cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

𝑬𝒏𝒐𝒓 𝒎𝒖𝒔𝒍𝒊𝒎𝐬 𝒎𝒆𝒅𝒊𝒂

Publicaciones publicitarias
559
Suscriptores
Sin datos24 horas
-47 días
-1730 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

وَقَالَ الْمَلِكُ ائْتُونِي بِهِ أَسْتَخْلِصْهُ لِنَفْسِي ۖ فَلَمَّا كَلَّمَهُ قَالَ إِنَّكَ الْيَوْمَ لَدَيْنَا مَكِينٌ أَمِينٌ ንጉሡም «እርሱን አምጡልኝ ለራሴ ግለኛ አደርገዋለሁና» አለ፡፡ ባናገረውም ጊዜ «አንተ ዛሬ እኛ ዘንድ ባለሟል ታማኝ ነህ» አለው፡፡ قَالَ اجْعَلْنِي عَلَىٰ خَزَائِنِ الْأَرْضِ ۖ إِنِّي حَفِيظٌ عَلِيمٌ «በምድር ግምጃ ቤቶች ላይ (ሹም) አድርገኝ፡፡ እኔ ጠባቂ አዋቂ ነኝና» አለ፡፡ وَكَذَٰلِكَ مَكَّنَّا لِيُوسُفَ فِي الْأَرْضِ يَتَبَوَّأُ مِنْهَا حَيْثُ يَشَاءُ ۚ نُصِيبُ بِرَحْمَتِنَا مَن نَّشَاءُ ۖ وَلَا نُضِيعُ أَجْرَ الْمُحْسِنِينَ እንደዚሁም ለዩሱፍ በምድር ላይ ከእርሷ በፈለገው ስፍራ የሚሰፍር ሲሆን አስመቸነው፡፡ በችሮታችን የምንሻውን ሰው እንለያለን፡፡ የበጎ ሠሪዎችንም ዋጋ አናጠፋም፡፡ ሱረቱ ዩሱፍ 54-56 ወህኒ ቤት ውስጥ ከዩሱፍ ጋር  ሁለት ወጣቶች እንደነበሩ ታስታውሳለህ አይደል? ስለዩሱፍ የልብ ንፅህናና ፈሪሃ አላህነት ጥያቄ የለብንም። ብርሃናማ ሰው ነበር። ግን ደግሞ እርሱ በእስሩ ለተወሰኑ ዓመታት እንዲቆይ ተደርጎ ሁለቱ ወጣቶች ነፃ ተባሉ። የመጀመሪያው  አገልጋይ ለመሆን ወጣ ሌላኛው ደግሞ ለሞት ፍርድ ከእስር ተለቀቀ። ዩሱፍ ደግሞ ከረጅም ጊዜ በኋላ የግብፅ ንጉስ ለመሆን ከግድግዳው መሀል ተጠራ። ምን ልልህ ነው? "ስጦታውን ሊያበዛልህ ሲፈልግ አንዳንዴ መንገዱ ሊርቅህ፣ እግርህም ሊጎተት ይችላል። ጌታህ ልክ እንደዩሱፍ ዓለምህን እየሰራው ነው…  አንተ ግን ጥበቡ አልደረሰህም።" እያልኩህ ነው። اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وعلى آله وصحبه أجمعين በማያልቀው የጌታዬ የሁን ቃሉ መሻታችን የሚሞላበት ፣ የተጨነቁት ወንድሞቻችን ድልን የታመመ መዳንን የሞቱት ሸሂድነትን የሚወፈቁበት በሰለዋት በሱራህ አልካህፍ በዱዓእ የታጀበ ምርጥየ ጁምዓ ይሁንልን🖤🖤🖤
Mostrar todo...
👍 5
እኛ የዚያ ከረሃብ የተነሳ ሆዳቸው ላይ ድንጋይ ያሰሩት😥 ነብይ ህዝቦች ነን... የዛ የመልካም ስነምግባር ቁንጮ መልክተኛ  ህዝቦች ! የዚያ ህዝቦቹ ናፍቀውት  ያነባው  ረሱል ህዝቦች ያ በመለየቱ የቴምር ዛፍ የተንሰቀሰቀለት ታላቅ ሰው ፣ አይደለም የሰው ደም ዉሃ እንኳን ያለ አግባብ ሲፈስ የሚቆጡት ነቢይ ህዝቦች ነን...ተወዳጅ በሆኑት ነብያች ሰ.ዐ.ወ ላይ በሚቀጥፉት ላይ አላህ ቁጣውን ያውርድ🤲 የልብ እርጋታን ምታገኙበት ጁሙዓ ይሁንላቹ ፣ በዱዓ እንተዋወስ ።❤️🖤
Mostrar todo...
8👍 6
Photo unavailableShow in Telegram
ሰላሙአለይኩም እቺ በፎቶ እምትመለከቷት እናታችን የ6ልጆች እናት ስትሆን በጅማ ዞን የአሰንዳቦ በሚባል አካባቢ የምትገኝ ሲሆን አካባቢው ላይ ያሉ ወንድሞች ምን ገጥሞሽ ነው ኬትስ ነው የመጣሽው የሚል ጥያቄ ሲያቀርቡላት ከእኖር ወረዳ ጠረደ ከሚባል አካባቢ የሄደች መሆኑዋን ተናግራቸዋለች። እናታችን የአዕምሮ ህመም እንዳለባትም ጥርጣሬያቸውን ነግረውናል ከባለ ቤታቸውም ተጣልተው እንደወጡ የገለፁ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆኑልንም ብለዋል። በመሆኑም የእኖር ሙስሊም ሚዲያ አባላት እኚህ እናት ከቤተሰቦቻቸው እንዲገናኙ ጥረት ማድረግ ይኖርብናል። እንረባረብ ጠረደ አካባቢ ያላችሁ ልጆች ምስሉን በማረጋገጥ ደውሉልን🙏 +251923600505
Mostrar todo...
👍 3
03:00
Video unavailableShow in Telegram
አሰላሙአለይኩም የእኖር_ሙስሊም ሚዲያ አባላት አብዛኞቻን በእኖር ወረዳ ጉንችሬ ከተማ መስተዳደር ውስጥ እየተገነባ ያለው የአል-አቅሳ መስጂድ ግንባታን በተመለከተ ብዙዎቻችን ችላ ብለነዋል። ከሰሞኑ ከወገናችን መላኩ ቢረዳ/አርቲስት ከአካባቢ ተወላጅነት በመነጨ ሞራል ስለዚህ መስጂድ መልእክቱን አስተላልፏል። ከመልእክቱም እንደሰማችሁት ለሙስሊሙ አንገት በሚሰብር ሁኔታ ግንባታው ከተጀመረ 3 አመታትን አስቆጥሮዋል!! እኛስ ወዴት ነው ያለነው!? ለመሆኑ ለዚህ መስጂድ ግንባታ የበኩላችንን አስተዋፆ አርገን ይሆን?! ካላደረግንም አሁኑኑ ለአኺራ ሚተርፍን ሰደቀተል ጃሪያ ተካፋዮች እንሁን እያሉ መልዕክቱን ያስተላልፋሉ የመስጂዱ ኮሚቴዎች።
Mostrar todo...
6
Repost from N/a
Repost from N/a
Repost from N/a