የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ Addis Ababa Revenues Bureau
Ir al canal en Telegram
Mostrar más
6 399
Suscriptores
-424 horas
+297 días
+12830 días
Archivo de publicaciones
ገቢን በተመለከተ
ባለፉት አምስት ዓመታት የገቢ መሰረትን በማስፋትና አዳዲስ ግብር ከፋዮችን በማካተት የከተማዋን ገቢ በ2013 ከነበረበት 51 ቢሊዮን ብር በ2018 ወደ 350 ቢሊዮን ብር ማሳደግ ተችሏል። የ2018 የገቢ አሰባሰብ ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ50 በመቶ (116.3 ቢሊዮን ብር) ዕድገት አሳይቷል።
ሐምሌ 05 / 11 / 2018 ዓ.ም
+5
ገቢን በተመለከተ
ባለፉት አምስት ዓመታት የገቢ መሰረትን በማስፋትና አዳዲስ ግብር ከፋዮችን በማካተት የከተማዋን ገቢ በ2013 ከነበረበት 51 ቢሊዮን ብር በ2018 ወደ 350 ቢሊዮን ብር ማሳደግ ተችሏል። የ2018 የገቢ አሰባሰብ ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ50 በመቶ (116.3 ቢሊዮን ብር) ዕድገት አሳይቷል። በዚህም አዲስ አበባ ከአፍሪካ 6 ከተሞች ቀዳሚ በመሆን ልምዷን ማካፈል ችላለች።
የበጀት ድልድል፡- ከዘንድሮው 360.07 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ በጀት ውስጥ 71 በመቶው ለዘላቂ ልማት ሲመደብ፣ 29 በመቶው ለመደበኛ ወጪ ውሏል።
ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር፡- በኦዲት ግኝቶች 200 ሚሊዮን ብር ማስመለስ የተቻለ ሲሆን፣ በ61 ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ተተግብሯል። የንብረት አያያዝን በማዘመን 6,815 የመንግስት ሕንጻዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ87 ቢሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ሀብቶች በዘመናዊ መረጃ ቋት ተመዝግበዋል። በተጨማሪም ከተጋነነ የህንጻ ኪራይ ክፍያ 100 ሚሊዮን ብር ተመልሷል።
ሀገራዊ አስተዋፅዖ፡- ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከ6.6 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት ማሰባሰብ ተችሏል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
ትራንስፖርትን በተመለከተ፡-
የህዝብ ትራንስፖርት አቅርቦትን ለማሻሻል ባለፉት አምስት ዓመታት 467 አዳዲስ አውቶቡሶች በመገዛታቸው የመንግስት አውቶቡሶች ቁጥር 1,628 ደርሷል። በዚህም የቀን ተሳፋሪዎች ቁጥር ወደ 4.19 ሚሊዮን ከፍ ሲል፤ የብዙሃን ትራንስፖርት ሽፋን ከ9 በመቶ ወደ 41 በመቶ አድጓል። ችግሩን ይበልጥ ለማቃለልም የ500 ተጨማሪ አውቶቡሶች ግዢ በሂደት ላይ ይገኛል።
የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ አገልግሎቶችን በማሻሻል የተሽከርካሪ ምዝገባ፣ የቴክኒክ ምርመራ እና የብቃት ማረጋገጫ አሰጣጥ በከፍተኛ ደረጃ ዕድገት አሳይቷል።
የትራንስፖርት ዘርፉን በቴክኖሎጂ ከመደገፍ አኳያ፤ የስምሪት ቁጥጥር፣ የትራፊክ ቅጣት ክፍያ፣ እንዲሁም 36 የሚሆኑ ዋና ዋና የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ አገልግሎቶች በዲጂታል ስርዓት እንዲሰጡ ተደርጓል። ይህም አሰራሩን ቀልጣፋ በማድረግ፣ ቅሬታን በመቀነስና የደንበኞችን እርካታ በማሳደግ ረገድ ጉልህ ለውጥ አምጥቷል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+7
የኢንዱስትሪ ልማት በተመለከተ
ባለፉት አምስት ዓመታት ለአምራች ዘርፉ በተሰጠዉ ልዩ ትኩረት የውጪ ንግድን በመተካት (ተኪ ምርትን በማምረት) በኩል 24.2 ሚሊዮን ቶን በማምረት ከፍተኛ አፈጻጸም አሳይቷል፡፡ ይህም አገሪቱ ልታወጣው የነበረውን 8.4 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ለማዳን አስችሏል።
በኤክስፖርት ዘርፍም 92,522 ቶን ምርት ለውጭ ገበያ በማቅረብ ዕቅዱን ማሳካት ተችሏል፡፡ የተገኘው የውጭ ምንዛሬ 729 ሚሊዮን ዶላር ሆኖ ተመዝግቧል።
ከዚህ በተጨማሪ፣ 2,585 የሚሆኑ አምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅማቸው የተለካ ሲሆን፣ አጠቃላይ ምርታማነታቸው 69.75 % ደርሷል።
በበጀት አመቱ ለ 664 ኢንዱስትሪዎች በ3.3 ቢሊዮን ብር 6,667 ማሽኖችን ማቅረብ፣ የምርት አቅም ለማሳደግ ደግፈናል፡፡ በተጨማሪም በመስሪያ ቦታ እና መሬት አቅርቦት ረገድ ለ 210 ኢንዱስትሪዎች ምላሽ መስጠት ተችሏል።
እነዚህን የኢንዱስትሪ ውጤታማ ለማድረግም ለ664 የመብራት፣ የመንገድ እና የውሃ መሠረተ-ልማቶች በተሟላ ሁኔታ እንዲያገኙ ተደርጓል። የካፒታል እጥረትም ለመቅረፍ ባደረግነው ጥረትም፣ 3.84 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ብድር ለአምራቾቻችን ማድረስ ችለናል።
አምራቾችን ከጥቃቅን ወደ መካከለኛ የማሸጋገር ሥራ 57% ማድረስ የተቻለበት ትኩረት የተሠጠዉ ስራ ነው፡፡
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
በወሳኝ ኩነት ዘርፍ የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችና ብተመለከተ
የአገልግሎት ሥርዓቱን በማዘመን የነዋሪነትና የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አገልግሎትን ግልጽ፣ ቀላል፣ ቀልጣፋና ፈጣን በማድረግ በፋይል ክምርና መጥፋት እንዲሁም በብልሹ አሠራር ይስተዋሉ የነበሩ ውስብስብ ችግሮችን መቅረፍ ተችሏል።
የምዝገባ ሽፋን ዕድገት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የከተማዋን የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ሽፋን 62.55% ማድረስ ተችሏል።
የዲጂታል መታወቂያ አቅርቦት ከአጠቃላይ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ከ4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የነዋሪነት ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት ተሰጥቷል
ፋይዳ መታወቂያ ሥርጭት በተመለከተ ፤ 8.6 ሚሊዮን ዜጎች ብሔራዊ የፋይዳ መታወቂያ እንዲወስዱ ተደርጓል።የልደት ምዝገባ አፈጻጸም ስንመለከት በበጀት ዓመቱ 109,891 ወቅታዊ የልደት ምዝገባዎችን በማከናወን ዕቅዱን 94% ማሳካት ተችሏል። በአጠቃላይ አምስቱ የኩነት ዓይነቶች (ልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ሞት እና ጉዲፈቻ) በጥምር 500,363 ምዝገባዎች ተከናውነዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
የበጎ ፈቃድና ሰው ተኮር ስራዎችን በተመለከተ
አዲስ አበባን የሰው ተኮር ስራዎችና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማዕከል ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቧል። ባለፉት አምስት ዓመታት የአቅመ ደካሞችን ቤት በመገንባት፣ ማዕድ በማጋራት፣ በምገባ እና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች ከ92 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት ማሰባሰብ ተችሏል። በዚህም ከ6 ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ሆነዋል።
በፕሮግራሙ ከ46 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶች ተገንብተዋል፤ 30 የምገባ ማዕከላት ተደራጅተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። በየዓመቱም እስከ 600 ሺህ ዜጎች ማዕድ ተጋርተዋል። በበጀት ዓመቱ ብቻ በገንዘብ፣ በዓይነትና በጉልበት 28.5 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ 1.8 ሚሊዮን ህዝብን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።የበጎ ፈቃድና ሰው ተኮር ስራዎችን በተመለከተ
አዲስ አበባን የሰው ተኮር ስራዎችና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማዕከል ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቧል። ባለፉት አምስት ዓመታት የአቅመ ደካሞችን ቤት በመገንባት፣ ማዕድ በማጋራት፣ በምገባ እና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች ከ92 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት ማሰባሰብ ተችሏል። በዚህም ከ6 ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ሆነዋል።
በፕሮግራሙ ከ46, ሺህ 411 በላይ የመኖሪያ ቤት ተገንብቷል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
ወጣቶችና ስፖርትን በተመለከተ
በመዲናዋ በ114 የወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት አገልግሎቶችን እንዲሰጡና አገልግሎቶች እንዲያሻሽሉ በማድረግ ወጣቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል።
በባለፉት አምስት አመታት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ቁጥራቸው 495 የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት 2,581 ማድረስ ተችሏል፡፡
ከ84,678 በላይ ታዳጊ ወጣቶች በከተማ አቀፍ ስልጠና ልማት ፕሮግራም በማሰልጠን 723 ተተኪና ምርጥ ስፖርተኞችን ለብሄራዊ ቡድን እና ለክለብ የማፍራት ስራ ተሰርቷል።
በሌላ በኩል ከ211,213 በላይ ወጣቶች የማይንድሴትና በ225,222 በላይ ወጣቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና እንዲሰለጥኑ ለማድረግ ተችሏል ያሉ ሲሆን በበጀት አመቱም ደረጃቸውን የጠበቁ 91 የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራዎችን፣ ስፖርት ፓርክን፣ ለብሔራዊ ጀግኖች ለሆኑ አትሌቶቻችን የአክብሮት አውልት ማቆምን ጨምሮ ብዙ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡
በተጨማሪም በየደረጃው የማህበረሰብ አቀፍ ስፖርትን በትምህርት ቤት፤ በመኖሪያ እና መዝናኛ ቦታዎች እንዲሁም በስራ ቦታዎች በማስፋፋት ሁሉንም ዜጎች በአካል እና በአእምሮ ጎልብተው ጤናማ እና አምራች እንዲሆኑ እና ማህበራዊ መስተጋብርን ለማጠናከር ያለማቋረጥ እየተሰራ ሲሆን በአገራችንም ሆነ በከተማ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ 5 አለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ ከተማችንን የአለም አቀፍ ውድድሮች መዳረሻ ማድረግ ተተችሏ::
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
ባህላዊ፣ ኪነ ጥበባዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሮአዊ ሀብቶችን መጠበቅና ማሳደግ በሚመለከት
ብሔራዊ አንድነትና የጋራ ትርክት ከመገንባት፣የሀገርን መልካም ገጽታ ለመገንባት፣ የሕዝቦችን አንድነት፣ አብሮነትና ወንድማማችነት የሚያጠናክሩ በርካታ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።
የባህልና እሴቶች ጥበቃ ስራ ጋር ተያይዞ ፡ ባህላዊ እሴቶችንና አገር በቀል ዕውቀቶችን ለማሳደግ፣ እንዲሁም ጎጂ ልማዶችንና መጤ ባህሎችን ለመከላከል 6 የቶክሾው ውይይቶችና በርካታ የስልጠና ስርፀቶች ተካሂደዋል።
የጀግኖች መታሰቢያ ስራችን በተመለከተ፡ በሀገርና በትውልድ ግንባታ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የኪነጥበብ ሰዎችና የሀገር ኩራት ለሆኑ አትሌቶች የክብር ሐውልት ቆሟል።
የኪነጥበብ መሠረተ ልማት፡ ቲያትርና ሲኒማን ለማሳደግ ዘመናዊ መሣሪያዎች የተሟሉላቸው እጅግ ዘመናዊ ኮምፕሌክሶች ተገንብተዋል። ጥበብን ለሕዝብ ከማቅረብ አኳያ፡ ኪነጥበብ ወደ ሕዝብ ይበልጥ እንዲጠጋ ለማድረግ በርካታ አንፊ ቲያትሮችና የሕዝብ ፕላዛዎች በሰፊው ተገንብተው ለአገልግሎት በቅተዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
የኑሮ ውድነትን በተመለከተ
የኅብረተሰቡን የኑሮ ጫና ለማቃለልና የምርት አቅርቦትን ለማሳደግ 259 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ተስፋፍተዋል።
በተጨማሪም በ15.9 ቢሊዮን ብር ወጪ መጋዘኖችን፣ የጅምላና የችርቻሮ ሱቆችን ያካተቱ 7 ዘመናዊ የግብርና ምርቶች መሸጫ ማዕከላት በከተማዋ መግቢያዎች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል። ቢሮክራሲን በመቀነስም ከ270 ሺህ በላይ አዳዲስ ነጋዴዎች ወደ ንግድ ሥርዓቱ እንዲቀላቀሉ ተደርጓል።
በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ጫና ለማቃለል ለትራንስፖርት፣ ለጤና መድህን፣ ለተማሪዎች ምገባና ለዳቦ ምርት 18.2 ቢሊዮን ብር የመንግስት ድጎማ ተደርጓል።
በተጨማሪም ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ መነሻ ካፒታል ያለው የንግድ ኮርፖሬሽን ሲቋቋም፤ መሠረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች በተለይም ስኳር እና የምግብ ዘይት በፍትሃዊነት እንዲሰራጩ ተከናውኗል። አቅርቦትን ለማጠናከርም ለ11 ዩኒየኖች የ825 ሚሊዮን ብር የተዘዋዋሪ ብድር ፈንድ ተሰጥቷል።
ህጋዊነትን ለማረጋገጥ በተደረገ ቁጥጥር ህገ-ወጥ በነበሩ 24,568 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ሲወሰድ፣ 20,617ቱ ወደ ህጋዊነት ተመልሰዋል።
በሌላ በኩል አዲስ አበባን አምራች ለማድረግ በተሰራው የከተማ ግብርና እና የሌማት ትሩፋት ስራ 1.2 ሚሊዮን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ሆነዋል። እንዲሁም ከይዞታቸው ለተፈናቀሉ አርሶ አደሮች 19,507 የይዞታ ማረጋገጫ ካርታዎች በመስጠትና ወደ ኢንቨስትመንት እንዲገቡ በማድረግ ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ ተከናውኗል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
የደብረ ማርቆስና የአካባቢው ሕዝብ ለዓመታት በጉጉት ሲጠብቀው የነበረውና ለ30 ዓመታት ያህል ተቋርጦ የነበረው ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት የአውሮፕላን ማረፊያ፤ በዘመናዊ መልክ ተሻሽሎና ደረጃው ከፍ ብሎ ተገንብቶ ዛሬ በይፋ አስመርቀናል።
በ2,400 ሜትር ርዝመትና 30 ሜትር ስፋት ላይ የተገነባው እንደ Q400 እና B737 ያሉ ግዙፍ የሕዝብና የጭነት አውሮፕላኖችን ማሳረፍ የሚያስችል ከፍተኛ ዐቅምም ፈጥሯል። ይህ አውሮፕላን ማረፊያ ሥራ መጀመሩ የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት ለአካባቢው እና ለመላው ሀገራችን የኢኮኖሚ ዕድገት አዲስ ምዕራፍ ይከፍታል።
ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር፤ የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስና የጀመርናቸውን ሜጋ ፕሮጀክቶች በጥራትና በፍጥነት አጠናቆ ለምርቃት ለማብቃት ያለንን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየን እንቀጥላለን።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
+9
ዛሬ 3ኛ ዙር የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ማጠቃለያ ጉባኤ ማካሄድ ጀምረናል።
ምክር ቤቱ ያጸደቃቸው አጀንዳዎች:-
1. የምክር ቤቱን 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
2. የከተማ አስተዳደሩን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
3. የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
4. የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት 2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም እና የኦዲት ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
5. የአዲስ አበባ ከተማ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቶች የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
6. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2019 በጀት አዋጅ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
7. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ይዞታ ማስለቀቅና ካሳ ጉዳዮች ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ እንደገና ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
ከህፃናት እንክብካቤ በተመለከተ:-
ጤናን በሕክምና ብቻ ሳይሆን በመከላከል ጭምር ለመጠበቅ በተቀመጠው ፖሊሲ መሠረት፤ አዲስ አበባን ፅዱ፣ አረንጓዴ እና ለህጻናት ምቹ ለማድረግ ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል። ከተማዋን ህጻናትን ለማሳደግ ምርጥ የአፍሪካ ከተማ ለማድረግ በተነደፈው የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም 1.3 ሚሊዮን ህጻናትን (በተለይም 330 ሺህ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን) ተጠቃሚ ያደረጉ አንኳር ተግባራት ተተግብረዋል፡-
የምክር እና የክትትል አገልግሎት፡- 5,000 ሰራተኞችን በማሰማራት ለወላጆችና አሳዳጊዎች በየ15 ቀኑ የቤት ለቤት የምክር አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጓል። በ95 ጤና ጣቢያዎችም ለህጻናት የዕድገት ክትትል የተደረገ ሲሆን፤ የዕድገት ውስንነት ለታየባቸው 1,362 ህጻናት የሪፌራል ህክምና አገልግሎት ተመቻችቷል።
የምግብ እና የትምህርት ዝግጁነት ድጋፍ፡- ለ15 ሺህ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው እናቶችና ህጻናት ተከታታይ የአልሚ ምግብ ድጋፍ ተደርጓል። በተጨማሪም ከ50 በመቶ በታች የነበረው የህፃናት የመደበኛ ትምህርት ዝግጁነት፣ በጨዋታ መልክ እንዲማሩ በተሰራው ስራ ወደ 99 በመቶ ማሳደግ ተችሏል።
የመሰረተ ልማት ዝርጋታ፡- የምግብና የንፅህና መጠበቂያ አገልግሎትን ያካተቱ 1,155 የህጻናት ማቆያዎች የተገነቡ ሲሆን፤ ህፃናት ቦርቀው እንዲያድጉ የሚያስችሉ 5,003 የመጫወቻ ቦታዎች ለምተው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።
በጥቅሉ በእነዚህ የተቀናጁ ስራዎች የህጻናት የዕድገት ሁኔታ ላይ ከፍተኛ መሻሻል የታየ ሲሆን፤ ቀደም ሲል 13 በመቶ የነበረው የዕድገት ውስንነት ምጣኔ በአራት በመቶ በመሻሻል ወደ 9.45 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+7
ከተማችንን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግና የከተማ ዲፕሎማሲ ስራዎች በተመለከተ
የጎብኚዎች ቁጥር መናር፡ የአገር ውስጥ ጎብኚዎች ቁጥር ከ4.1 ሚሊዮን ወደ 10.5 ሚሊዮን፤ የውጭ ቱሪስቶች ቁጥር ደግሞ ከ123,489 ወደ 1.2 ሚሊዮን አድጓል።
የገቢ ዕድገት፡ ከውጭ ቱሪዝም የሚገኘው ገቢ ከ5.63 ቢሊዮን ብር ወደ 242.6 ቢሊዮን ብር ያደገ ሲሆን፣ ከአገር ውስጥ ቱሪስቶች ደግሞ 63.3 ቢሊዮን ብር ወደ ከተማዋ ኢኮኖሚ ፈሷል።
የኮንፈረንስ ቱሪዝም፡ በበጀት ዓመቱ 221 ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ኮንፈረንሶች በስኬት ተስተናግደዋል፤ መዳረሻዎችንም እንዲጎበኙ ተደርጓል።
ከተማ ዲፕሎማሲ እና ዓለም አቀፍ ትስስር፤ የእህትማማች ከተሞች ትስስር፡ ከተማዋ ከዓለም አቀፍ ከተሞች ጋር ያላት ትስስር ከነበረበት 20 ወደ 30 ከተሞች ከፍ ብሏል።
ሽልማቶችና እውቅናዎች (Smart City)
👉 የሴኡል ስማርት ከተማ ሽልማት (2024)
👉የአፍሪካ ምርጥ ስማርት ከተማ
👉ሽልማት (ናይሮቢ፣ 2024)
👉ለቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት የ“C40
👉ከተሞች የብሉምበርግ ሽልማት” (ቦነስ አይረስ)
👉በሪዮ ዴጄኔሪዮ የተሰጠ የምገባ ፕሮግራም ሽልማት
👉በመንገድ ደኅንነትና ፍጥነት ማስተዳደር ዘርፍ የዓለም አቀፍ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ መሆን።
ዓለም አቀፍ አባልነት፡ አዲስ አበባ የብሉምበርግ ፊላንትሮፒስ የከተሞች ጥምረት አባል ለመሆን በቅታለች።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
ከተማ ማደስ በተመለከተ
የከተማዋን ነዋሪዎች አስከፊ አኗኗር በማሻሻል ጤናማና ለመኖር ምቹ አካባቢን ለመፍጠር በተከናወኑ የከተማ ማደስ ስራዎች ከፍተኛ ለውጥ ተመዝግቧል።
16 ኮሪደሮችና 8 ወንዞችን ያካተተ 6 ሺህ ሄክታር የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ ልማት ተከናውኗል። በውስጡም 2 ሺህ ሄክታር አረንጓዴ ሽፋን፣ 24 የውሃ ግድቦችና ሰው ሰራሽ ሀይቆች ይገኙበታል። በሶስት ዙር በተከናወነው የኮሪደር ልማት 426 ኪ.ሜ የእግረኛ፣ 223 ኪ.ሜ የተሽከርካሪ እና 255 ኪ.ሜ የሳይክል መንገዶች እንዲሁም የፍሳሽና ጎርፍ ማስወገጃዎች ተገንብተዋል። የተንጠለጠሉ የመብራትና ቴሌኮም መስመሮችን መሬት ውስጥ በመቅበርና በስማርት ፖል በመቀየር ከተማዋን ውብ ማድረግ ተችሏል።
በተጨማሪም 205 ፕላዛዎች፣ 162 የስፖርት ሜዳዎች፣ ፓርኮችና 233 የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች ተገንብተዋል።
አሮጌ የጭቃ ቤቶችን በመቀየር ከ26 ሺህ በላይ አዳዲስ መኖሪያ ቤቶች ተገንብተው ቀርበዋል። ለተነሺዎችም ከ40 ቢሊዮን ብር በላይ ካሳ እና 400 ሄክታር ምትክ መሬት ተሰጥቷል። በጥገኝነትና በደባልነት ይኖሩ የነበሩ ከ3,700 በላይ ነዋሪዎች የቤት ተጠቃሚ ሲሆኑ፤ ከ4 ሺህ በላይ ሼዶችና 5 ሺህ ሱቆች ለስራ ዕድል ፈጠራ ውለዋል።
ይህ “አይቻልም” የተባለን እሳቤ የቀየረና በሀገር በቀል አቅም የተከናወነ ፕሮጀክት፤ የአመራሩንና የሰራተኛውን የ24/7 የስራ ባህል ያሳደገ ነው። አጠቃላይ የልማት ስራው በርካታ የስራ ዕድሎችን የፈጠረ፣ በመቶ ሺዎች ለሚቆጠሩ ነዋሪዎች ጤናማ የመኖሪያ አካባቢን ያስገኘ እና የኮንፈረንስ ቱሪዝምን በማሳደግ የከተማዋን ኢኮኖሚ ከፍ ያደረገ መሆኑ ተረጋግጧል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+7
ፅዳት በተመለከተ
በደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ከ5 ሚሊዮን ቶን በላይ ቆሻሻ ተሰብስቧል። የቆሻሻ አያያዝን ከመጣል ባለፈ ወደ 484 ሺህ ቶን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል፣ ኮምፖስት በማምረት እና ከ910 ሺህ ቶን በላይ ለኃይል ማመንጫ በማቅረብ ቆሻሻን ወደ ሀብትነት መቀየር ተችሏል። በዚህም አዲስ አበባ ከአፍሪካ 10 ፅዱ ከተሞች አንዷ በመሆን ዓለም አቀፍ እውቅናን አግኝታለች።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
ከጤና አገልግሎት በተመለከተ:-
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት ከተማዋን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ በሰራው ስራ፤ የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ከእጥፍ በላይ በማደጉ የእናቶችና የጨቅላ ህፃናት ሞት ምጣኔን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ መቻሉን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሪፖርታቸው ገልጸዋል።
በመሰረተ ልማት ረገድ፤ አዳዲስ እና ግዙፍ ሆስፒታሎች (እንደ አበበች ጎበና፣ ላፍቶ፣ ኮልፌ እና ገላን) እንዲሁም 9 አዳዲስ ጤና ጣቢያዎች ተገንብተዋል። የሆስፒታል አልጋዎች አቅም ከ1,384 ወደ 4,195 ያደገ ሲሆን (ይህም ባለፉት 100 ዓመታት ከተመዘገበው በእጥፍ ይበልጣል)፣ የአምቡላንስ ቁጥርም ወደ 109 ከፍ ብሏል። ሆስፒታሎቹም በዘመናዊ መሣሪያዎች ማለትም በMRI እና ሲቲ ስካን ተደራጅተዋል።
በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን 2.7 ሚሊዮን ነዋሪዎች የታቀፉ ሲሆን፤ ከተማ አስተዳደሩ በየዓመቱ ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ያደርጋል። የወረቀት አልባ የጤና መረጃ ስርዓትም (EMR) በ68 ተቋማት ተተግብሯል። በተጨማሪም ለማህበራዊ ፍትህ ሲባል ለ200 ታካሚዎች በዓመት 100 ሚሊዮን ብር በመመደብ ነፃ የኩላሊት እጥበት አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል።
በሌላ በኩል የህዝብን ጤና ለመጠበቅ በተደረገ ጥብቅ ቁጥጥር፤ 193 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው 350 ሺህ ኪሎ ግራም የምግብ ምርቶች፣ 42 ሺህ ሊትር መጠጦች፣ እና 21 ሺህ ኪሎ ግራም ጊዜ ያለፈባቸው መድሃኒቶች እንዲወገዱ መደረጉን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል።
+3
ሌብነትና ብልሹ አሰራርን ከማስቀረት አንፃር የተሰሩ ስራዎች
ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን በተጨባጭ ለመታገል በተያዘው ቁርጠኝነትና በጥፋት ላይ ተሰማርተው በተገኙ በአጠቃላይ 5,857 አካላት ላይ ( 79 ሹመኛ አመራሮች፣ 213 የሜሪት አመራሮች፣ 5,430 ባለሙያዎች እና 135 ተገልጋዮች ) እንደ ጥፋታቸው ክብደት ከማስጠንቀቂያ እስከ ስንብትና በህግ ተጠያቂ ማድረግ የሚደርሱ እርምጃዎች ተወስደዋል።
የረቡዕና አርብ የባለጉዳይ ቀናት ላይ በተደረገ ምልከታ በአማካይ 90% አመራርና፣ ሰራተኞች በስራ ገበታ በመገኘት አገልግሎት እየሰጡ ነው። በዚህም በበጀት አመቱ አገልግሎት ከጠየቁ ተገልጋዮች ከ87% በላይ አገልግሎት ማግኘት ችለዋል፤
አገልግሎትን ግልፅና ተጠያቂነት የሰፈነበት ለማድረግ በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ “ አገልጋዩ ” የሚል አመራሩ ከሕዝብ ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጥበት የቀጥታ ስርጭትና “ ዋርካ ” የሚል አገልጋዩና ሕዝቡ በአካል ተገናኝቶ ፊት ለፊት የሚጠያየቅበት ኘሮግራም ተግባራዊ በማድረግ 89 % የሚሆኑት ችግሮች መፍታት ተችሏል።
የመንግስት ሰራተኞችን የኑሮ ጫና ከግንዛቤ ያስገባ ሁለት ጊዜ የደሞዝ ጭማሪ የተደረገ ሲሆን፣ በተጨማሪም በቢሊዮን በጀት በመመደብ የሰራተኞች ካፍቴሪያ ድጐማ፣ በየተቋማት የሸማቾች ሱቅና የህፃናት ማቆያዎችን ከነሙሉ ወጪው አደራጅተን አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
