Bashewam Primary & Junior School 1-8
Ir al canal en Telegram
2 778
Suscriptores
+1524 horas
+287 días
+8230 días
Archivo de publicaciones
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ተማሪዎች ውጤታችሁን ለማየት ሊንኩን በመጫን https://aa.ministry.et/#/result
Registration number ና first name በማስገባት መመልከት ትችላላችሁ
ውድ የባሸዋም 8ኛ ክፍል ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች: እንኳን ደስ ያላችሁ :ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ማለፍያ ውጤት 50%እና በላይ ሆኖ ከ30 በላይ ተማሪዎቻችን 90% እና በላይ ፣78 ተማሪዎች ከ75-89% ያስመዘገቡ ሲሆን ሌሎችም በጣም በከፍተኛ ውጤት ወደ 9ኛ ክፍል ተዛውረዋል።በተጨማሪም ተማሪ ኑሀሚን ጀንበር 99.17 በማስመዝገብ ከፍተኛ ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል።
የትኩረት ዜና!
የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ይፋ ሆነ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በዛሬው እለት የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ማለፊያ ውጤትን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡ ሲሆን በመግለጫቸውም በዘንድሮው ማለፊያ ውጤት 50% እና ከዛ በላይ ያስመዘገቡ መደበኛ ተማሪዎች ወደ ዘጠነኛ ክፍል እንደሚዘዋወሩ ጠቁመው የተለያየ የአካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች የማለፊያ ነጥቡ 45% መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዘንድሮ 73,385 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደው 70.6% ያህሉ 50 ፐርሰንትና ከዛ በላይ በማምጣት ማለፋቸውን ዶክተር ዘላለም ገልጸው 61,840 ከሚሆኑ የቀን ተማሪዎች መካከል 50,812 የሚሆኑት ማለትም 82.16 % ያህሉ የማለፊያ ውጤቱን በማስመዝገብ ወደቀጣዩ የትምህርት እርከን መዘዋወራቸውን አስረድተዋል፡፡
የዘንድሮው ውጤት ባለፉት አመታት ጋር ሲነጻጸር መሻሻል ማሳየቱን ኃላፊው ጠቁመው ለዚህም የሞዴል ፈተናዎችና የማጠናከሪያ ትምህርቶች መሰጠታቸው ፤የተሻለ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ስርዓት መዘርጋቱ፤አዲሱን ስርአተ ትምህርት መሰረት ያደረገ ፈተና መዘጋጀቱ እንዲሁም መምህራን እና የትምህርት አመራሮች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣታቸው እንዲሁም በትምህርት ቤቶች የተጀመረው የምገባ ስርዓትና ለተማሪዎች እየቀረቡ የሚገኙ ዩኒፎርምን ጨምሮ የተለያዩ የመማሪያ ቁሳቁሶች ለውጤቱ መሻሻል አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን አስገንዝበዋል፡፡
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
