Procurement Insights Ethiopia
Ir al canal en Telegram
Join us for expert insights, best practices, updates, and advisory on procurement of Local and International market. ይህ ቻናል በኢትዮጵያና ዓለም አቀፍ የግዢ ሂደት ላይ በማተኮር መረጃ የሚሰጥ ሲሆን፦ ሙያዊ እይታዎች፣ ምርጥ ተሞክሮዎች ፣ መረጃዎችና ምክረ ሃሳቦች ይቀርቡበታል። ቤተሰብ ይሁኑ! ያግኙን: @Procinsight_bot
Mostrar más1 241
Suscriptores
Sin datos24 horas
+27 días
+1030 días
Archivo de publicaciones
📌 ጨረታ ማስገቢያ ቀን መርሳት የሌለባችሁ 3 ዋና ዋና ጉዳዮች! 📑
ለጨረታ ተወዳዳሪዎች የሚሆኑ ወሳኝ ማስታወሻዎች፡-
1. የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Security) የተጠየቀ ከሆነ በጨረታ ሰነዱ አስተሻሸግ መሠረት መያያዙን ማረጋገጥ 💰
2. የሰነዶች ዝግጅትና ማህተም ✍️
እያንዳንዱ ገጽ ላይ ማህተም እና ፊርማ መኖሩን፣ እንዲሁም የቴክኒክ እና የፋይናንስ ሰነዶች በታዘዘው መሠረት (Original & Copy) መለየታቸውን ያረጋግጡ።
3. የሰዓት እና የቦታ ጥንቃቄ ⏰
ጨረታው የሚዘጋበትን ሰዓት በኢትዮጵያ አቆጣጠር ይሁን በፈረንጅ ለይተው በማወቅ፣ ቢያንስ ከ1 ሰዓት በፊት ሰነዱን ያስገቡ።
በተለይ በ e-GP የሚከናወኑ ጨረታዎች ላይ የኢንተርኔት መቆራረጥን ታሳቢ በማድረግ ቀድሞ መጫን ብልህነት ነው።
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
✍✍ በእጅ የተሞላ የፋይናንሻል ፕሮፖዛል (Financial Proposal)✍✍
🟢 በጨረታ ውድድር ወቅት የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድን (Bill of Quantities) ኦሪጅናል ላይ በእጅ ሞልቶ ማቅረብ በተለያዩ ግዥዎች ላይ የተለመደ ነው።
🟠 አንዳንድ ተቋማት በኦሪጅናል ጨረታ ሰነዱ የዋጋ ማቅረቢያ ላይ በእጅ ተፅፎ ያልቀረበን financial offer ተቀባይነት የለውም በሚል መጫረቻ ሰነዱን ውድቅ ያደርጋሉ። ሆኖም ይህ አግባብ የሆነ መስፈርት አይደለም።
🟢 ጨረታን በእጅ ወይም በኮምፒውተር ተፅፎ መቅረብ እንዳለበት የተቀመጡ አስገዳጅ ሁኔታዎች ባይኖሩም እንኳ በማይጠፋ ቀለም (Indelible Ink) መፃፍ እንዳለበት ግን አብዛኛው SBD ላይ የተጫራቾች መመሪያ ላይ ይገለፃል።
🟣 በእጅ የተፃፉ ቁጥሮችን ለመረዳት አሻሚ ከመሆኑ አንፃር በእጅ የተፃፈ ፋይናንሻል ማስገባት አይመከርም።
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
+1
Officials of Addis Abeba’s City Administration have ordered a freeze on new procurements across the bureaucracy, imposing a citywide spending clampdown as the capital enters the final quarter of the fiscal year, in an attempt to halt the rush to exhaust public budgets.
📌 የነዳጅ እጥረት/ ዋጋ መናር በግንባታ ውሎች ላይ ላለው ተፅዕኖ ምን መፍትሄ አለ?
🟣 የዋጋ ማስተካከያ አንቀጽ በውሉ ውስጥ ካለ፣ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው በውሉ ቀመር (Formula) መሠረት ተሰልቶ የሚከፈል በመሆኑ ስጋቱ በተወሰነ መልኩ ይቀንሳል። ሆኖም ነዳጅ ካለመገኘቱ ጋር ተያይዞ ለሚመጣ የስራ መጓተት፣ ተቋራጩ የጊዜ ማራዘሚያ (EOT) የሚያሰጠው ነው።
🟢 የዋጋ ማስተካከያ (Price Adjustment) ለሌላቸው ውሎች የነዳጅ ዋጋ መናር እና እጥረት ችግሩ አገራዊ በመሆኑ እና በርካታ ፕሮጀክቶችን ሊያስተጓጉል ስለሚችል፣ የሚመለከተው አካል (የገንዘብ ሚኒስቴር) ልዩ መመሪያ በማውጣት የዋጋ ማስተካከያ እንዲደረግ ሊፈቅድ ይችላል። አሰሪ መ/ቤቶች ይህንን ልዩ ፈቃድ ሊጠይቁ ይችላሉ።
🟢 የነዳጅ ዋጋ መናር እና እጥረት ለረጅም ጊዜ ቀጣይነት ያለው ከሆነ የሚከተሉት አማራጮችም ሊታዩ ይችላሉ👇
1⃣ ሥራን ለጊዜው ማቆም (Suspension):
ነዳጅ ጨርሶ ካልተገኘ (በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ፕሮጀክቶች ላይ) ሥራን ለጊዜው ማቆም አማራጭ ነው። ሆኖም ተቋራጩ በራሱ ውሳኔ ሥራ ከማቆም ይልቅ፣ አሰሪው በጽሁፍ ሥራ እንዲያቆም (Suspension order) እንዲሰጠው መጠየቅ ይኖርበታል።
2⃣ ውልን በስምምነት ማቋረጥ (Amicable Termination):
የነዳጅ እጥረቱ እና የዋጋ ንረቱ ተቋራጩን ሙሉ በሙሉ ከስራ ውጭ የሚያደርገውና ፕሮጀክቱንም ለከፋ መጓተት የሚዳርገው ከሆነ፤ ሁለቱ ወገኖች ተነጋግረው ያለምንም የቅጣት ክፍያ ውልን በስምምነት ማቋረጥ ይችላሉ።
ተጨማሪ ሃሳብ ካለዎት ያጋሩን?
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
Manufacturer’s Authorization [በአምራቹ የተሰጠ የአቅራቢነት ሥልጣን]
❇️ የዕቃ ግዥዎች በምናከናውንበት ጊዜ ተጫራቾች ራሳቸው የዕቃው አምራቾች ካልሆኑ የሚያቀርቧቸው ዕቃዎችና ተያያዥ አገልግሎቶች የአምራች ድርጅት መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
❇️ ይህም የሚቀርብበት ቅፅ በጨረታ ሰነዱ ላይ መካተት ይኖርበታል። ይህ ከአምራቹ የተሰጠ የአቅራቢነት ፈቃድ፤ ፈቃድ በሰጠው የማምረቻ ተቋም አርማ ባለበት ደብዳቤ ሰፍሮ እና የመፈረም ስልጣን ባለው አካል ተፈርሞ ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት።
❇️ Manufacturer’s Authorization (MaF) ለምን ያስፈልጋል?
📍የተጫራቹን በትክክል ከአምራቹ ጋር ህጋዊ ግንኙነት ያለው መሆኑን እና ጥራት ያለው አስተማማኝ እቃዎችን ማቅረብ እንደሚችል ወይም Grey-market goods (ከአምራቹ በትክክለኛው መንገድ ያልመጡ) እቃዎችን እንደማያቀርብ ለማረጋገጥ
📍ተጫራች ያቀረባቸውን ዕቃዎችና ተያያዥ አገልግሎቶች በተመለከተ ዋስትና ያለው መሆኑን ለማረጋገጥ
📍ተጫራቾች በተያዘለት ጊዜ ዕቃዎቹን ማቅረብ እንደሚችል መተማመንን ይፈጥራል
📍ትክክለኛ እና አስተማማኝ ተጫራቾች መሆናቸውን ማወቅ ያስችላል
❇️ የቀረበው Manufacturer’s Authorization ትክክለኛ ስለመሆኑ አምራቹን በቀጥታ በመጠየቅ ማረጋገጥ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል።
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
+3
#Procurement_Tips
📢 Join: @procinsightet or https://www.tiktok.com/@procurement_insight_et?_r=1&_t=ZS-94lmuoMNezv
📬 Contact: @Procinsight_bot
⛔️በጨረታ ሰነድ ላይ ባልተቀመጠ መስፈርት ግምገማ ማከናወን🙊🙊
🔴 የጨረታ ግምገማ ሂደት ላይ ካሉ መሠረታዊ ስህተቶች መካከል የግምገማ መስፈርቶችን በግምገማ ሂደት ላይ መቀየር ወይም በጨረታ ሰነዱ ላይ ባልተቀመጠ መስፈርት መገምገም ይጠቀሳል።
🟣 በመንግስትና በዓለም አቀፍ አበዳሪዎች ፋይናንስ የሚደረጉ ጨረታዎች ላይ ይህ ሆኖ ቢገኝ ፍትሃዊነትን የሚያጎድልና የጨረታ ሂደቱን ውድቅ የሚያስደርግ ስህተት ነው።
📢 Join: @procinsightet or https://www.tiktok.com/@procurement_insight_et?_r=1&_t=ZS-94lmuoMNezv
📬 Contact: @Procinsight_bot
📢 We’re Now on TikTok!
We’re excited to announce that Procurement Insight Ethiopia is now sharing short, practical procurement tips on TikTok 🎥
🔐https://vt.tiktok.com/ZSu9nVfqR/
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ረቂቅ የግዥ መመሪያ ምን ይዟል❓
🟢 ይህ ረቂቅ መመሪያ ከአንድ ወር በፊት በከተማ አስተዳደሩ ምክርቤት አዲስ የግዥ አዋጅ መፅደቁን ተከትሎ የተዘጋጀ ነው። ሆኖም የፀደቀውን የግዥ አዋጅ ቢሮው እስካሁን ይፋ አላደረገም።
🟣 ረቂቅ መመሪያው ባለፈው ዓመት ከፀደቀው የፌደራል ግዥ መመሪያ ጋር በይዘት ተመሳሳይ ሆኖ የተዘጋጀ ነው።
📍📍ከፌደራል ግዥ መመሪያው የቀየራቸው ምን ዋና ዋና ነገሮች አሉት?
1⃣ ለግንባታ ሥራ የዋጋ ማስተካከያ የሚደረገው ውሉ ተፈጻሚ መሆን ከጀመረበት ከዘጠኝ ወራት በኋላ ተደርጓል። በፌደራል ግዥ መመሪያው 12 ወራት እና ከዚህ በላይ ለሚቆዩ የግንባታ ስራዎች ውሉ ተፈጻሚ መሆን ከጀመረበት ከስድስት ወራት በኋላ የዋጋ ማስተካከያ የሚደረግላቸው መሆኑ ይታወሳል። ለማዕቀፍ ግዥ እንዲሁ ከ ሶስት ወራት ወደ ስድስት ወራት ከፍ ተደርጓል።
2⃣ በቀጥታ ግዥ ዘዴ የሚፈፀም ግዥ መካከል በነጠላ ቁርጥ ዋጋ (fixed rate) በከተማ አስተዳደሩ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ እያጠና በሚያቀርበው ወይም በከተማ አስተዳደሩ የቁርጥ ዋጋ እያጠና እንዲተክል በሚፈቀድለት ሌላ አስፈጻሚ አካል በሚያወጣው የኮንስትራክሽን ስራዎችና ሌሎች ተያያዥነት ያላቸው ስራዎች ነጠላ ቁርጥ ዋጋ ግዥ ለመፈፀም እንደሚቻል አካቷል።
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
የአዲስ አበባ ከተማ የግዥ መመሪያ ረቂቅ አስተያየት እንዲሰጥበት የከተማው ፋይናንስ ቢሮ አጋርቷል☝️
አስተያየታችሁን በዚህ ላኩልን👇
@Procinsight_bot
📢 Join: @procinsightet
👵 Discussion: @procinsightet2
+2
ለመረጃ | ብሄራዊ ባንክ ውል ማስከበሪያ ዋስትናን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ለኢንሹራንስ ኩባንያዎች ያስተላለፈው መመሪያ
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
🔑 ለጨረታ ማስከበሪያ ከመድን የሚቀርቡ ዋስትናዎች (Conditional Bond) ከዚህ በኋላ ተቀባይነት አይኖራቸውም። ስራ ተቋራጮች ለውል ማስከበሪያ ከመድን የሚያቀርቡት ዋስትና Unconditional መሆን ይጠበቅበታል።
📌 በነባሩ የፌደራል ግዥ መመሪያ በግንባታ ስራ ለተሰማሩ የሃገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የመድን ዋስትና (Conditional Insurance Bonds) ለጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የነበረው ቢሆንም አዲሱ መመሪያ ይህንን አማራጭ አላካተተም።
📌 ለውል ማስከበሪያ ደግሞ ከአገር ውስጥ የግንባታ ዘርፍ ሥራ ተቋራጮች ወይም መድሐኒት እና የሕክምና መሣሪያዎች አምራች ድርጅቶች ለሚፈጸም ግዥ ከታወቀ የመድን ድርጅት የሚቀርብ በሁኔታ ላይ ተመሠረተ የመድን ዋስትና ቢያቀርቡ ተቀባይነት የነበረው ቢሆንም በአዲሱ የግዥ መመሪያ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ መሆን እንዳለበት ተመላክቷል።
N.B. የሃገር ውስጥ መድን ድርጅቶች በብሄራዊ ባንክ በኩል በተሰጣቸው መመሪያ መሰረት በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ዋስትና (Unconditional) መስጠት የማይችሉ ከመሆኑ አንጻር ይህ እንዴት ተፈጻሚ ሊሆን እንደሚችል ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው።
📌 የአገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች እንዲሁም የመድሀኒት እና ሕክምና መሳሪያ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሁኔታ ላይ የተመሰረተ (conditional) የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና (Advance Payment Guarantee) ከታወቀ የመድን ድርጅት ሊያቀርቡ እንደሚችሉ የሚገልፀው አንቀፅ ባለበት ፀንቷል።
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
ከአቅም በላይ ሁኔታ (Force Majeure)
🟢 በውል አስተዳደር ወቅት የሚያጋጥሙ ከአቅም በላይ ሁኔታ (Force Majeure) በተመለከተ አዲሱ የፌደራል ግዥ መመሪያ አንቀፅ 149 ዝርዝር ጉዳዮችን አካቷል።
🔴 ያስታውሱ: ግልጽ የሆነ ተቃራኒ የውል ቃል ከሌለ በቀር ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ሁኔታዎች ከአቅም በላይ የሆኑ ችግሮች ተደርገው ሊቆጠሩ አይችሉም።
1⃣ ለውሉ አፈጻጸም አስፈላጊ የሆኑ አቅርቦቶች ዋጋ መወደድ ወይም መርከስ (Increases or decreases in prices of essential supplies for contract performance)
2⃣ ተዋዋይ ያለበትን የውል ግዴታ አፈጻጸም ወጪ የሚያከብድበት አዳዲስ ህግ መውጣት (New legislation rendering contractual obligations more onerous)
ዝርዝሩ ከላይ ተያይዟል☝️
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
⭐️Variation/ተጨማሪ ስራ/✨
በፌደራል የግዥ መመሪያ መሠረት:
🟢 ያልታሰቡ ሁኔታዎች በማጋጠማቸው ምክንያት በመጀመሪያ ውል ውስጥ ያልተካተቱ ተጨማሪ የግንባታ ሥራዎች ማሠራት አስፈላጊ ሲሆንና በቴክኒክ ወይም በኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ምክንያት እነዚህን ተጨማሪ የግንባታ ሥራዎች ከመጀመሪያው ውል ነጥሎ ማሠራት የማይቻል ሲሆን ተጨማሪ ስራ ማሰራት ይቻላል።
🟣 በተጨማሪነት ወይም በዋናው ሥራ ውስጥ ያልተካተቱ አዲስ የሚሰሩ የግንባታ ሥራዎች የገንዘብ መጠን ከመጀመሪያው ውል ጠቅላላ ዋጋ ከ30% /ሠላሳ በመቶ/ የበለጠ መሆን የለበትም።
🔴 አሸናፊው ተጫራች በውድድር ከተመረጠ በኋላ ከተፈረመ ውል ውጭ የመጀመሪያው ግዥ የተከናወነባቸው ከምክር ውጭ የሆነ አገልግሎት ወይም የምክር አገልግሎት ሥራዎች ወይም አቅርቦቶች ውል አጥጋቢ በሆነ ሁኔታ መጠናቀቁ እና ቁጠባንና ቅልጥፍናን የሚያስገኝ መሆኑ በመረጋገጡ ቀደም ሲል ውሉን ከፈረመው አቅራቢ እንዲሠራ ወይም እንዲቀርብ ማድረግ አስፈላጊ ሲሆን፣ በተጨማሪነት የሚታዘዘው ዕቃ፣ የምክር ወይም ሌሎች አገልግሎት ግዥ መጠን ከውሉ ጠቅላላ ዋጋ 25% (ሃያ አምስት በመቶ) መብለጥ የለበትም።
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
Foreign_Contractors_Performance_Rating_Report_for_the_month_of_December.pdf3.27 KB
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
