BBC Amharic | ቢቢሲ አማርኛ
Ir al canal en Telegram
2 074
Suscriptores
-524 horas
-197 días
-8730 días
Archivo de publicaciones
የዓለምን ገጽታ የቀየረው የመስከረም 1 ጥቃት 25ኛ ዓመት እና የስለላው ዘርፍ ያጋጠመው ውድቅት
ለብዙ አስርተ ዓመታት የተለያዩ መሪዎች እንደተናገሩት፣ የማንኛውም መንግሥት የመጀመሪያ ግዴታ ሕዝቡን መጠበቅ ነው። በአውሮፓውያኑ 2001 መስከረም 11 ቀን ግን አሜሪካ ይህንን ግዴታ ለመወጣት ሳትችል ቀርታለች። የስለላ መረጃዎች ቢኖሩም፣ የተለያዩ ፍንጮችን በጊዜው አገናኝቶ ተግባራዊ እርምጃ የወሰደ አልነበረም። በኋላ "911" ተብለው የታወቁት በአሜሪካ ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶች እና ለእነሱ የተሰጠው ምላሽ፣ በዚህ ክፍለ ዘመን የመጀመሪያዎቹን ሁለት አስርተ ዓመታት የውጭ ጉዳይ፣ የደኅንነት እና የስለላ ፖሊሲዎችን በእጅጉ የቀረጹ ክስተቶች ሆነዋል። በ2001 መስከረም 11፣ አጥፍቶ ለመጥፋት የተዘጋጁ የአልቃኢዳ አብራሪዎች የተጠለፏቸው አውሮፕላኖችን ዓለም ንግድ ማዕከል ሰማይ ጠቀስ ሕንጻዎች ጋር በማጋጨት ጥቃቱን ከጀመሩ በኋላ በዚያ ቀን 2,977 ሰዎች ተገድለዋል። እነዚህ ጥቃቶች ከየትም ተነስተው የመጡ አልነበሩም። የአሜሪካ ማዕከላዊ የስለላ ድርጅት (ሲአይኤ) ከ2001 በፊት ለብዙ ዓመታት ስለ አልቃኢዳ እና በስደት ስለሚኖረው ሳዑዲያዊ መሪው ኦሳማ ቢን ላደን መረጃ ነበረው። እንዲያውም እሱን ለመያዝ ተመድቦ የሚሠራ ልዩ ቡድን ነበረው።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
በዲሞክራቲክ ኮንጎ ትምህርት ቤት ውስጥ በተከሰተ የእሳት አደጋ ከ20 በላይ ልጆች ሞቱ
በምሥራቃዊው የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በአማጺያን ቁጥጥር ሥር ባለችው ቡካቩ ከተማ ውስጥ ሁለት ትምህርት ቤቶች ላይ የእሳት አደጋ ከተነሳ በኋላ ከእሳቱ ለማምለጥ በተፈጠረ መረጋገጥ ቢያንስ 24 ተማሪዎች መሞታቸውን ባለሥልጣናት ገለጹ። በተከሰተው የእሳት አደጋ ምክንያት ከተማሪ ልጆች በተጨማሪ አዋቂዎችም ሕይወታቸውን ማጣታቸው የተመዘገበ ሲሆን የሟቾች ቁጥርም ሊጨምር እንደሚችልም ስጋት አለ። ከአደጋው የተረፉ ሰዎች በአቅራቢያ ወደ ሚገኙ ሆስፒታሎች ተወስደዋል፤ ከቦታው የተቀረጹ ምሥሎችም ጉዳት የደረሰባቸው ልጆች እየተሰቃዩ በሆስፒታል ወለል ላይ ተኝተው ያሳያሉ። በእሳቱ ምክንያት 300 ያህል ቤቶችም ወድመዋል፤ የእሳቱ መንስኤ ግን እስካሁን አልታወቀም።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
የየመን ሁቲ ታጣቂዎች ወሳኝ የቀይ ባሕር ወደብ የሆነችውን ሞካን መቆጣጠራቸው ተዘገበ
የየመን ሁቲዎች፣ በሳዑዲ የሚደገፉ የመንግሥት ኃይሎችን በመርታት ስትራቴጂያዊ የሆነችውን በቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የምትገኘውን ሞካ የወደብ ከተማን መያዛቸውን ወታደራዊ ምንጮች እና የዐይን እማኞች ገለፁ። በኢራን የሚደገፈው ቡድን ሞካን መያዙን ተከትሎ፣ ከባብ ኤል መንደብ ወሽመጥ ያለው ርቀት 75 ኪሎ ሜትር ብቻ ሆኗል። ይህ ወሽመጥ እስያን እና አውሮፓን የሚያገናኝ እንዲሁም በቀይ ባሕር በኩል ለሚደረጉ የመርከብ ጉዞዎች ቁልፍ የሆነ የንግድ መስመር ነው። ነገር ግን ሁቲዎቹ በዓለም አቀፍ የመርከብ እንቅስቃሴ ላይ ምንም ስጋት እንደማይፈጥሩ ገልጸዋል። ሆኖም ከሳዑዲ አረቢያ የሚመጡ መርከቦችን ዒላማ እንደሚያደርጉ በድጋሚ ዝተዋል። ሳዑዲ አረቢያ የአሜሪካ እና የእስራኤል ጦርነት በባሕረ ሰላጤው የሚገኘው የሆርሙዝ ወሽመጥን በአብዛኛው ከተዘጋ በኋላ የነዳጅ ምርቶቿን ለመላክ በቀይ ባሕር ላይ ጥገኛ ሆናለች።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
ከ600 በላይ እስረኞች በይቅርታ ሲለቀቁ 28 ይቅርታ ባለመጠየቃቸው ሳይፈቱ ቀሩ
ከአማራ እና ከኦሮሚያ ክልሎች በከባድ ወንጀሎች ተከስሰው በፌደራል መንግሥቱ በእስር ላይ ይገኙ የነበሩ ከስድስት መቶ በላይ ሰዎች በይቅርታ መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። በተመሳሳይ ክስ ለዓመታት በእስር ላይ የቆዩ ነገር ግን ይቅርታ ለመጠየቅ ፈቃደኛ ያልሆኑ 28 እስረኞች ደግሞ ሳይፈቱ ቀርተዋል። በ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት ዋዜማ ጳጉሜ 52018 ዓ.ም. ከእስር መፈታታቸው የተነገረው በመቶዎች የሚቆጠሩ ታሳሪዎች ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው በይቅርታ፣ ክሳቸው በሂደት ላይ የነበረው ደግሞ እንዲቋረጥ ተደርጎ መሆኑን ኮሚሽኑ አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም ለአዲሱ ዓመት ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ላይ ልዩ ልዩ ወገኖች "በአንድም ሆነ በሌላ ስህተት የታሠሩ ወገኖች በይቅርታ እና በሕግ አግባብ እንዲፈቱ" መጠየቃቸውን እና መንግሥትም ተቀብሎ "በሂደቱ የተስማሙትን ፈትቷል" ብለዋል። ኢሰመኮ እንዳለው የተለቀቁት ሰዎች ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ በሽብር እና በሌሎች ከባድ ወንጀሎች ተከሰው ፍርድ ቤት ውሳኔ የሰጠባቸው እንዲሁም በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው በፍርድ ሂደት ላይ የሚገኙ ነበሩ። ታሳሪዎቹ "ጉዳያቸው በልዩ ሁኔታ እንዲታይ. . . በኮሚሽኑ በኩል ለመንግሥት እንዲቀርብላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ" በማድረግ ኢሰመኮ ታሳሪዎቹ በሕግ ሂደት ይቅርታ እንዲገያኙ ጉዳዩን ለመንግሥት አቅርቦ ምላሽ ማግኘቱን ገልጿል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
ኮሚሽኑ ትግራይን የሚመለከቱ አጀንዳዎችን የሚያቀርበው ለፌዴራል መንግሥቱ መሆኑን ገለፀ
ከአራት ዓመታት በላይ ወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮችን በማሰባሰብ ከአንድ ወር በላይ ምክክር ያደረገው ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ውጤቱን ለሚመለከታቸው አካላት እንዲሁም ትግራይን የሚመለከቱ አጀንዳዎችን ለፌደራል መንግሥቱ እንደሚያርብ አስታወቀ። በዚህም አራት ሺህ የሚሆኑ ተመካካሪዎች የተሳተፉበትን ኮሚሽኑ የሀገራዊ ምክክር ውጤት የሆነውን የመጨረሻውን ምክረ-ሃሳብ ከመስከረም 10 በፊት ለመንግሥት እንደሚያቀርብ አመልክቷል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ በምክክሩ የቀረቡ ምክረ-ሃሳቦችን ለተግባሪ የፌዴራል መንግሥት አካላት ከመስከረም 10 በፊት ለማቅረብ ምክረ-ሃሳቦቹን እያደራጀ መሆኑን ይፋ አድርጓል። በተጨማሪም በክልሎች እና በከተማ አስተዳደሮች ውስጥ ለሚደረጉ ምክክሮች የሚረዱ አጀንዳዎችን፣ እንዲሁም እነዚህ አካላት ሊፈፅሟቸው የሚገቡ የሕዝብ ጥያቄዎችንም በዚሁ ጊዜ ውስጥ ለማስረከብ እየሠራ መሆኑን ገልጿል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
ከ325 ሺህ ብር በላይ የሚያስወጣው አዲሱ የአይፎን ስልክ ምን ይዟል
አፕል አይፎን ስልኮችን ለገበያ ካቀረበ ከ20 ዓመታት በኋላ በስልኩ ላይ የተደረገውን ትልቁን ለውጥ ይፋ አድርጓል። ረቡዕ ዕለት በኩባንያው ዓመታዊ የምርት ማስተዋወቂያ ዝግጅት ላይ የመጀመሪያውን ታጣፊ የአይፎን ስልክን ማቅረቡን አስታወቋል። እንደ መጽሐፍ በሚታጠፍ ቅርጽ የተዘጋጀው አዲሱ አይፎን "ዱዎ" ተብሎ የተሰየመ ሲሆን፣ እስካሁን ከተመረቱት አይፎኖች ሁሉ በመጠኑ ትልቁ ነው። አዲሱ ስልክ በአሜሪካ ዋጋው ከ1,999 ዶላር ጀምሮ እስከ 3,200 ዶላር (325 ሺህ አስከ 500 ሺህ ብር በላይ) የሚደርስ ሲሆን፣ እስካሁን ለገበያ ከቀረቡ የአይፎን ስልኮች መካከል ከፍተኛ ዋጋ የሚያስወጣ ነው።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
አስመራ፡ በውሃ እጥረት የምትሰቃየው ከተማ
"ትንሿ ሮም" በመባል የምትታወቀው አሥመራ አሁን መልክዓ ምድሯ ተለውጦ፣ ነዋሪዎቿ በከባድ የውሃ እጥረት የሚንገላቱባት ሆናለች። የከተማዋ ጎዳናዎች በቢጫና ሰማያዊ የውሃ ጄሪካኖች እንዲሁም ውሃ በሚያመላልሱ በእጅ የሚገፉ ጋሪዎች ተሞልተው ይስተዋላሉ። ይህ ለወራት የቀጠለ የውሃ ችግር ነው። ሕጻናት ሳቀይር ውሃ ለመፈለግ ሲንገላቱ ይታያል። የዚህን ችግር መንስኤ እና የሚተገበሩ የመፍትሄ አማራጮችን በተመለከተ ቢቢሲ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ ገብረመስቀል እና በለንደን የሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲን ጠይቋል። ሁለቱም አካላት መልስ አልሰጡም። የአመሥራ ከተማ ነዋሪ የሆነው አስመሮም (ስሙ ተቀይሯል) "በዕድሜዬ እንዲህ ያለ ችግር አይቼ አላውቅም" ይላል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
የአማካይ ዘመን ምርጫን ሪፐብሊካኖች ካሸነፉ እያንዳንዱ አዋቂ አሜሪካዊ 5,000 ዶላር እንደሚያገኝ ትራምፕ ተናገሩ
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በኅዳር ወር በሚካሄዱት የአማካይ ዘመን ምርጫዎች ሪፐብሊካኖች ሁለቱንም ምክር ቤቶች ካሸነፉ፣ እያንዳንዱ አዋቂ አሜሪካዊ 5,000 ዶላር እንዲያገኝ እንደሚያደርጉ ተናገሩ። ይህ ዕቅድ ከአንድ ትሪሊዮን ዶላር በላይ የሚያስወጣ መሆኑ ተገልጿል። ትራምፕ አከራካሪ የሆነውን ይህን ቃል የገቡት በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ዘመን አማካይ ላይ የሪፐብሊካን ፓርቲ ለመጀመሪያ ጊዜ ባካሄደው ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው። ዕቅዱ እንዴት እንደሚተገበር እና ገንዘቡ ከየት እንደሚመጣ ግን ምንም ዝርዝር አልሰጡም። ሆኖም ገንዘቡ አሜሪካ ውስጥ ብቻ መዋል እንዳለበት ተናግረዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
ሰሜን ኮሪያ አዲስ ባለ ሁለት ፎቅ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ጣቢያ መገንባቷ ተገለፀ
ሰሜን ኮሪያ ተጨማሪ ባለ ሁለት ፎቅ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ጣቢያ መገንባቷን የዓለም የኒውክሌር መሣሪያዎች ተቆጣጣሪ ተቋም አስታወቀ። ይህንን ድርጊትም "እጅግ አሳሳቢ" ሲል ገልፆታል። አዲሱ ግንባታ የዋናው ኒውክሌር ማዕከል ዮንግብዮን አካል ሲሆን፣ ዩራኒየምን ለማበልጸግ የሚጠቅሙ እስከ 28 ሴንትሪፊዩጅ የሚባሉ የማሽን ስብስቦችን ማስተናገድ እንደሚችል ተነግሯል። ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ ባለፈው ወር መጨረሻ በወጣው ሪፖርት፣ ፒዮንግያንግ በሌላ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ቦታ ላይም አዲስ ማስፋፊያ ሰርታ ወደ ሥራ አስገብታለች። እነዚህ ግኝቶች ሰሜን ኮሪያ በማዕቀብ የተገደበውን የኒውክሌር መሠረተ ልማቷን ቀስ በቀስ እያስፋፋች መሆኗን የሚያመለክቱ ናቸው። ተቆጣጣሪዎቹ ከአውሮፓውያኑ 2009 ጀምሮ ከሰሜን ኮሪያ ከተባረሩ በኋላ በሀገሪቱ ውስጥ የክትትል ሰራተኞች የሌሉት ኤጀንሲው፣ በሳተላይት ምስሎች ላይ በመመስረት ነው ግምገማዎችን የሚያደርገው።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
ስደተኞች ከሞሮኮ ወደ ሴዩታ ከመሻገራቸው በፊት የስፔን የደኅንነት ተቋም መረጃ እንደደረሰው ተገለጸ
በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ከሞሮኮ ወደ ስፔን ግዛት ሴዩታ ከመሻገራቸው በፊት የስፔን የደኅንነት ተቋም መረጃ ደርሶት እንደነበረ አዲስ የመንግሥት ሰነድ ይፋ አደረገ። የስፔን መንግሥት በርካታ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች ከሞሮኮ መሻገራቸውን በተመለከተ ተመጣጣኝ እርምጃ አልወሰደም በሚል እየተወቀሰ ሳለ ነው ሰነዶቹን ያወጣው። በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ስደተኞች የስፔንን ድንበር እንዲሻገሩ ጥሪ የሚያደርጉ ይዘቶች መዘዋወራቸውን በተመለከተ በአውሮፓውያኑ ሐምሌ 29 የስፔን ብሔራዊ ደኅንነት ተቋም ለሞሮኮ እና ሴዩታ ባለሥልጣናት አስታውቋል። በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩት ስደተኞች ሴዩታ የገቡት ሐምሌ 30 ነበር።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
በአሜሪካ ከፍተኛ የተባለውን ከ230 ሚሊዮን ዶላር በላይ ክሪፕቶከረንሲ የሰረቀው ሴንጋፖራዊ ወጣት
የሲንጋፖር ዜጋ የሆነ ወጣት በአሜሪካ ካጋጠመ ከፍተኛ ከሆኑት የክሪፕቶከረንሲ ስርቆቶች መካከል አንዱን በመምራት የቀረበበትን ክስ ተቀብሎ ለፍርድ ቤት ጥፋተኛ መሆኑን አመነ። የ22 ዓመቱ ማሎን ላም ከጓደኞቹ ጋር በመተባበር 245 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ቢትኮይን በመስረቅ እና የተሰረቀውን በሕጋዊ መንገድ እንደተገኘ ለማስመሰል መሞከሩን አምኗል። የአሜሪካ ፍትሕ ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ላም እና ተባባሪዎቹ የተሰረቀውን ገንዘብ በመጠቀም በአንድ ምሽት እስከ 500 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በምሽት መዝናኛ ክለቦች ወጪ ያደርጉ ነበር። በተጨማሪም ዋጋቸው ከ100 ሺህ እስከ 3.8 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ውድ የቅንጦት መኪኖችንም ገዝተው ነበር። ላም ጥፋተኝነቱን ማመኑን ተከትሎ እስከ 20 ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት ሊፈረድበት ይችላል። ጉዳዩን የተመለከቱት ዳኛ ኮሊን ኮላር-ኮቴሊ የቅጣት ውሳኔ ለማሳለፍ ቀን አልቆረጡም።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
የአሜሪካ እና የኢራን ጦርነት እንዴት ሊቆም ይችላል የሦስት ተንታኞች ዕይታ
የአሜሪካ እና የኢራንን ጦርነት ለማስቆም ተጨባጭ የሆነ ስምምነት ላይ ይደረሳል የሚለው ተስፋ ደብዝዞ ይታያል፤ ሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች ጥቃቶችን በመፈጸም እና የማይለሳለሱ አቋሞችን በማንጸባረቅ ላይ ናቸው። እነዚህ ጥቃቶች የተከሰቱት አሜሪካ ወደ አዲስ ምዕራፍ እየገባች መሆኗን ከገለጸች ከቀናት በኋላ ነው፤ በኢራን እና ከኢራን ጋር የንግድ ግንኙነት ያላቸው አገራት ላይ ያነጣጠረ ሰፊ የኢኮኖሚ ማዕቀብ ይፋ አድርጋለች። የአሜሪካ ዓላማ ኢራንን ወደ ድርድር ማምጣት እና በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የምትፈጽማቸውን ጥቃቶች እንድታቆም ማስገደድ ነበር። ይህ ለዓለም ንግድ በጣም ወሳኝ የሆነው የመርከብ መተላለፊያ መስመር፣ አሜሪካ እና እስራኤል ግጭቱን ባለፈው የካቲት ወር ከጀመሩ ወዲህ በተግባር ተዘግቶ ቆይቷል። ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር የፈረሙት እና በ60 ቀናት ውስጥ ወደ ቋሚ የተኩስ አቁም እና የሰላም ስምምነት ሊያመራ የነበረው የመግባቢያ ሰነድ ጊዜው አልፏል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
ኤርትራ ግለሰቦች እና ተቋማት በሚይዙት የጥሬ ገንዘብ መጠን ላይ ገደብ ጣለች
የኤርትራ ግለሰቦች እና የንግድ ተቋማት ከባንክ ሥርዓት ውጭ ለተወሰነ ጊዜ መያዝ የሚችሉትን የጥሬ ገንዘብ መጠን የሚገድብ አዲስ መመሪያ ማውጣቷን የአገሪቱ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ። ረቡዕ ጳጉሜ 42018 ዓ.ም. በአገሪቱ መንግሥታዊ የሕግ ጋዜጣ ላይ ታትሞ ይፋ በተደረገው መመሪያ ማንኛውም ዓይነት የኤርትራ ገንዘብ፣ ናቅፋ ዝውውር በባንኮች እና በገንዘብ ተቋማት ብቻ መሆን እንዳለበት አዝዟል። በአዲሱ መመሪያ መሠረት ግለሰቦች ከ25 ሺህ ናቅፋ በላይ የሚሆን ጥሬ ገንዘብ ከ15 ቀናት በላይ በእጃቸው ማቆየት አይችሉም። እንዲሁም በተለያዩ ሦስት ደረጃዎች የተመደቡ የንግድ ተቋማትም በ50 ሺህ፣ በ100 ሺህ እና በ150 ሺህ ናቅፋ መጠን የተገደበ ጥሬ ገንዘብ ለሁለት ሳምንታት ብቻ መያዝ እንዲችሉ ተፈቅዷል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
ሜታ የሕጻናት ወሲባዊ ብዝበዛ ይዘት ያላቸው ማስታወቂያዎች ማስተላለፍ መቀጠሉን አዲስ ሪፖርት አጋለጠ
ሜታ ሰው ሠራሽ አስተውሎት በመጠቀም በመቶዎች የሚቆጠሩ የሕጻናት ወሲባዊ ብዝበዛ ይዘት ያላቸው ማስታወቂያዎችን ማስተላለፉን አዲስ የወጣ ሪፖርት አጋለጠ። ክፍያ የተፈጸመባቸው ማስታወቂያዎቹ ባለፉት 10 ወራት መለቀቃቸውን መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገ የመብት ተሟጋች ቡድን ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል። እነዚህ ማስታወቂያዎች በሕንድ በስፋት ወጥተዋል። ከሁለት ወራት በፊት ሜታ የሕጻናት ወሲባዊ ብዝበዛ ይዘት ያላቸውን ማስታወቂያዎች ከኢንስታግራም እንዲያጠፋ ከሕንድ መንግሥት ማሳሰቢያ ተሰጥቶት ነበር።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
የሱዳን የጤና ሥርዓት የውድቀት አፋፍ ላይ መድረሱን አንድ የሕክምና በጎ አድራጎት ድርጅት ገለፀ
ዓለም አቀፍ ድጋፍ በመቀነሱ ምክንያት በመላው ሱዳን በርካታ የጤና ተቋማት እየተዘጉ መሆናቸውን እና ቀድሞውንም የተዳከመው የሱዳን የጤና ሥርዓት የውድቀት አፋፍ ላይ እየተጠጋ እንደሆነ ሜዲሲን ሳን ፍሮንቲየርስ (ኤንኤስኤፍ) አስጠነቀቀ። የሕክምና በጎ አድራጎት ድርጅቱ እንዳለው፣ የሱዳን ከፍተኛ እርዳታ ለጋሽ የነበረችው አሜሪካ የውጭ እርዳታ የሚያቀርበውን ኤጀንሲ ዩኤስኤአይዲን ባለፈው ዓመት ከዘጋች በኋላ፣ በርካታ ድርጅቶች ተለዋጭ የገንዘብ እርዳታ ምንጭ ማግኘት አልቻሉም። በኒው ዮርክ የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ የተሰበሰቡ የዓለም መሪዎች ፈጣን እርምጃ እንዲወስዱ ኤንኤስኤፍ ጥሪ አቅርቧል። በሱዳን ጦር እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች መካከል በሚያዝያ ወር 2015 ዓ. ም. የተጀመረው ጦርነት፣ ዓለም ላይ ካሉት እጅግ አስከፊ ሰብአዊ ቀውሶች አንዱ እንዲፈጠር አድርጓል። በአሁኑ ጊዜ በሱዳን ከ33 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የሕክምና እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
ኦፕንኤአይ 90 ዓመት ላስቆጠረ ከባድ የሒሳብ ጥያቄ በ88 ሰዓታት ውስጥ መልስ ማግኘቱን አስታወቀ
ኦፕንኤአይ 90 ዓመት ላስቆጠረ ከባድ የሒሳብ ጥያቄ በሰዓታት ውስጥ ምላሽ ማግኘቱን አስታወቀ። የሰው ሠራሽ አስተውሎት ሞዴል እና በሺህዎች የሚቆጠሩ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቦቶችን በመጠቀም ለሒሳብ ጥያቄው በ88 ሰዓታት ውስጥ መልስ ማግኘት ተችሏል። ቻትጂፒቲን የሠራው ኦፕንኤአይ ትናንት ማክሰኞ እንዳስታወቀው 10,000 የኤአይ ቦቶች በመጠቀም የሒሳብ ችግሩ ተፈትቷል። የሒሳብ ጥያቄው 'ናቪየር-ስትሮክስ ኢኩዌዥንስ' የተባለው የሒሳብ ቀመር ክፍል ሲሆን፤ ለ90 ዓመታት ያህል ስሌቱ ሳይረጋገጥ ቆይቷል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
የአሜሪካ እና ካናዳ የንግድ ጦርነት ሲቀጥል፣ አሜሪካ በርካታ የካናዳ ምርቶች እንዳይገቡ አገደች
አሜሪካ የአልኮል መጠጦችን፣ የወተት ተዋጽኦ እና ሞተር ሳይክሎችን ጨምሮ በርካታ የካናዳ ምርቶች እንዳይገቡ እግድ ጣለች። እርምጃው የተወሰደው ካናዳ በአሜሪካ ምርቶች ላይ የጣለቻቸው አፀፋዊ ቀረጦች ተግባራዊ መሆናቸውን ተከትሎ ነው። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ማክሰኞ ዕለት በፈረሟቸው ተከታታይ ፕሬዝደንታዊ ትዕዛዞች፣ ካናዳ በአሜሪካ ላይ "አድልዎ እያደረገች ነው" ብለዋል። በካናዳ ምርቶች ላይ የጣሉት እገዳ ከመስከረም 19 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆንም ገልፀዋል። ከትራምፕ እርምጃ አስቀድመው በተመሳሳይ ቀን የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ካርኒ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልእክት፣ አገራቸው ከፍተኛ የንግድ አጋሯ ከሆነችው ከአሜሪካ በመራቅ አዲስ አጋሮችን ለመፈለግ በምታደርገው ሽግግር "ዋጋ በማስከፈል" የሚፈፀም ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
ህወሓት ኦሉሴጎን ኦባሳንጆን "ገለልተኛ አይደሉም" ማለቱ አንድምታው ምንድን ነው
ህወሓት የፕሪቶሪያ ስምምነት አሸማጋይ የሆኑት የአፍሪካ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ "የገለልተኛ አደራዳሪነት መርኅ አልታየባቸውም" ሲል ከስሷል። የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦባሳንጆ ለቀረበባቸው ክስ በጽሕፈት ቤታቸው በኩል በሰጡት ምላሽ፤ በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ባለሥልጣናት መካከል የነበረው ግንኙነት ተቋርጦ የፕሪቶሪያን ስምምነት የሚጥሱ ሙከራዎች እንዲሁም "ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ጠብ ጫሪ" ሁኔታዎች በመታየታቸው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንደጀመሩ አስታውቀዋል። የትግራይ ጦርነት በፕሪቶሪያ ስምምነት ከተገታ በኋላ የስምምነቱ ተፈጻሚነት ላይ ሁለቱም ወገኖች ጥያቄ እያነሱ ሲሆን፤ ለተፈጠሩ ክፍተቶች አንዳቸው ሌላቸውን ሲወቅሱም ይደመጣል። በስምምነቱ መሠረት መፈጸም የነበረባቸው በርካታ ጉዳዮች ተግባራዊ አለመሆናቸውን ሁለቱም ወገኖች ሲያነሱ ቆይተዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
በዋስ ከተለቀቁ "ፅምዶን ሊቀላቀሉ ይችላሉ" በሚል ፖሊስ ይግባኝ በማቅረቡ የኢሕአፓ ፖለቲከኞች እና ጠበቃ አበራ ሳይፈቱ ቀሩ
ባለፈው ሳምንት ፍርድ ቤት ከእስር በዋስ እንዲለቀቁ የወሰነላቸው ፖለቲከኞች እና የሕግ ባለሙያ ፖሊስ ይግባኝ በማቅረቡ ምክንያት ሳይፈቱ መቅረታቸውን ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ። ተጠርጣሪዎቹ በዋስ የሚፈቱ ከሆነ "ከፅምዶ ቡድን ጋር ተቀላቅለው ሊሰወሩ ይችላሉ" በማለት የስር ፍርድ ቤትን የዋስትና ውሳኔ በመቃወም ፖሊስ ይግባኝ ጠይቋል። "በሽብር ወንጀል" የተጠረጠሩት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ፖለቲከኞች አቶ አበበ አካሉ እና አቶ ይሳቅ ወልዳይ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ፣ እያንዳንዳቸው በ50 ሺህ ብር ዋስ እንዲፈቱ የፌዴራሉ ፍርድ ቤት ባለፈው ሳምንት ዓርብ ነሐሴ 292018 ዓ.ም ነበር የወሰነው። የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦች ትላንት ሰኞ ጳጉሜ 2 የዋስትናውን ገንዘብ ቢያስይዙም፣ ፖሊስ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ በማለቱ አለመፈታታቸውን ጠበቃቸው አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የፌዴራል ፖሊስ ለጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ባቀረበው የይግባኝ አቤቱታው፣ ሦስቱ ተጠርጣሪዎች "ጫካ ከሚገኘው ፅምዶ ቡድን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው" ሲል አመልክቷል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
የተካረረው የአሜሪካ እና የካናዳ የንግድ እና የታሪፍ ጦርነት
የአሜሪካንን እርምጃ ተከትሎ ካናዳ በበርካታ የአሜሪካ ምርቶች ላይ የጣለችው የአጸፋ ታሪፍ ከዛሬ ማክሰኞ ጀምሮ ሥራ ላይ መዋል ጀመረ። ይህ ካናዳ በአሜሪካ ላይ የጣለቸው የአጸፋ ታሪፍ ወደ 28 ቢሊዮን የካናዳ ዶላር (20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር) የሚጠጉ ከአሜሪካ ወደ ካናዳ የሚገቡ ምርቶችን ይመለከታል። ይህም ከብረት እስከ የቤት እቃዎች፣ ጥጥ እና የተለያዩ አልባሳትን የሚያካትት ሲሆን፣ የታሪፉ መጠን እስከ 50 በመቶ ይደርሳል። የአሜሪካ እና የካናዳ ባለሥልጣናት አዲስ ስምምነት ለመፈራረም ፍላጎት እንዳላቸው ቢገልጹም፣ በነሐሴ መጨረሻ የተቋረጡትን ውይይቶች ለመቀጠል የሚደረግ ምንም እርምጃ አልታየም።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
