cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Merkato Media

#merkato_media #መርካቶ_ሚድያ በዚህ ቻናል ለኢትዮጵያ ፍቅር ሰላም አንድነት ስለ ፍትህ የምናወራበት ድምፅ ላጡ ድምፅ የምንሆንበት ቻናል ነው። ''We testify about the Truth ''

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
7 323
Suscriptores
-524 horas
-367 días
-28230 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

መንግሥት የመንግሥት ሠራተኞች ቅጥርና ምደባ የአገሪቱን ብሄረሰቦች ብዝኀነትና የጾታና የአካል ጉዳተኞችን ተዋጽዖ የጠበቀ እንዲኾን የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል። ምክር ቤቱ፣ በረቂቅ አዋጁ ላይ ትናንት ተወያይቷል። ረቂቅ አዋጁ፣ በመንግሥት ሠራተኞች ደሞዝ ጭማሪ፣ ደሞዝ እርከን፣ ክፍያና ጥቅማጥቅሞች ላይ ማሻሻያ እንዳደረገም ተገልጧል። የአነሳ ብሄረሰቦችና የማኅበረሰብ ክፍሎች በመንግሥት መስሪያ ቤቶች በቅጥር፣ ምደባ፣ ዝውውር፣ በሥራ ደረጃ እድገት፣ በትምህርትና ሥልጠና ረገድ ተጨማሪ መንግሥታዊ ድጋፍ እንዲደረግላቸውም ረቂቅ አዋጁ ይደነግጋል። ምክር ቤቱ፣ ረቂቅ አዋጁን ጉዳዩ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል። [ዋዜማ]
Mostrar todo...
👍 7👎 5
ዋቻሞ ዩኒቨርስቲ🙆‼️ በሀድያ ዞን ዋቻሞ ዩኒቨርስቲ ለአንድ የዩኒቨርስቲው የፋይናንስ ቡድን መሪ የ790 ቀን አበል እንዲሁም ለሌላኛው የፋይናንስ የቡድን መሪ ደግሞ በስድስት ወራት ውስጥ ብቻ የ1,469 ቀን (1,056,854 ብር) አበል እንደተከፈላቸው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሰነድ ማስረጃዎችን፣ጥቆማዎችን እና መመሪያዎችን በማጣቀስ ምርመራ አድርጎ ውጤቱን ይፋ አድርጓል። ሌላም የዩኒቨርስቲው ፋይናንስ ሳያውቅ 1.4 ቢሊዮን ብር ለኦክስጅን ማምረቻ በሚል በህገወጥ መንገድ መንቀሳቀሱን እና ፍቃድ የሌለው የኮንስትራክሽን ድርጅት ግንባታውን እንዲሰራ ያለ ጨረታ እንደተሰጠው በምርመራ ውጤቱ ተገልጿል። በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተመሳሳይ ምርመራ ቢደረግ ከዚህም በላይ የሙስና ወንጀል እንደሚገኝ እሙን ነው። @sheger_press @sheger_press
Mostrar todo...
👍 21 1
2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መርሐግብር ይፋ ሆኗል፡፡ መርሐግብሩ ከትግራይ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱም የከተማ አስተዳደሮች በወረቀት እና በበይነ መረብ ፈተናውን ለሚወስዱ ተፈታኞች እንደሚያገለግል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና:— ✔ከሐምሌ 3-5/2016 ዓ.ም ለማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ✔ከሐምሌ 9-11/2016 ዓ.ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ይሰጣል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት @sheger_press @sheger_press
Mostrar todo...
👍 5
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ በአፋርና ሱማሌ ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች በአፋር እና ኢሳ ጎሳዎች መካከል በሚያጋጥሙ ግጭቶች ሳቢያ ከ38 ሺህ በላይ ዜጎች አፋር ክልል ውስጥ በሦስት ወረዳዎች መፈናቀላቸውን ባካባቢው ባደረገው ጉብኝት ማረጋገጡን አስታውቋል። የኹለቱ ጎሳዎች ታጣቂዎች ባብዛኛው ግጭት ውስጥ የሚገቡት፣ በአፋር ክልል ገቢ ረሱ ዞን እና በሱማሌ ክልል ሲቲ ዞን አጎራባች አካባቢዎች ሲኾን፣ በተለይ በተያዘው ዓመት ተደጋጋሚ ግጭቶች ተካሂደዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ በኹለቱ ጎሳዎች መካከል በተደጋጋሚ የሚካሄደውን ግጭት ለመፍታት ከሳምንታት በፊት አሸማጋይ ኮሚቴ ማቋቋሙ አይዘነጋም። ኾኖም የጎሳ ግጭቱ እስካለፈው ሳምንት ድረስ ቀጥሎ እንደነበር ተሰምቷል። @merkato_media
Mostrar todo...
👍 11
ታሰረ ‼️ በቲክቶክ የማህበራዊ ትስስር ገፅ መሌ ፌዳው በሚል ስም የምናውቀው የፌደራል ፖሊስ አባል መለሰ ብርሃኑ መታሰሩ ተሰምቷል። የፖሊስ አባሉ የታሰረበት ምክንያት የመከላከያን የክብር ልብስ ለብሶ የሰራዊቱን ስም የሚያጎድፍ ቪድዮ ሰርቷል በሚል ሲሆን ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርቦ ዋስትና ሳይፈቀድለት ቀጠሮ እንደተሰጠበት እንደቀረ ታውቋል። @sheger_press @sheger_press
Mostrar todo...
👍 17😁 6😢 3
ባለፉት ጥቂት ቀናት በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን መራዊ ከተማ በፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግሥት ኃይሎች መካከል ግጭቶች እንደተካሄዱ ዋዜማ ከምንጮች ሰምታለች። በግጭቱ ሳቢያ፣ የክልሉን ዋና ከተማ ባሕርዳርን ከምሥራቅ ጎጃም ዞን ዋና መቀመጫ ደብረማርቆስ ጋር የሚያገናኘው መንገድ ለተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ተዘግቶ እንደነበር ተሰምቷል። በተመሳሳይ፣ በሰሜን ወሎ ዞን ውርጌሳ ከተማ እና አካባቢዋ በኹለቱ ወገኖች መካከል ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ግጭት እንደተካሄደ ምንጮች ተናግረዋል። @merkato_media @merkato_media
Mostrar todo...
👍 12
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል የሕወሃት ኃይሎች ከሱዳን ጦር ሠራዊት ጋር ወግነው እየተዋጉ ነው በማለት ያቀረበውን ውንጀላ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስተባብሏል። የፈጥኖ ደራሹን ኃይል ውንጀላ "በጥብቅ እንደሚያወግዝ" የገለጠው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ይህን ውንጀላ ያሰማው ዓለማቀፍ ድጋፍ ለማግኘት ሲል ነው በማለት አጣጥሎታል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ሕወሃት የፖለቲካ ፓርቲ በመኾኑ "የታጠቀ ኃይል ወይም ሚሊሺያ የለውም" በማለትም ምላሽ ሰጥቷል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ አያይዞም፣ ሱዳን በትግራዩ ጦርነት ወቅት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የክልሉን ስደተኞች ያስጠለለች እንደመኾኗ ትግራይ በሱዳን የውስጥ ጉዳይ የምትገባበት ምክንያት ሊኖራት አይችልም ብሏል። ኹለቱ ወገኖች ጦርነቱን ከሚያባብሱ ንግግሮች እንዲቆጠቡና ጦርነቱን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ጠይቋል። @merkato_media @merkato_media
Mostrar todo...
👍 7
ለመላው የመርካቶ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ   እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። በዓሉ የሰላም ፣ የደስታ ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ  ይሆን ዘንድ እየተመኘን በዓሉን ስናከብር ዓቅመ ደካሞችን በመርዳት ይሆን ዘንድ በትህትና እንጠይቃለን። መልካም በዓል @merkato_media @merkato_media
Mostrar todo...
👍 19 2
ተፈታ‼️ ልጅ ያሬድ ተፈቷል💇‍♂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ክብር የሚነካ ቃላት ተናገሮ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበረው ልጅ ያሬድ በዛሬው ዕለት ተፈቷል። @sheger_press @sheger_press
Mostrar todo...
👎 33👍 7🖕 1
ጌታቸው ረዳ‼️ "በየጊዜው ወጣቶች የምገብርበት የጦርነት ምዕራፍ መዘጋት አለበት " - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በኩል ዛሬ መልዕክት አሰራጭተው ነበር። በዚህም ፤ " የህዝባችን ሁለንተናዊ መብትና ጥቅም ከማረጋገጥና አስተማማኝ ከማድረግ የሚቀድም ሌላ አጀንዳ የለንም " ብለዋል። " የህዝባችን ጥቅምና መብት የሚያረጋግጥ መንገድ ሁሉ እንጓዘዋለን " ያሉት አቶ ጌታቸው " ጉዞው እንዲሳካ የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው " ሲሉ አክለዋል። ፕሬዜዳንቱ ፤ " ከሚገባው በላይ ያበረከተ ህዝብ በቅንነትና ታማኝነት ማገለገል ይገባል " ሲሉም ገልጸዋል። " ህዝቡ ከጦርነትና ጦርነት ወለድ ችግሮች በማላቀቅ ወደ አስተማማኝ ሰላም እንዲሸጋገር መስራት ይገባል " ሲሉም አስገንዝበዋል። አቶ ጌታቸው ረዳ  ፤ " በየጊዜው ትኩስ ሃይል የሆኑትን ወጣቶች የምንገብርበት የጦርነት ምዕራፍ ተዘግቶ ፤ የልማትና የእድገት ፍላጎታችን እንዲሳካ መስራት አለብን " ብለዋል። (Tikvah)
Mostrar todo...
😁 18👍 15🕊 3👎 2