ክፍል 3
ከpornography በሽታ እንዴት እናምልጥ👌።
Part 2
እንደጠቀስነው ችግሩ እንዳለ ነው።
እንግዲህ ከፖርኖግራፊ ሱስ ለመውጣት የምትፈልጉ
ወገኖች ከዚህ ቀጥሎ የቀረቡትን ተግባራዊ ነጥቦች
ብትከተሉ ከእግዚአብሔር ፀጋ ጋር 100% ልትወጡ
እንደምትችሉ አረጋግጥላቹሃለው።
1. እግዚአብሔር እንደሚወዳቹ አውቃችሁ ንሰሐ ግቡ
በዚህ ሱስ ውስጥ የገቡ ሰዎች እግዚአብሔር
እንደሚጠላቸውና እንደሚጸየፋቸው
ያስባሉ። እንዲህ አይነቱ
ሃሳብ ሰዎችን የሱሱ ባሪያ አድርጎ ለማኖር ሰይጣን
ይጠቀምበታል። በፖርኖግራፊ ሀጢያት መውደቅን ተከትሎ
ሰይጣን ሁልጊዜ እዛው ተብትቦ
ሊያስቀረን ይጥራል። ይህም
ራሳችንን እንድንጠላ፤ እግዚሐብሄር ለእኛ ግድ
እንደማይለውና ሩቅ እንደሆነ እንድናስብ
እና ተስፋ ቢስነት
እንዲሰማን ሀሳባችንን በመያዝ ይተጋል። ሁሌም ቢሆን
ውድቀትን ተከትሎ ዋና ጠላታችን ማን እንደሆነ ማወቁ ተገቢ
ነው። በጥፋታችን ማዘናችን ተገቢ ቢሆንም እንደ ይሁዳ ወደ
ከፋ እርምጃ የሚወስድ መሆን
የለበትም።
(ማቴ 27:4-5 )
ራሳችንን በመጥላት
ውስጥ ዋዥቀን ራሳችንን የመቅጣት
አዝማሚያው ቢኖረንም መውሰድ ያለብን እርምጃ
በእግዚአብሄር
ፊት እንደዳዊት በንስሃ መደፋት ነው (መዝ
51:1-10) በእኛ እና በሐጥያታችን መካከል ልዩነት አለ።
እግዚአብሔር ኃጥያትን ይጠላል፤ ኃጥያተኛውን ግን
ይወዳል። እናት የልጅዋ ልብስ ቢቆሽሽ ለልጅዋ ያላት ፍቅር
እንደማይቀየር እግዚአብሔርም ለእኛ ያለው ፍቅር
አይቀየርም። ከዚህ ህይወት ወጥታቹ ወደ እርሱ ለመምጣት
ብትወስኑ
እጆቹን ዘርግቶ ይቀበላችኋል። በቀራንዮ ላይ
የፈሰሰው የኢየሱስ ደም ከኃጥያታቹ ሁሉ እንደሚያነጻቹ
አምናቹ በእግዚአብሔር ፊት ንስሐ ግቡ። “የልጁም የኢየሱስ
ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ
ያነጻናል” (1ዮሐ 1:7)
የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ስለ አለም ሁሉ ስለፈሰሰ
በእግዚአብሔር ፊት ይቅር የማይባል ኃጥያት የለም።
2. አምናቹ ጸልዩ
የሰው ልጅ በራሱ ጥረት ከኃጥያት መውጣት አይችልም።
የእግዚአብሔር ጸጋ ሲያግዘው ግን የማይቻለውን ችሎ
በቅድስና አሸብርቆ መኖር ይቻላል። እስከ ዛሬ በግል ጥረታቹ
ከዚህ ሱስ መውጣት ስላልቻላቹ ተስፋ ቆርጣቹ ሊሆን
ይችላል።
ጸጋው ግን ጣልቃ ገብቶ አዲስ ህይወት ሊሰጣችሁ
ይችላል። ይህ ደግሞ የሚሆነው “እኔ ደካማ ስለሆንኩ
የሚረዳኝ ጸጋ ይሰጠኝ” ብሎ በጸሎት እግዚአብሔርን
በመለመን ነው። በፀሎት ትጉ (ኤፍ 6:18)። መውጣት
እንደሚቻል አለማመን በራሱ ሰንሰለት ነው። የእግዚአብሔር
ጸጋ ታሪክን እንደሚቀይር ከዚህ ህይወት መውጣት
እንደሚቻል እመኑ። ምክንያቱም ከኃጥያት አስወጥቶ ቅዱስ
የሚያደርግ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን
የእግዚአብሔር ጸጋ
ተገልጧልና። ( ቲቶ 2:11-13)
3. ሀሳብን በሀሳብ(Word of God) ተዋጉ
የፖርኖግራፊ ኃጢያት ስርወ-መሰረቱ ሀሳብ አንደመሆኑ
ሀሳብን ልንዋጋው የምንችለው በሌላ ሀሳብ በመተካት ብቻ
ነው ። አዕምሮእችንን በእግዚብሄር ሀሳብ ለመሙላት ደግሞ
ዕለት ዕለት የእግዚአብሄርን ቃል በማንበብ እና
በፀሎት ጊዜ
ማሳለፍ ያስፈልጋል። ምን ድነው ምናየው ምናየውን እንሆናለን ምን ድነው
ምንሰማው ምንሰማውን እንሆናለን ምን ድነው chat ምን ደራረገው በtelegrham ሊሆን ይችላል ። የምናውቀውንም የማናውቀዉንም ሰው ዝም ብለን እያወራን በ
pornography ሱስ እንዳንጠመድ አብዝተን እንጠንቀቅ ዝም ብለን ግዜ ከምናባክን ቃሉን እየበላን bold እየሆንን እንሂድ እንጅ ደስታችንን በእግዚአብሄር ስናገኝ
በሀጢያት የምናገኘውን ጊዜያዊ ደስታ እየተፀየፍን
እንሄዳለን።
ይቀጥላል👌👌👌👌
Part 3
https://t.me/essat7.