺ አንድ ሕንጻ ለማሠራት አቅደናል ድንጋይ ግዙልን… ለዚኽማ ትረባረባላችኹ አይደል!😁😭 እናልቅስ እንሳቅኮ ግራ ገባን

እስኪ ጽደቁብን! ሰው ለድንጋይ በኩራት ያውም በዚኽ ሰዓት እየለመነ ከኾነ እኛ ለቅንጭላት ሥሪት (መጽሐፍ) የማንጠይቅበት ምክንያት ምንድነው…? የመጻሕፍት ጥማት አለን…ብዙ መጻሕፍት…በተለይ በምዕራቡ ዓለም ያላችኹ አደራ ዓረብ አገር አላልንም የእናንተን ላብ መብላት መቅሰፍት ያመጣብናል…ግን በምዕራቡ ዓለም ያላችኹ እኽት ወንድሞች የሻያችኹን ለእኛ ብትሰዉልን ምን ያክል እንደ ሚጠቅመን ብታውቁ…ወደ እጃችን ጥሬ ገንዘብ አንፈልግም የምንፈልጋቸው የመጻሕፍት ዝርዝር ከነዋጋቸው እናስቀምጥላችኹና ከዛ የአቅማችኹን እኔ እኼን እችላለኹ እያላችኹ ትጸድቁብናላችኹ የሰጣችኹትንም ብር መጽሐፍ ተገዝቶበት በቪድዮ ለኹላችኹም እናሳያቹኋለን። ከነ መግዣውና ወዳየለንበት ማስመጫ ብዙ ሺሕ ብር ገብረናል ከኛ ከራሳችን ትተን አይደለም የምንጠይቃችኹ! 50 ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክም እንዲሉ አበው! ወሬኞች እየለመኑ ነው…በሉ ደግሞ አሏችኹ…ለመጽሐፍ መለመን አይደለም ግብረ ኃይል አደራጅተን ለመዝረፍ ዝግጁ ነን…ትለቅዳለኽ እንዴ ጃል እንደውም እናንተም ስጡን! ለዚኽ እውነቱን ለመናገር በውጭ የሚኖር ኗሪ 10 እንኳን በቂ ነው። ምን ትላላችኹ አግዛለኹ የሚል ሰው ይኖር ይኾን…? የመጻሕፍት ዝርዝራቸውን እንልቀቅላችኹ?