የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church
Ir al canal en Telegram
1 070
Suscriptores
+124 horas
+177 días
+3830 días
Archivo de publicaciones
የነገ ሟች የዛሬን ሟች ይቀብራልከ150 ዓመታት በኋላ ዛሬ በሕይወት ካለነው ሰዎች አንዳችንም በሕይወት አንገኝም። ዛሬ ላይ ከምንታገልላቸው ነገሮች 70 በመቶ የሚሆኑት ከ150 ዓመታት በኋላ አንዳቸውም ለምልክት እንኳ አይገኙም ፈፅመው ይጠፋሉ ይረሳሉ። እስኪ ወደኋላ 150 ዓመታት እንሂድ ወቅቱ 1870 ገደማ ነው የሚሆነው ያኔ የሰው ልጅ እንደ ዕቃ በአደባባይ ተደርድሮ የሚሸጥበት ወቅት ነበር በወቅቱ ብርቅ የነበረውን መስታወት ለማግኘት ሲሉ የገዛ ዘመዶቻቸውን የሸጡ ሰዎች የታሉ? መስታወትንስ ዛሬ እንደ ሀብት የሚያስበው ማነው? ጨው ወይም ጌጥ ወይም ሌላ ነገር ለማግኘት ሲሉ የተሻሻጡ ብዙ ሰዎች ነበሩ። ዛሬ ላይ እነዚያ ሰዎች የሞቱላቸው፣የገደሉላቸው፣የተካካዱባቸው፣የተሻሻጡላቸው አብዛኛው ነገሮች ይሄ ነው ሚባል የረባ ዋጋ ያላቸው ነገሮች አይደሉም።በጊዜው ግን ለሰው ልጅ የሞትና የህይወት ልዩነት ነበሩ።የሰው ልጅ በየጊዜው የሚታገልላቸው አብዛኛው ነገሮች ዛሬ ላይ ዞር ተብለው ሲታዩ በጣም የሚያስቁ ናቸው። ምንም ሆነ ምንም ምድራዊ ነገር ለዘላለም የሚኖር አይደለም መክ ምዕራፍ 1:-8-11 8፤ነገር ሁሉ ያደክማል ሰው ይናገረው ዘንድ አይችልም፤ ዓይን ከማየት አይጠግብም፥ ጆሮም ከመስማት አይሞላም። 9፤የሆነው ነገር እርሱ የሚሆን ነው፥ የተደረገውም ነገር እርሱ የሚደረግ ነው፤ ከፀሐይም በታች አዲስ ነገር የለም። 10፤ማንም። እነሆ፥ ይህ ነገር አዲስ ነው ይል ዘንድ ይችላልን? እርሱ ከእኛ በፊት በነበሩት ዘመናት ተደርጎአል። 11፤ለፊተኞቹ ነገሮች መታሰቢያ የላቸውም፤ ከኋለኞቹም ነገሮች ከእነርሱ በኋላ በሚነሡት ሰዎች ዘንድ መታሰቢያ አይገኝላቸውም። በዚህ ምድር ላይ የምንጋደልለት ነገር ፣እርስ በእርሳችን የምንወነጃጀልበት ነገር ፣ ወንድሞቻችንን ለማጥፋት ስሙን ለማጠልሸት ከጀርባ የምናሴርበት ነገር፣በሐሰት የምንመሰክርበት ነገር፣በውሸት እና ተንኮል አንዳችን ሌላችንን ለመጣል የምናደባው ነገር፣ለወንድም እህቶቻችን መሰናከያ በምንሆንበት ነገር ሁሉ የሰው ልጅ ጥቅሙ ምንድነው? መክብብ 2:-22-23 22፤ ከፀሐይ በታች በደከመበት ድካም ሁሉና በልቡ አሳብ የሰው ጥቅም ምንድር ነው? 23፤ ዘመኑ ሁሉ ኀዘን፥ ጥረትም ትካዜ ነው፤ ልቡም በሌሊት አይተኛም፤ ይህም ደግሞ ከንቱ ነው። መክብብ 3:-12 " ሰው ደስ ከሚለውና በሕይወቱ ሳለ መልካምን ነገር ከሚያደርግ በቀር መልካም ነገር እንደሌለ አወቅሁ። ፍቅር ይግዛን፣መጠላለፍ ከጀርባ መወጋጋት መቀናናት መፎካከር ይቅርብን። ህይወት ከማንም ጋር የምናደርገው ፉክክር አይደለችም። ቀደምንም ዘገየንም መጨረሻችን መቃብር ነው።ለዚች ምድር ዘላለማዊ ሳይሆን ተረኛ ነዋሪ ነን ነገ የምናልፍ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ 15:-50-58 50፤ ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እላለሁ። ሥጋና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊወርሱ አይችሉም፥ የሚበሰብሰውም የማይበሰብሰውን አይወርስም። 51-52፤ እነሆ፥ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበት ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን። 53፤ ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና። 54፤ ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ። ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል። 55፤ ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ? 56፤ የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው፤ 57፤ ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን። 58፤ ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ። ፨ ስለዚህ ወገኖቼ ትርፋችን ሰማይ ነው በክርስትና ጉዟችን የህይወት መውጫ የሆነችውን ልባችንን አጥብቀን እንጠብቅ። የደከምንለት ክርስትናችን ለሰማይ ዜግነት ያብቃን ምድራዊ ህይወትን ተስፋ አናድርግ " በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:19) ጌታ በነገር ሁሉ ይርዳን!!!
የተጠማ ሁሉ ይምጣና ይጠጣ" የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?" 1ኛ ቆሮ 3:16 ከሐምሌ 13 እስከ ሐምሌ 19 ፨ዘወትር ከእሁድ እስከ አርብ ከ 12:00 - 1:30 ቅዳሜ ሙሉ ቀን ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!
እውነተኛውን ሕይወት መያዝያዕቆብ የአስመሳይነት ምሳሌ ዘፍጥረት 27:19 ያዕቆብም አባቱን አለው፡— የበኵር ልጅህ እኔ ዔሳው ነኝ፤ እንዳዘዝኽኝ አደረግሁ፤ ነፍስህ ትባርከኝ ዘንድ ቀና በልና ተቀመጥ፥ ካደንሁትም ብላ። ዘፍጥረት 27:1-4 ''ይስሐቅ ሸምግሎ ዓይኖቹ ከማየት በፈዘዙ ጊዜ ታላቁን ልጁን ዔሳውን ጠርቶ፡— ልጄ ሆይ አለው፤ እርሱም፡— እነሆ አለሁ፡ አለው። ይስሐቅ ሸምግሎ ዓይኖቹ ከማየት በፈዘዙ ጊዜ ታላቁን ልጁን ዔሳውን ጠርቶ፡— ልጄ ሆይ አለው፤ እርሱም፡— እነሆ አለሁ፡ አለው። እርሱም አለው፡— እነሆ እኔ አረጀሁ፥ የምሞትበትን ቀን አላውቅም። አሁንም ማደኛህን የፍላጻህን አፎትና ቀስትህን ውሰድ፥ ወደ ምድረ በዳም ውጣ፥ አደንም አድንልኝ፤ ሳልሞትም ነፍሴ እንድትባርክህ የጣፈጠ መብል እኔ እንደምወደው አዘጋጅተህ እበላ ዘንድ አምጣልኝ።'' ፨ይስሐቅ ታላቁን ልጁን ኤሳውን ነበር ለመባረክ ያሰበው። ያዕቆብ ግን የአባቱን አይን መፍዘዝ እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ እድሉን ለመጠቀም ፈለገ። የበግ ጠጉር በሰውነቱ ላይ በማጣበቅ እንደ ኤሳው ጠጉራም ለመምሰል ሞከረ። ፨ምግቡን ይዞ በአባቱ ፊት ቆሞ ስጠራው ከድምጹ የተነሳ ይስሐቅ ብጠራጠርም እንኳ ሰውነቱን ዳስሶ ሲያይ ግን ኤሳው እንደሆነ አመነ። ምግቡንም በልቶ ባረከው። ፨ነገር ግን ምንም እንኳ አባቱን ቢያጭበረብርም በሰማያት ሆኖ ሁሉን የሚመለከተውን ጌታ ሊያጭበረብር አይችልም ነበር። ፨ያዕቆብ ከዚህ ከማስመሰልና ከማጭበርበር ሕይወቱ የተነሳ ለሃያ (20) አመታት በስዴትና በባርነት በመጭበርበር ሕይወት ኖረ። ከምወዳት እናቱና ከአባቱም ተለይቶ ተሰደደ። ሞተው እንኳን ልቀብራቸው አልቻለም። የድካሙ ዋጋ 10 ጊዜ ተቀያየረበት የበረከቱም መንገድ ረዘመበት። ግን በመጨረሻ የውሸት የማስመሰል ሕይወት እንደማያዋጣው በተረዳ ጊዜ ሁሉን ወደ ፊት አሻግሮ ብቻውን ከእግዚአብሔር ጋር ትግል ገጠመ። እግዚአብሔርም ስሙን (ታሪኩን/አመለካከቱን/ ሕይወቱን) ቀየረለት። እውነተኛውን ሕይወት መኖር ሲጀምር እውነተኛውን መባረክ ተባረከ። በማጭበርበር ያገኘው በረከት አንገላታው በእውነተኛው ሕይወት ያገኘው በረከት አረጋጋው። እውነተኛውን ሕይወት መያዝ ይሁንልን። መልካም ሰንበት ምንጭ:- ውቅያኖስ መሰለች
የሀዘን መግለጫ 😭ሐምሌ 10,2017 ዓ.ም የቤተክርስቲያናችን አባል የሆኑት የአባታችን የአቶ አጋፋሪ ባለቤት ወ/ሮ አረሴ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ቤተክርስቲያናችን በእናታችን ሞት ጥልቅ ሀዘን የተሰማት መሆኗን እየገለፀች ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ትመኛለች። የቀብር ስነ ስርዓቱ ነገ አርብ ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ በሚሽን መካነ መቃብር ይፈፀማል። አድራሻ :- 05 ሰፈር በሴንቴራል ሆቴል ጀርባ
እውነተኛውን ሕይወት መያዝየከተማችን ቅብ እና የሕይወታችን መመሳሰል ውዶች ሰላማችሁ ይብዛ። ሰሞኑን በከተማችን ውስጥ ስመላለስ ግድግዳዎች እና በሮች ቀለም ሲቀቡ አያለሁ። ይህ ቅብ ከተማውን አሳምሮታል። ምንም እንኳን አንዳንዶቹ ያለ እቅዳቸው ያስቀቡ ቢኖሩም ሁሉም በመደዳው መቀባቱ ለከተማዋ አንዳች ውበት ጨምሮላታል። ይሄንን ሐሳብ ማንሳቴ ግን ዋና አላማዬ የከተማዋን መቀባት ልነግራችሁ አይደለም። ይልቅ አንድ ነገር ከሕይወታችን ጋር ተመሳስሎ አግኝቸዋለሁ። የታዘብኩትን ነገር ልንገራችሁ። አንዳንድ ቤቶች ቀለም ሲቀቡ ትክክለኛ ጥንካሬ እና ተስተካክሎ የተሰራ ግድግዳ አላቸው። መቀባታቸው እንዲያምሩ አድርጓቸዋል። ሌሎቹ ቤቶችና አጥሮች ግን ቀለም ይቀባ ስለተባለ ብቻ የተቀቡ ነበሩ። የተቦዳደሰ፣ የሻከረ፣ ያዘነበለ፣ የፈረሰ... ብቻ ብዙ ብዙ ጉድ ያለው ግድግዳ እና በር ጭምር ተቀብቷል። ይሄንን ስመለከተ በውስጤ መንፈስ ቅዱስ አንድ ግሳጼ ተሰጥቶኛል። ማቴዎስ 23 25 እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በውስጡ ቅሚያና ስስት ሞልቶ ሳለ የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ስለምታጠሩ፥ ወዮላችሁ። 26 አንተ ዕውር ፈሪሳዊ፥ ውጭው ደግሞ ጥሩ እንዲሆን አስቀድመህ የጽዋውንና የወጭቱን ውስጡን አጥራ። 27 እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በውጭ አምረው የሚታዩ በውስጡ ግን የሙታን አጥንት ርኩሰትም ሁሉ የተሞሉ በኖራ የተለሰኑ መቃብሮችን ስለምትመስሉ፥ ወዮላችሁ። 28 እንዲሁ እናንተ ደግሞ በውጭ ለሰው እንደ ጻድቃን ትታያላችሁ፥ በውስጣችሁ ግን ግብዝነትና ዓመፀኝነት ሞልቶባችኋል። ሕይወታችን ውስጡ የፈረሰ፣ የተቦረቦረ፣ የሻከረ እና በብዙ መልኩ ያልተስተካከለ ሆኖ ትልቁ ጥረታችን ከላይ አምሮና ደምቆ መታየት ነው። ደምቆ መታየቱ በራሱ ችግር የለውም። ነገር ግን እውነተኛው መድመቅ የሚመጣው ከውስጥ ስሆን ነው። ውስጣችን ሲለወጥ ዉጪያችንን ለመለወጥ አንቸገርም። እንዲሁ ይለወጣል። ዛሬ እግዚአብሔር አምላካችንም የሚያደርግልን ጥሪ ሕይወታችን ከውስጥ ከሥር ከመሠረቱ እንድለወጥ ነው። እውነተኛውን ሕይወት ማስመሰል ሳይሆን እውነተኛውን ሕይወት እንድንኖር ነው። እውነተኛውን ሕይወት መያዝ ይሁንልን። ምንጭ:- ውቅያኖስ መሰለች
መርዶ
ቀን ሐምሌ 07,2017
የቤተክርስቲያናችን አባል እና አገልጋይ የሆነችው እህታችን ወ/ሮ አልማዝ ሾንጋ የእህቷን መርዶ ይዛ ነገ ማክሰኞ ሐምሌ 08,2017 ከሰዓት ወደ ቤቷ የምትመለስ በመሆኑ የቤተክርስቲያናችን ምዕመናን እህታችንን እና ቤተሰቦቿን በመድረስ እንድታፅናኑ እያሳሰብን ቤተክርስቲያንም ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ የማፅናኛ ፕሮግራም ስለሚኖር የቤ/ያን አባላት በሙሉ እንድትገኙ እናስታውቃለን።
አድራሻ. 04 ቀበሌ
የከነዓናዊቷ ሴት ጸሎት
ስለ እምነታቸው ታላቅነት ጌታችን ኢየሱስ ከመሰከረላቸው ጥቂት ሰዎች መካከል ለልጇ ፈውስን የለመነችው ከነዓናዊቷ ሴት አንዷ ናት። ልጇ በጋኔን ክፉኛ ትሰቃይ ነበርና ጌታችን ኢየሱስ ከዚህ መከራ እንዲገላግላት ጥያቄዋን በታላቅ መቃተት አቀረበች። ከዚህች ሴት ጸሎትና እምነት የሚከተሉት ሦስት ወሳኝ ነጥቦች ልብ እንበል።
1 በእምነት ለመጸለይ ጌታን ማወቅ ያስፈልጋል።
ይህቺ ሴት ምንም እንኳን ከነዓናዊት ብትሆንም፣ ጌታችንን ግን “የዳዊት ልጅ” ብላ ጠራችው። ይህም መሲህነቱን መቀበሏን፣ መለኮታዊ ማንነቱንና ችሎታውንም መረዳቷን ጠቋሚ ነበር። እኛም በእምነት ለመጸለይ የምንችለው የአምላካችንን ማንነት ስንረዳና የችሎታውንም ታላቅነት ስናስተውል ነው።
2 በእምነት መጸለይ ጌታን በትእግስት መጠበቅን ይጠይቃል።
ምንም እንኳን ይህቺ ከነዓናዊት ሴት ድምጿን ጮኽ አድርጋ ጥያቄዋን ብታቀርብም “ኢየሱስ ግን አንድም ቃል አልመለሰላትም” ነበር። ከዝምታው ርዝማኔና ከእርሷም ያለማቋረጥ ልመናዋን ማቅረብ የተነሳ ደቀ መዛሙርቱ ወደ ጌታ ቀርበው እንዲህ አሉት፦
“እየተከተለችን ትጮኻለችና ብታሰናብታትስ?” ብለው ጠየቁት።” ማቴ 15፡ 23
3 በእምነት መጸለይ ጌታን የሙጥኝ ማለትን ይጠይቃል።
ይህቺ ሴት ወደ ጌታ መጀመሪያ ላቀረበችው ጥያቄ መልስ ባላገኘች ጊዜ እንዲሁ ዝም ብላ አልነበረም የጠበቀቸው። ይልቁንም እምነቷ በጌታ ላይ ታላቅ ስለነበረ የሚከተሉትን ነገሮች አድርጋ ነበር፦
“እየተከተለች ትጮኽ ነበር” በአንድ ቦታ ቆማ ሳይሆን ጌታን እየተከተለች፣ በሹክሹክታ ሳይሆን በጩኸት ልመናዋን ማቅረብ ቀጠለች።
ዝም ብሏት የቆየው ጌታ "እኔ የተላኩት ለእስራኤል ቤት ነው” ባላት ጊዜ ከመራቅ ይልቅ እንዲያወም “እግሩ ላይ ወድቃ፣ ‘ጌታ ሆይ፤ ርዳኝ አለች።” ቁ. 25
በመጨረሻም ጌታችን እንደዚህች ሴት ያሉት ከአይሁድ ወገን ያልሆኑት እንደ ውሻ ይቆጠሩ ነበርና “የልጆችን እንጀራ ወስዶ ለውሾች መጣል አይገባም” ባላት ጊዜ፣ ጌታን የሙጡኝ ያለችው ይቺ ሴት እንዲህ ብላ መለሰች፦
“አዎን ጌታ ሆይ፤ ውሾችም እኮ ከጌታቸው ማእድ የወዳደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ” ማቴ 15፡ 27
ጌታም ይህንን የሙጥኝ የሚለውን እምነቷን አደነቀላት፤ ደግሞም ልጇን ፈወሰላት።
አባት ሆይ፣ እኛም አንተን በማወቅ፣ ልመናችን ወዲያው መልስ ባላማግኘቱ ተስፋ ባለመቁረጥ እንዲሁም አንተን የሙጥኝ ብለን እስከመጨረሻ በመታገስ ልትሰጠን የወደድኸውን መቀበል እንድንችል እርዳን። አሜን።
መልዓክ አለማየው እንደፃፈው
ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊነትንና እውቀትን ካጣች፨ከእምነት ጋር ግንኙነት በሌለው በሀይማኖታዊ ሥርዓትና ወግ ላይ ብቻ ያተኮረ ባዶ ተቋም ትሆናለች።በተጨማሪም ፨የዓላማ ማጣት: ምዕመኑን ከእግዚያብሔር ጋር የማገናኘት፣ መንፈሳዊነትን የማሳደግ አይን ማጣት ፨ባዶ ስርዓት:ከውስጥ መንፈሳዊ ለውጥ ይልቅ በተለምዶና በወግ ሥርዓት ላይ ትኩረት ማድረግ ፨ትርጉም ያጣ አምልኮ: ምዕመኑ አገልግሎት ተካፋይ ብቻ እንዲሆን ነገር ግን ለእምነት ያለውን ዓላማ በመሳት በከንቱ አምልኮ መሆን ፨ምዕመኑ እና ሌሎች ሰዎች ላይ ተፅዕኖ የማድረግ፤ ወደ መንፈሳዊ መንገድ የመምራት እና የማነቃቃት አቅም ማጣት ፨ደካማ የፀሎት ልምምድ እና ሕይወት ፨ውጫዊ ገጽታ ላይ ብቻ ማትኮር ፨እውነት ሲነገር በሀሰት መከላከል ፨በራስ ኋይል መመራት ፨ግላዊ መንፈሳዊ ዕድገትን ችላ ማለት ፨ተቀባይነትን ማጣት ፨መዛል ፨ ቂምና በቀል ፨መተማመንና አክብሮት ማጣት ፨ከእውነተኛ ምንጭ ምዕመኑን ማሸሽና ማላቀቅ ፨የተሳሳቱ ትርጉሞችና መረዳቶች:ቃሉን በቅጡ ያለመረዳት፣ መመሪያዎችንና መተዳደሪያዎችን በአግባቡ ያለመረዳት እና ያለማወቅ ትንቢተ ሆሴዕ 4:6 " ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ።
ማስታወሻእግዚአብሔር ሁላችንንም ከጥፋት መንገድ ይመልሰን በከንቱ ነገር ዘላለማዊውን እንዳናጣ ይጠብቀን።
ልዩ ማስታወቂያ ከታቦር ነፀብራቅ ጎዳና ፈላጊልዩ የክረምት ትምህርት ለልጅዎ ፨ዕድሜ - ከ 4 ዓመት እስከ 14 ዓመት ፨ትምህርት የሚሰጥበት ቦታ እና ቀን * ከሐምሌ 1 እስከ ሐምሌ 5 - ታቦር ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ * ከሐምሌ 7 እስከ ሐምሌ 25 - በአድቬንቲስት ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ፨የመመዝገቢያ ጊዜ - ከሰኔ 29 እስከ ሐምሌ 7 በታቦር ቤቸ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ እሁድ ቀን ፨ሰዓት - ከሰኞ እስከ ሐሙስ ዘወትር ከ 2:15 - 9:15 - አርብ ዘወትር ከ 2:15- 6:15
የጎዳና ፈላጊ ልይ$"_
Liyu ye kiremt timirt ke 4 amet eske 14 amet lalu bemulu
Timirtu yemisetew ke hamle 1 eske hamle 25 sihon ke hamle 1 - 5 be tabor adventist church, ke 7 - 25 be adventist timirt bet gibi yeminset bemehonu ke ke sene 29 - hamle 7 dires lijochachun enditasmezegibu enasasibalen
ዜና
ፓስተር ኤርተን ኮህለር በአሜሪካ ሴንት ሉዊስ ሚዙሪ እየተካሄደ በሚገኘው የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን 62ኛ ዓለም አቀፍ ጉባዔ (Seventh Day Adventist General Conference Session 2025) ላይ ቀጣዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ ዓለም አቀፍ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመርጠዋል።
ከምርጫው በኋላ ያደረጉትን ንግግር ቀጥሎ ባለው ማስፈንጠሪያ ላይ ያገኙታል።
https://youtu.be/t7Q7ICyCg4Y?si=jFjnTjv6Yk-UYOir
ጌታ ቤተ ክርስቲያናችንን እና ምድራችንን አብዝቶ ይባርክ!
መልካም ሰንበት!
ማስታወቂያ
"ዘጸአት" በተሰኘ ርዕስ 3ተኛ ሩብ ዓመት የሰንበት ትምህርት ነገ እንደምንጀምር የሚታወቅ ነው በመሆኑም እንደተለመደው ያለቀውን ሰንበት ትምህርት በማረሚያ ለሚገኙ እህት ወንድሞቻችን እንዲያጠኑ ለመስጠት ሁላችሁም ነገ ይዛችሁ እንድትመጡ በጌታ ፍቅር እናሳስባለን።
መልካም ሰንበት!!
የሀዘን መግለጫ
ሰኔ 23,2017 ዓ.ም
የቤተ ክርስቲያናችን አባል እና አገልጋይ የሆኑት የአቶ አዳነ ዲንጋሞ አባት ስላረፉ እና ቀብሩም ነገ ማክሰኞ (ሰኔ 24 / 2017 ዓ.ም) ስለሆነ የምትችሉ ሁሉ ቤተሰብን እንድታጽናኑ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።
ያዘኑትን ሁሉ ጌታ ያጽናናልን!
የቀብሩ ቦታ:- ከአለታ ጩኮ ወደ አለታ ወንዶ በሚወስደው መንገድ ላይ ጉሬ አድቬንቲስት ቤ/ክ ፊት ለፊት
አትመኝ፦ እንደ አዳም የዲያብሎስ ባሪያ ትሆናለህ፡፡
አትቅና፦ እንደ ቃየን ወንድምህን ትገላለህ፡፡
አትስከር፦ አዕምሮ አሳጥቶ የማይገባ ሥራ ትሠራለህ፡፡
ዓለምን አትመልከት፦ እንደ ሎጥ ሚስት የጨው ዐምድ ሆነህ ትቀራለህ
በአባቶች አትሳቅ፦ እንደ ካም ትረገማለህ፡፡
እልከኛ አትሁን፦ እንደ ፈርዖን ትሰጥማለህ፡፡
በሐሰት አትመስክር፦ እንደ ሐማ ባዘጋጀኸው ጉድጓድ ትገባለህ።
ትዕቢተኛ አትሁን፦ እንደ ሰናክሬም ትወድቃለህ፡፡
ክፉ ባልንጀራን አትያዝ፦ እንደ ሶምሶን በጠላት እጅ ትወድቃለህ፡፡
አትዘሙት፦ እንደ ሰሎሞን አምላክህን አስረስቶ ጣዖትን እንድታመልክ ያደርግሃል፡፡
ሥልጣንን አትውደድ፦ እንደ አቤሴሎም በአባትህ ላይ ትነሣለህ።
ገንዘብን አትውደድ፦ እንደ ይሁዳ ጌታህን ያስክድሃል፡፡
@Markengeta
መርዶ
ቀን ሰኔ 21,2017
የቤተክርስቲያናችን አባል እና አገልጋይ የሆነችው እህታችን ወ/ሮ ተናኘ ደገፉ(የዘማሪ ገነቱ ጋጋዶ ባለቤት) የእህቷን መርዶ ይዛ ነገ እሁድ ሰኔ 22,2017 በጠዋቱ ወደ ቤቷ የምትመለስ በመሆኑ የቤተክርስቲያናችን ምዕመናን እህታችንን እና ቤተሰቦቿን በመድረስ እንድታፅናኑ እያሳሰብን ቤተክርስቲያንም በእህታችን ላይ በደረሰው ሀዘን ጥልቅ ሀዘን የተሰማት መሆኑን እናሳውቃለን!!
