es
Feedback
Bashewam Primary & Junior School 1-8

Bashewam Primary & Junior School 1-8

Ir al canal en Telegram

Bashewam School Grade 1-8

Mostrar más
2 748
Suscriptores
+124 horas
+57 días
+4330 días
Archivo de publicaciones
የተፈታኞች መብትና ግዴታ ✅ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት  አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና   ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች(Orientation)ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት። ⭐️ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል። ✅ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፍ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)። ✅ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል:: ✅ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት  የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ። ⭐️እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ። ✅ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ  ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል። ⭐️ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም ⭐️ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው። ✅ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም። ⭐️ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም። ⭐️ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት   እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። ✅ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል። ✅ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል። ✅ለተፈታኞች የተፈቀዱ ✍️እርሳስ ✍️የቀን ተማሪዎች የደንብ ልብስ (UNIFORM) ✍️ADMISSION CARD ✍️ላጲስ፣ መቅረጫና ማስመሪያ ❌ለተፈታኞች የተከለከሉ 🔠 ስልክ ይዞ መግባት አይቻልም 🔠ካልኩሌተር 🔠የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን 🔠ሰዓት 🔠በሀኪም ከታዘዘ ውጪ የሆኑ መነጽሮች 🔠የሚነበቡ ጽሁፎች በሙሉ ✅የፈተና ኦረንቴሽን ቀን ክፍል      በ9/10/2017 ዓ.ም ✅ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ ሰኔ 10,11እና 12  /2017 ዓ.ም                                   

የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ 👉 የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ 👉 በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ብቻ ማጥቆር አለበት፡፡ 👉 ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ 👉 ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን የአራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ 👉 በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ መልስ (የአራት ማዕዘን ቅንፍ/Square Bracket) ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ 👉 ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው 👉 መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። 👉 መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ 👉 ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ 👉 በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ 👉 ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። 👉 በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በመንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።

የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ 👉 የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ 👉 በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ብቻ ማጥቆር አለበት፡፡ 👉 ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ 👉 ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን የአራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ 👉 በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ መልስ (የአራት ማዕዘን ቅንፍ/Square Bracket) ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ 👉 ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው 👉 መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። 👉 መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ 👉 ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ 👉 በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ 👉 ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። 👉 በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በመንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።

Grade 5 & 7 Final Exam. Program.

ማሳሰቢያ:- እስካሁን ወደ መፈተኛ ጣቢያ መግቢያ Admission - Card ያልወሰዳችሁ የ6ኛ ከፍል ተማሪዎች ያለመግቢያ ካርድ ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት ስለማይቻል በድጋሚ እንድትወስዱ በጥብቅ እያሳሰብን ባለመዉሰዳችሁ ምክንያት ለሚፈጠረዉ ችግር ት/ቤቱ ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን ከወዲሁ እናሳስባለን::

የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚኒስትሪ ፈተና ከሰኔ 10 - 12/2017 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም የቀጣይ ክንውን መርሀ-ግብር እንደሚከተለው ይሆናል:: 1.✅ሰኞ ሰኔ 09/2017 ዓ. ም ከጠዋቱ 2:00 ላይ በት/ቤታችን በመገኘት የመፈተኛ ጣቢያ (ብስራት ት/ቤት) በፈታኝ አካላት Orientation ወስደዉ እና መፈተኛ ክፍል አይተው 5:00 ሰዓት ላይ ወደ ቤት የሚለቀቁ ይሆናል። 2.✅  ማክሰኞ ሰኔ10, አማርኛ እና እንግሊዘኛ እስከ 9:00 የሚፈተኑ ይሆናል:: 3.✅ረቡዕ ሰኔ11, ሂሳብ እና አካባቢ ሳይንስ እስከ 9:00 የሚፈተኑ ይሆናል:: 4.✅ ሐሙስ ሰኔ12 እስከ 4:30 ሰዓት የመጨረሻውን ፈተና ግብረግብ ተፈትነዉ የሚያጠናቅቁ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን::   ት/ቤቱ

photo content

የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚኒስትሪ ፈተና ከሰኔ 10 - 12/2017 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም የቀጣይ ክንውን መርሀ-ግብር እንደሚከተለው ይሆናል:: 1.✅ሰኞ ሰኔ 09/2017 ዓ. ም ከጠዋቱ 2:00 ላይ በት/ቤታችን በመገኘት የመፈተኛ ጣቢያ (ብስራት ት/ቤት) በፈታኝ አካላት Orientation ወስደዉ እና መፈተኛ ክፍል አይተው 5:00 ሰዓት ላይ ወደ ቤት የሚለቀቁ ይሆናል። 2.✅  ማክሰኞ ሰኔ10, አማርኛ እና እንግሊዘኛ እስከ 9:00 የሚፈተኑ ይሆናል:: 3.✅ረቡዕ ሰኔ11, ሂሳብ እና አካባቢ ሳይንስ እስከ 9:00 የሚፈተኑ ይሆናል:: 4.✅ ሐሙስ ሰኔ12 እስከ 4:30 ሰዓት የመጨረሻውን ፈተና ግብረግብ ተፈትነዉ የሚያጠናቅቁ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን::   ት/ቤቱ

photo content

photo content
+3

photo content
+4

ለ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ስለሚኒስትሪ ፈተና ሕግና መመሪያ,የተፈታኝ ተማሪ መብትና ግዴታ, መደረግ ስለሚገባው ቅድመ ዝግጅትና ጥንቃቄ  እንዲሁም ተማሪዎች በራስ የመተማመን ስነ-ልቦና ላይ እና የሞራል መነሳሳት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና ገለፃ (Orientation) ተሰጠ::

photo content

photo content