cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

መርዕድ - አማራ

. . አብዮተኛ አማራ Capastrist... . .

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
1 092
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

Photo unavailableShow in Telegram
የሰላም ሚኒስትር ደኤታ የሆኑት አቶ ስዩም መስፍን ከሃገር መጥፋታቸው ተሰማ። ሚኒስትሩ ከሃገር ከጠፉ ዛሬ 5 ቀናቸው ሲሆን አሜሪካ መግባታቸውም ተሰምቷል። የደብረ ማርቆስ ከተማ ከንቲባ የሆኑት አቶ ይባረክም ከሃገር መጥፋታቸው ተሰምቷል። ምክትል የመንግስት ተጠሪ የሚባሉትም አቶ አሰማኸኝ አስረስ ከሃገር መውጣታቸው እና መጥፋተቻው ተነገሮኛል።
Mostrar todo...
👍 13
Photo unavailableShow in Telegram
የመምህራን ብሔር ፎርም...? የአዲስ አበባ አማራ መምህራን ጥንብ አንሳው እየዞራቸው ነው። . . .
Mostrar todo...
👍 12
By the way .... በዚህ ጽሑፍ ላይ ከ 1 ሚሊየን በላይ የትግሬ ወጣት ያለቀው በሕወሓት የተነሳ መሆኑን አምነዋል። ግን በአማርኛ ሲጽፉ አማራን ብቻ ተጠያቂ ያደርጋሉ.... በበታችነት ስሜት የተነሳ አማራ ባልዋለበት ይከሰሳል።
Mostrar todo...
👍 5
Photo unavailableShow in Telegram
ከፈረሱ አፍ ስሙትማ.😂 ክፍፍሉ ከሕውሐት እና ከጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች አልፎ ኤሊቶች ጋር ደርሷል። ደግሞ አማራ እንዳይሰማ ይላሉ...translator ተጠቅማችሁ አንብቡ የሚፅፉትን። 👇👇 @MereidAmhara @MereidAmhara
Mostrar todo...
👍 4
ሰበር ህውሓት..! አንድ የስራ አስፈፃሚ አባል እና ሶስት የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ከስራ ታግደዋል። ክፍፍሉ እየሰፋ ነው። በርቱ
Mostrar todo...
👍 8
02:04
Video unavailableShow in Telegram
#የጀግናው ሻምበል መማር ጌትነት የመታሰቢያ ቀን ጥቅም 17/2/2016 ዓ/ም ነፍስህ በሰላም ትረፍ!!! 😭😭😭😭
Mostrar todo...
34.48 MB
😢 14 1
Photo unavailableShow in Telegram
በ18 ቢሊየን ብር በአዲስ አበባ በ11 ክፍለ ከተማ የአርቲስቶች መንደር ሊገነባ ነው! የአዲስ አበባ ሕዝብ የሚቀምሰው አጥቷል። ቤቱ ፈርሷል። ደሞዙ ቆሟል። ልጆቹ ትምህርት አቁመው ሴተኛ አዳሪ መሆን ጀምረዋል። እነ አጅሬ ግን ከድሃ ደሞዝ በተሰበሰበ ግብር ምን አይነት ፕሮጀክት እንደሚያቅዱ ተመልከቱ!?
Mostrar todo...
👎 4👍 3
የሜዲያው ጦርነት ከግንባሩ ጦርነት ያልተናነሰ ነው #ግርማካሳ መረጃ ኃይል ነው፡፡ ያልነቃ ህዝብ አይነሳም፡፡ ያልተነሳ ህዝብ አይደራጅም፡፡ ያልተደራጀ ህዝብ መብቱን አያስከብርም፡፡ ሁልጊዜ አንገቱን ደፍቶ ነው የሚኖረው፡፡ ዘረኛው አገዛዙ ይሄን ያውቃል፡፡ ህዝብን ለማታለል፣ ለማደንዘዝ፣ለማወናበድ ያላደረገው ነገር፣ ያልፈነቀለው ድንጋይ የለም፡፡ ህዝብ መረጃ እንዳያገኝ፣ ሕዝብ እውነቱን እንዳያውቅ፣  ማድረግ ትልቁና ቀዳሚው ስራ አድርጎ ነው የወሰደው፡፡ ኢተኖ ፋሺስቱ አገዛዙ የአገሪቱን ሃብት፣ ገንዘብ የተቆጣጠረ ነው፡፡ ትልቅ ባጀት መድቦ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሶሻል ሜዲያ ሰራዊት አሰማርቷል፡፡ በብሮድካስቲን አገልግሎት ፍቃድ ተሰጥቷቸው ይንቀሳቀሱ የነበሩት ሙሉ ለሙሉ አጥፍቷቸዋል፡፡ በአገር ቦእት ያሉ ጋዜጠኞች በብዛት ታስረዋል፡፡ኢትዮጵያ ውስጥ የግል ሜዲያ፣ ነጻ ፕሬስ ብሎ ነገር የለም፡፡ ያሉት የግል ሜዲያዎች፣  እንደ ቃና፣ ኤቤኤስ፣ አርት ቲቪ በዋናነት አገዛዙን በማያስከፋ መልኩ፣  በመዝናኛ ፕሮግራሞች ላይ ነው ያተኮሩት፡፡ በሜዲያው ጦርነት አገዛዙ ያስቸገረው ነገር ቢኖር፡ 1ኛ እንደ ኢትዮ360፣ አዲስ ድምጽ፣ ኢትዮ 251  ያሉ በርካታ የዩቱብ ሜዲያዎች፣ ታዋቂ የፌስ ቡክ፣ ቴሊገራምና ትዊተር ብሎገሮች ናቸው፡፡  ዩቱብን በተመለከተ፣ የማይፈልጓቸው የዩቱብ ሜዲያዎች ማዘጋት የቻሉበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ የመረጃ ቲቪ ዩቱብ ወደ 300 ሺህ ሰብስክራይበር ነበረው፤ መጀመሪያ የተዘጋው እርሱ ነበር፡፡  ኢትዮ360፣ አዲስ ድምጽ ፣ መረጃ ቱዴይ፣ እያለ የብዙዎች ዩቱቦችም ተዘጉ፡፡  ኩሽ ሜዲያ፣ ዛራ ሜዲያ፣ ትግራይ ሜዲያ ሃውስ፣ OMN የመሳሰሉ  ዩቶቦቻቸው ሲዘጉ አናይም፡፡ ለምን የአማራው ማህበረሰብ እያደረገ ያለውን ትግል ለህዝብ የሚዘግቡ ዩቱቦች ይዘጋሉ ? ብዙዎችን ግራ ያጋባ ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ መልሱ ቀላል ነው፡፡ የአገዛዙ ሰዎች፣ ገንዘብ ከፍለው፣ ሶስት ፣ አራት ሺህ ሰዎች በአንዴ ለዩቱብ ሪፖርት እንዲያደረጉ ያስደረጋሉ፡፡ ከዚያም ዩቱብ፣  ሪፖርተ የተደረገባቸው  ፕሮግራሞች፣  ከዩቱብ ስታንዳርድ ውጭ መሆኑን የማጣራት ስራ ይጀምራል፡፡ ዝግጅቶቹ በአማርኛ ስለሆኑ ወደ አስተርጓሚዎች ይላካል፡፡ ችግሩ ያለው እንግዲህ እዚያ ጋር ነው፡፡ አስተርጓሚ ሆነው የሚሰሩት ወያኔዎች፣ ኦነጎችና ብልጽግናዎች ብቻ ሳይሆን፣ ከፍተኛ ገንዘብ ከአገዛዙ የተከፈላቸው ናቸው፡፡ 2ኛ ሌላው ትልቁ የአገዛዙ ሕመም፣ የመረጃ ቲቪ ነው፡፡መረጃን ቲቪን ከአየር/ሳተላየት ለማውረድ  እጅግ በጣም ለፍተዋል፡፡  ግን እስከ አሁን አልቻሉም፡፡ ዩቱብ እነ ኢትዮ360፣ አዲስ ድምጽ የመሳሰሉትን ቢዘጋም፣ እነዚህ ፕሮግራሞች በሳተላይት ወደ ህዝብ እየደረሱ ነው፡፡  በነዚህ  ጉዳዮች ላይ ሁለት ነገር ማድረግ እንችላለን፡፡ አንደኛው የመረጃ ቲቪን መደገፍ ነው፡፡ መረጃ ቲቪን አየር ላይ ማድረጉ የትግሉ ትልቅና አንገብጋቢ ጉዳይ ነው፡፡ መረጃ ቲቪ ከሌለ ኢትዮ360፣ አዲስ ድምጽ ሌሎች ዝግጅቶችን ህዝብ መስማት አይችልም፡፡  የፊታችን ቅድሜና እሁድ ( October 7  እና 8 )ለመረጃ ቲቪ ድጋፍ የማሰባሰብ ዘመቻ ይደረጋል፡፡ ሁላችንም ለዚያ እንዘጋጅ፡፡ ለዩቱቡ ችግር ደግሞ፣  ዩቱብ ከሌሎቻችንን መስማት መቻለል አለበት፡፡ እነርሱ ዩቱቡቾን ለማዘጋት ከሰሩ፣ እኛ እንዴት ለማስከፈት የበለጠ መስራት ያቅተናል ? በዚህ ጉዳይ ላዩ ፔቲሽን እየተሰበሰበ ነው፡፡ እንፈርም፡፡ እስከ አሁን ወደ 4 ሺህ ወገኖች ፈርመዋል፡፡ ይህ ቁጥር መቶ ሺህ መድረስ አለበት፡፡https://www.change.org/p/uphold-freedom-of-expression-and-fair-treatment-for-ethiopian-amhara-medias/u/31877464?recently_published=true%E1%89%B5T
Mostrar todo...
ጦርነት የተከፈተበትን የአማራን ድምጽ ለማፈን የተወሰዱ እርምጃዎች፤ሚዲያዎቹ ተመርጠው የታገዱበት ምክንያትና የእኛ ሚና

በፋሺስታዊው የኦሮሙማ ቡድን በነገደ አማራ ሕዝብ ላይ በታወጀው ወታደራዊ ኢኮኖሚያዊና መረጃዊ ጦርነት የአማራን ድምጽ ለመዝጋት የተወሰዱ የእፈና እርምጃዎች ውድ ወገኖች፣ ውድ እድምተኞችና ውድ አንባቢያን በሙሉ፣ በያላችሁበት ሁሉ ሰላማችሁ የተጠበቀ ይሁን እያልኩ ወደዛሬው አርእስት ሳመራ የአማራን ሕዝብ ድምጽ ለማፈን በተወሰዱ ሕገ ወጥ የአፈና እርምጃ ከተዘጉት ሚዲያዎች ውስጥ የሶስቱን ሚዲያዎችን ታሪክና ለምንና እንዴት ኢላማ እንደተደረጉ በመግለጽ በመደምደሚያዬ ላይ ይህንን ጥቃት ከመከላከልና ብሎም ከማስቀረትም አንጻር የዚህን ፔቲሽን ሚናን በመጠቆም እቌጫለሁ - ውድ ግዜያችሁን ሰውታችሁ በዚህ ዘመቻ ላይ በመሳተፍ ፔቲሽኑን በፊርማ፣በማሰራጨት፣ ስርጭቱ እንዲሰፋና እንዲጨምር ደግሞ በገንዘብ አስተዋጾኦ ላደረጋችሁና እያደረጋችሁ ላላችሁ ውድ ወገኖች በሙሉ የከበረ ልባዊ ምስጋናዬን እየገለጽኩ አሁንም ፔትሺኑ የተከፈተበትን ዓላማ ግብ ይመታ ዘንድ የእናንተ አስተዋጾኦና ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ መሆኑን በመግለጽ ተሳትፎእችሁን አጠንክራችሁ እንድትቀጥሉ በድጋሚና በታላቅ አክብሮት አደራ እላለሁ። ውድ ወገኖች ለምንድነው ስርዓቱ የአማራን ድምጾች ማፈን የፈለገው ?? በተለይም ተመርጠው ከተዘጉት በርካታ ሚዲያዎች ውስጥ ይህ ፔቲሽን ለምን እና እንዴት አድርጎ ነው የሶስት ሚዲያዎችን - ኢትዮ360 ሚዲያ ፣ የጋዜጠኛ አበበ በለው አዲስ ድምጽና የባሮን ቲውብ ቻናል መርጦ ለማቅረብ የበቃው የሚሉትን ጥያቄዎች የሚመልስ ምጥን ዘገባን በማስቀደም ልጀምር፣ ♦️ የአማራን ድምጽ ለማፈን ለምን አስፈለገ?? እንዴትስ ተቻለ?? ማንኛውም አፈና ተግባራዊ ሆኖ ተፈጻሚ የሚሆነው  የእንድ አፋኝ ቡድን፣ ኋይል ድምጹ እንዳይሰማ ማፈን አለብኝ ብሎ በሚወስደው የአፈና እርምጃ ምክንያት ብቻ የሚከሰት ክስተት ሳይሆን የታፋኙ ወገን አፈናውን ተቀብሎ…

👍 9🥰 1
ሰበር ዜና! በጠቅላላ ተማርከዋል! የወረኢሉ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና ምክትሉን ጨምሮ፤ የጃማ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና ምክትሉን ጨምሮ እንዲሁም የድርጅት ኃላፊውን ጨምሮ፤ የከላላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና ምክትሉን ጨምሮ እና ሌሎች የብልፅግና ሆዳደር አመራሮች ለስብሰባ ወደ ደሴ በሚጓዙበት ሰዓት በሸዋ ፋኖዎች በቅጥጥር ስር ውለዋል። ☀️የአማራ ፋኖ በየትኛውም ግንባር ስላለበት ሁኔታ የተጣራ መረጃ ለማግኘት ይቀላቀሉን። 👇👇 @MereidAmhara @MereidAmhara
Mostrar todo...
👏 13👍 2
" የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል " - ትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ  ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር ነገ መስከረም 28/2016 ዓ.ም ከቀኑ 6 ሰዓት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ ገልጿል።
Mostrar todo...
1
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.