ኢት-መጽሐፍት | ETHIO-BOOKS
Ir al canal en Telegram
👉 "የምታነበው መጽሐፍ ለአንተ የሚያስብልህ ሳይሆን አንተ እንድታስብ የሚያደርግ ነው።" ሃርፐር ሊ Fiction (ልቦለድ), History (ታሪክ), Politics (ፖለቲካ), Psychology (ስነልቦና), Biography (ግለ-ታሪክ), Self-help(ራስ አገዝ),& Philosophy(ፍልስፍና) የሀገር ውስጥ & የውጪ ሀገር መጽሐፎችን ያገኛሉ!አስተያየትዎን እዚህ @Desutech_bot ያድርሱን
Mostrar más1 991
Suscriptores
-124 horas
-47 días
-5230 días
Archivo de publicaciones
እረፉ!
“ዘመመ!” ብላችሁ የሰው ቤት አትግፉ
እሾህ ለማሳመር አበባ አታርግፉ።
እረፍ!
“ቆሜያለሁ!” ለማለት አጥሬን አትደገፍ
ለአመዳም ወዘናህ ቆዳዬን አትግፈፍ።
እረፍ!
በመስመርህ ፍካ በድንበርህ ለምልም
በየአልጋህ እደር በየእንቅልፍህ አልም።
እረፊ!
በኩረጃ ንባብ ትርጉም አትግደፊ
በሰባራ መርፌሽ የሰው ልክ አትስፊ።
...ማን አንደጠለፈኝ ማን እንደሰበረኝ
ጠያቂ አጣሁ እንጂ መልስማ ነበረኝ።
እያዩ ፈንገስ (ግሩም ዘነበ)
If you want to be happy,try only to Please God,not people
ደስተኛ መሆን ከፈለክ ሰውን ሳይሆን ፈጣሪን ብቻ ለማስደሰት ሞክር
(ሊዮ ቶልስቶይ)
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚ርዕስ:- ማክቤዝ
📝ደራሲ:- ዊልያም ሼክስፒር
👤ትርጉም:- ጸጋዬ ገ/መድህን
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
የታላላቅ ፈላስፎች ሀሳቦች እና አባባሎች
@Zephilosophy
1."ገንዘብ የማይገዛው ነገር እስከሌለህ ድረስ ባለፀጋ አይደለህም።"
2."የሰው ልጅ ነፃ ነኝ ብሎ የሚያምን የልማድ ባሪያ ነው።"
3."ጉድለትህን ወደ ፍፁምነት የሚቀይረው ፤ ፈጣሪህ እንጂ ሀይማኖትህ አይደለም።"
4."የመገለጥን ብርሃን ትጨብጥ ዘንድ የሥጋን ጨለማ አሸንፍ።"
5.እያንዳንዱ ሰው ልክ እንደጨረቃ ነው፡፡ ለማንም የማያሳየው ግማሽ ጎን አለው ።
6."በፍቅር የተሰራ ኃጢያት፤ ፍቅር ከሌለበት አምልኮ ይበልጣል።"
7."ፈላስፋ በሕይወት ጨዋታ ላይ የተገኘ ተመልካች ነው።"
8."የእኔ ፍላጎት የፈጣሪን ሀሳብ ማወቅ ነው ፤ ሌላው ሁሉ ዝርዝር ጉዳይ ነወ።"
9."የምትኖረባትን ሕይወት በቅጡ ሳታውቅ ስትሞት ሌላ ዓለም መኖሩን እንዴት ታውቃለህ።"
10."ታላላቅ እምነቶች ሁሉ መነሻቸው መናፍቅነት ነው።"
11."ያልተመረመረ ህይወት ሊኖሩት የማይገባ ነው። "
12."የእግዚአብሔር ፍቃድና እውቀት በእኛ አላዋቂነት ሊፈተን አይችልም።"
13."ለማመን እንጂ ላለማመን ምክንያት አያስፈልግም።"
14."የሞት ፍርሃት የሕይወት ማጣፈጫ ቅመም ነው።"
15."መልካምነት የተደረገልህን ሳይሆን ያልተደረገልህን የመክፈል ብቃት ነው።"
16."ከፍቅር ሁሉ የሚበልጠው ምላሽ ሳያገኙ ማፍቀር መቻል ነው።"
17."የሰው ልጅ ሐሳብ እንጂ እውነት አትለዋወጥም።"
18."የሰው የነፍስ አርነት በሥጋ ባርነት የሚገኝ ልምምድ ነው።"
19."እኔ የሚል አእምሮ በጨለማ እንዳልተለኮሰ ሻማ ነው።"
20."አዕምሮ እንደፈሳሽ ወንዝ ነው ፤ መገደብ ባትችልም አዲስ መንገድ አብጅለት።"
ምንጭ- ጥበብ ከጲላጦስ
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚ርዕስ:- ኢፒክ
📝ደራሲ:- በታደለ ገድሌ
📜ዘውግ:- ዘመን አይሽሬ የስነጽሁፍ ቅርስ
📖ገፅ ብዛት: -258
📆ዓ.ም:-1995
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚ርዕስ ሀምሌት
📝ደራሲ ዊልያም ሼክስፒር
👤ትርጉም ፀጋዬ ገ/መድህን
📖ገፅ ብዛት 134
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚ርዕስ:- ፍሬው
📝ደራሲ:- ገናናው ከተማ
📜ይዘት:- በዩኒቨርስቲ ህይወት ላይ ያተኮረ
📆ዓ.ም:- 2007
📖የገፅ ብዛት:- 190
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
ሀገር ማለት ምንድ ነው ?
ዘረኝነት በጨለማ ውስጥ እንደመፋለም ነው።የጨለማ ፍልሚያ ማለት ደግሞ የራስን ወንድም ጭምር ቢሆን እንደመፋለም ነው። ከማን ጋ እየተዋጋን እንደሆነ አንረዳም። ሀገር ሲባል ቋንቋ:ልማድ ወይም እምነት የሚመስለን ሰዎች ፍጹም ስህተት ውስጥ ነን። ዘር ወይም ጎሳ ጭምር ሀገር ማለት አይደሉም ። ባህሎች ናቸው።ሲወርድ ሲዋረድ ከትውልድ ትውልድ በትውፊት የሚሻገሩ እምነቶች ናቸው።
ሀገር ግን ሀሳብ ነው።በውስጡ አላማ አለው።ፍልስፍና አለው።ራዕይ አለው።ዜግነት የሚሰኝ ከጎጥ ውጪ የሆነ ግለሠብነት አለ። የሀገር ምንነት ፍልስፍናዊ ነው። ፍጹም ልማዳዊ መሆን የለበትም።መሆንም አይችልም።ከልማድ የሚነሳ መንግስት የለም።የጎሳ ቲኦክራሲ ልንፈጥር እንችላለን ። ዘመናዊ አለም የሚገዳደር ጠንካራ የመንግስት ይዘት ግን አናገኝም።
ኢትዮጵያን ማሠብ ያለብን ልንፈጥር ከምንችለው አብዮትና አንድ መሠረት ያለው የዜግነት ቅርጽ አንጻር እንጂ በቀበሌ ቋንቋና ትውፊት ላይ የምንተራስ ከሆነ ሀገር የሚለው ቃል አልገባንም ማለት ነው።የተለያዩ ጎሳዎች በሚናገሩት ቋንቋ:እምነት ወይም ልማድ ሀገር የሚለውን ጥልቅ ሀሳብ ሊዳኙ ሲሞክሩ ማየት ተለምዷል።ነውር ነው!! ሀገርና ልማድ የማይለይ ትውልድ ተፈጥሯል ማለት ነው።ልማድ ምክንያት የሌለው የማይለወጥ ግን እንዲሁ በህዝቦች ሽግግር የሚያልፍ ስርዐት ነው።ሀገር ግን ከዚህ ይለያል።በየዘመኑ እያደገ በሚመጣ ፍልስፍና : ርዕዮት አለም ወይም ዕሳቤ የሚጎላበት ትርጉምና ምንነት የሚኖር የብዙ ህዝቦች አንድነት መጠሪያ ነው።
መሀመድ አሊ ቡርሀን
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚ርዕስ :- ፍካሬ ከዋከብት
📝ደራሲ:- አባይነህ አበራ
📜ይዘት :- ስለ ኮኮቦቻችን
📖የገጽ ብዛት:- 192
📅ዓ.ም:- 1986
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚ርዕስ :-አቡሻክር
©ቋንቋ:- አማረኛ
📜ይዘት :- የቀን መቁጠሪያ
📖የገጽ ብዛት:- ፩- ፻፫
📅ዓ.ም:- ፩፱፻፷፪
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚ርዕስ:- ባሕረ ሃሳብ
📝ደራሲ:- ጌታቸው ኃይሌ
📅ዓ ም:- 1993
📖የገፅ ብዛት:- 303
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚ርዕስ፦ ኮዛ ኖስትራ (the Mafia)
📝ደራሲ:- ጆን ዳይኪ
👤ትርጉም:- መኩሪያ መካሼ
📜ዘውግ:- የሲሲሊ ማፊያ አስደናቂ ታሪክ
📖የገጽብዛት፦ 192
📆ዓ.ም:- 2007
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚ርዕስ፦ ሳልሳውቷ ልጃገረድ
📝ደራሲ:- አጋጣሚ ክርስቲ
👤ትርጉም:- አብይ ደምሴ
📜ዘውግ:-.......
📖የገጽብዛት፦245
📆ዓ.ም:- 1982
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
የህይወት_ፍልስፍና ( Life_Philosophy )
የሰው ልጅ ከተፈጠረበት ጀምሮ ኑሮን ለመምራት በሚያደርግበት ግዜ የተለያዩ መሰናክሎች ወይም አንቅፋቶች ያጋጥሙታል። ቁልፉ ግን የህይወትን አላማ ግብ መረዳት ነው። ባጋጠሙት እንቅፋቶች ምክንያት የህይወቱን አላማ ከዳር ሳያደርስ በመንገድ ላይ ሊገታ ይችላል። ስለዚህ ለስኬቱ መዳረስ የሚያራምደው የህይወት አመለካከት ወይም ፍልስፍና ቁልፍ ሚና ይጫወታል። አንዳንዴ ግን የህይወትን ፍልስፍና መያዙ ብቻ በቂ አይደለም። ፍልስፍናውን መከተልና መሆን(ዋነኛው የህይወቱ አካል አድርጎ መኖር) በጣም የተለያዩ ነገሮች ናቸው።
የህይወታችንን ግብ ከዳር አንዲደርስ ሁለት ግዙፍ የህይወት አመለካከት ግንባሮች አሉ (የሁለቱም ፍልስፍና አራማጆች በየግላቸው ትክክል ነው ብለው ያምናሉ ለምሳሌ ሁለት የእግር ኳስ ቡድኖች አሉ። ሁለቱም ለማሸነፍ ወደ ሜዳ ይገባሉ። ሁለቱም የአጨዋወት ስልት አላቸው። አንዱ የያዘው ስልት ለራሱ ትክክል ነው ለተጋጣሚው ግን ስህተት ነው ሌላውም በተመሳሳይ):-
🤔 1) ፕሮታጎኒስት (Protagonist):- የፕሮታጎኒስት አቀንቃኞች የሰው ልጅ እያንዳንዱን ቀን በታላቅ ትጋት መስራት አለባቸው ፣ በቻሉት መጠን ከራሳቸው አልፈው ለሌላው የሚፈይድ አንዳች መልካም ወይም ቀና የሆነ ተግባር መፈፀም አለባቸው። በህይወት ለሚያጋጥማቸው አያንዳንዱ መልካም ሆነ አሳዛኝ ገጠመኝ ሳይበገሩ ወደ ፊት መቀጠል አለባቸው ምክንያቱም ሁሉም የሰው ልጅ በምድር ላይ የተፈጠረበት ትልቁ ምክንያት በህይወት ዘመኑ መልካም ነገር ለመስራት አንጂ ኖሮ ኖሮ ለመሞት በቻ አይደለም ብለው ያምናሉ።
፨ የፕሮታጎኒስቶችን ፍልስፍና ጠቅለል ስናደርገው:-
• የሰው ልጅ የተፈጠረው ለስራና ለስራ በቻ ነው ፣
• ሁሌም ቢሆን መልካም ነገር መስራት ይኖርብናል ፣
• ተስፋ መቁረጥ በምንም ተዓምር የለበትም ፣
• ዛሬን ሳይሆን ነገን ነው መኖር የሚገባን ፣
• ሁሌም ወደ ኋላ ሳይሆን ወደ ፊት ይሉናል።
🤔 2) አንታጎኒስት (Antagonist):- አንታጎኒስቶች ያላቸው የህይወት ፍልስፍና የሰው ልጅ ሞትን ማሸነፍ ካልቻለ አልያም የሰው ልጅ መጨረሻው ሞት ከሆነ ህይወት ነገ ሳትሆን ዛሬ በቻ ናት። ስለዚህ የሰው ልጅ መኖር ያለበተደ ዛሬን ብቻ ባሻው መንገድ መሆን አለበት። ስራ ፣ አላማ ፣ ፅናት ፣ ግብ ፣ ራዕይ ... ወዘተ የሚባል ኮተት ሁሉ ከንቱ ስንቅ ነው። አጅግ መናጢ የሆነው ግለሰብና የናጠጠው ሀብታምም መጨረሻው ሞት ነው። ጠ/ሚኒስትሩው ፣ ኩሊው ፣ የተማረው ፣ ያልተማረው ፣ ስኬታማው ፣ ስኬት አልባው ... ሁሉም ይሞታሉ። ታዲያ ሞት የማይቀርል ዕዳ ከሆነ ምን አስለፋን ፣ አስደከመን ...? ሞት የማይቀር ከሆነ የሰው ልጅ ነገን እያሰበ ሳይሆን ዛሬን ብቻ መኖር አለበት ምክንያቱም የሰው ልጅ ምንም ይሁን ምንም መጨረሻው ሞት ነውና የሚል አመለካከት ያራምዳሉ።
፨ የአንታጎኒስቶችን ፍልስፍና ጠቅለል ሲደረግ:-
• የሰው ልጅ ይሞታል ፣
• ዛሬን ብቻ ነው መኖር ያለብን ፣
• የተፈጠርነው ለደስታ በቻ ነው ፣
• ሁሉም ነገር የተፃፈልን ስለሆነ መለወጥ አይቻለንም።
፨ ስለ ህይወት ፍልስፍና አንዳንድ ጥሬ ሀቆች
# በምድራችን ላይ ካሉት በቢልዬን የሚቆጠር ህዝብ መካከል ሶስት አራተኛው ወይም 75% የአንታጎኒስት አመለካከትን አስበውበት ይሁን ሳያስቡበት ያራምዳሉ። አንድ አራተኛው ወይም 25% የፕሮታጎኒስት አመለካከት ተከታዮች ናቸው።
አኛስ ከየትኞቹ ወገን ነን ...? ሀሳብና ድርጊት በጣም የተለያዩ ጥሬ ሀቆች ናቸው። አንዳንዴ በሀሳብ ደረጃ ተቀብለን በድርጊት ካልገለፅነው ትርጉም የለሽ ይሆናል። ስለዚህ ስንቶቻችን ነን ሀሳብና ድርጊት ሆድና ጀርባ መሆናቸው ቀርቶ መርፌና ክር የሆኑልን?
pdf ከፈለጋቸቹ በውስጥ አውሩኝ እለቅላቸዋለው 🙏
ምንጭ :- "ኦያያ ፣ 2000 ከፓሪስ መልስ"
✍ ደራሲ :- አዘርግ
📚ርዕስ:- ዩቶፒያ
📝ደራሲ:- ቶማስ ሞር
📜ዘውግ:- ታሪክ ምርምር
📅ዓ.ም፦ 1508
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
ርዕስ=የሸገር ወጎች(2005 ላይ የታተመ)
ደራሲ=ሰለሞን ታደሰ
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
