Bashewam Primary & Junior School 1-8
Ir al canal en Telegram
2 747
Suscriptores
-224 horas
+207 días
+4230 días
Archivo de publicaciones
Repost from Ministry of Education Ethiopia
+2
የ2018 ዓ.ም. ትምህርት ቤቶች ከመስከረም 05/2018 ዓ.ም ጀምሮ የመማር ማስተማር ሥራ ይጀምራሉ ፤ትምህርት ሚኒስቴር
ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ሞባይል ስልክ ፣ ታብሌትና ኤሌክትሮኒክስ ቁሰቀቁሶችን ይዞ ትምህርት ቤት መምጣት ተከልክሏል፡፡
----------------------------------------
(ጳጉሜን 01/2017 ዓ.ም) የ2018 የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤቶች አከፋፈት አስመልክቶ ትምህርት ሚኒስቴር ከክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ጋር የበይነ-መረብ ምክክር ባደረገበት ወቅት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ እንደገለጹት የ2018 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ ሰኞ መስከረም 5/ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ይጀመራል።
በትምህርት ካሌንደሩ መሠረት ዓርብ መስከረም 2 / 2018 ዓ.ም. ትምህርት ቤቶች ክፍት ሆነው መምህራንና ተማሪዎች ውይይት የሚያደርጉበትና መስከረም 5/2018 ዓ.ም ደግሞ በይፋ ለሚጀመረው የትምህርት ስራ ቅድመ ዝግጅት የሚያደርጉበት ቀን መሆኑንም ክብርት ወ/ሮ አየለች አስታውቀዋል፡፡
በ2018 የትምህርት ዘመን ባለፈው ዓመት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ጨምሮ ሁሉም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናትና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ወላጆች፣ መምህራንና የዘርፉ ባለድርሻዎች የጀመሩትን የንቅናቄ ተግባር አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባና የትምህርት ቤት ምዝገባም እስከ መጨረሻው ቀን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/19VhCdzuyH/
Repost from Ethio Entrance Zone
New Curriculum Teacher Guides from Grade 1- 12
Repost from N/a
በመሆኑም ሁሉም ት/ቤቶች መምህራን በዓመታዊ ዕቅዳቸው ከወዲሁ ለየትምህርት ይዙቱ ተስማሚ የሆኑ የማስተማሪያ ዘዴዎችን እየለዩ ማካተት እንዳለባቸው፤ በተጨማሪም
@ በፈተና ቢጋር አዘገጃጀት፣
@ በጥናትና ምርምር፣
@ በተከታታይ ምዘና፣
@ በተከታታይ ሙያ ማሻሻያ/ተሙማ/፣
@ በትምህርት ዕቅድ አዘገጃጀትና በሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ከወዲሁ ግንዛቤ እየፈጠሩ ወደ ስራ ማስገባት ያስፈልጋል።
Repost from N/a
+3
ቀን 28/12/2017 ዓ.ም
የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሠጠ
በዛሬው እለት በባሸዋም የመጀመሪያና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራንና ር/መምህራን በወረዳ 13 ትምህርት ፅ/ቤት ሚኪሊላንድ ክላስተር አስተባባሪ ሱፐርቫይዘር በሆኑት አቶ ስምዖን አለኸኝ ስልጠና ተሠጥቷል።
በስልጠናው:-
1. አሳታፊ የማስተማር ዘዴ ምንነት፣ዓይነቶች፣ጠቀሜታውና አተገባበርና
2. የፈተና ቢጋር አዘገጃጀት የተካተቱ ሲሆን፣ መምህራን ከመምህር ተኮር የማስተማር ዘዴ ወጥተው ተማሪ ተኮር የማስተማር ዘዴን ተግባራዊ በማድረግ የተማሪዎችን ውጤት በተሻለ መልኩ ማሻሻል እንደሚችሉ ገልጸዋል።
መምህራን በዕለታዊ ዕቅዳቸው ለትምህርት ይዘቱ ተስማሚ የሆኑ 3 እና በላይ የማስተማሪያ ዘዴዎችን በማካተት ማስተማር እንዳለባቸው ተግባብተናል።
በሥልጠና ከቀረቡ የማስተማሪያ ዘዴዎች መካከል:-
1. የአዕምሮ ቁስቆሳ/brainstorming/
2. ሠርቶ ማሣየት/ demonstration/
3. ፍትነታዊ/experimental
4. ጅግሳዉ ቡድን ውይይት
5. ፒራሚድ ቡድን ውይይት
6. የፕሮጀክት ስራ
7. የግል ስራ
8. ስዕልና ሰንጠረዥ
9. ማቅረብና በከፊል ማስተማር
10. ምክንያትና ውጤት
11. ፍላሽ ካርድ
12. አዕምሯዊ ትስስር
13.ጉብኝትና
14. ክርክር ዘዴዎችን እንደ ተማሪዎች የመማሪያ ምርጫ በአንድ ክፍለ ትምህርት 3ና በላይ የሆኑ የማስተማሪያ መንገዶችን አቅዶ መተግበር አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝበዋል።
ወደ ተግባር ሲገባ ር/መምህራን የቅርብ ክትትል እያደረጉ ግብረ መልስ ሊሠጡን ይገባል ብለዋል።
የፈተና ቢጋር አዘገጃጀት ላይም ፈተናዎች ሳይንሣዊ በሆነ መልኩ መዘገጀት እንዳለበት ተገንዝበናል ወደ ተግባርም መቀየር ይጠበቅብናል ብለዋል።
ር/መራኑም መ/ራን በወሠዱት ስልጠና መሠረት ወደ ተግባር እንዲገቡ ግልጽ መመሪያ ሠጥተዋል።
Repost from Bashewam pre-primary
ማሳሰቢያ
ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪ ወላጆች በሙሉ
እንደሚታወቀው በ14/12/2017 ዓ.ም ለልጅዎ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን እንዲያስረክቡ ማሳሰቢያ ልከን ነበር፡፡ ያላስረከባችሁ ወላጆች ትምህርት ሲጀመር ከህፃናት ጋር አብረን ቁሳቁስ ለመረከብ ስለማንችል፡፡ በተጨማሪም መምህራኖች አጠቃላይ ስብሰባ እና ስልጠና በ26/12/2017 ዓ.ም እና 27/12/2017 ዓ.ም ስለሚገቡ እስከ 23/12/2017 ዓ.ም ከ2፡30 – 6፡30 የምንረከብ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
Repost from Bashewam pre-primary
ማሳሰቢያ
ለባሸዋም ቅድመ አንደኛ ደረጃ (አፀደ ህፃናት) ት/ቤት ወላጆች በሙሉ
ለ2018 ዓ.ም ለልጅዎ ከ15/12/2017 ዓ.ም - 16/12/2017 ዓ.ም የሚያስፈልጉትን ቁሳቁስ ዝርዝር መጥተው ከርዕሰ መምህር ቢሮ እንዲወስዱ እያሳወቅን የማስረከቢያ ጊዜ ከ19/12/2017 ዓ.ም - 21/12/2017 ዓ.ም መሆኑን እንገልፃለን፡፡
Repost from Bashewam pre-primary
ማሳሰቢያ
ለባሸዋም ቅድመ አንደኛ ደረጃ (አፀደ ህፃናት) ት/ቤት ወላጆች በሙሉ
ለ2018 ዓ.ም ለልጅዎ ከ14/12/2017 ዓ.ም - 15/12/2017 ዓ.ም የሚያስፈልጉትን ቁሳቁስ ዝርዝር መጥተው ከርዕሰ መምህር ቢሮ እንዲወስዱ እያሳወቅን የማስረከቢያ ጊዜ ከ19/12/2017 ዓ.ም - 21/12/2017 ዓ.ም መሆኑን እንገልፃለን፡፡
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
