917
Suscriptores
Sin datos24 horas
+47 días
-330 días
Archivo de publicaciones
መጋቢት 18/2018 ዓ.ም
የሊዝ ጫረታ ማስታወቂያ
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የኢንጌ ማዘጋጃ ቤት በአዋጅ በተሠጠው ተግባርና ሀላፊነት ለመኖሪያ የሚውሉ ቦታዎች ለ9ኛ ዙር በሊዝ ጨረታ አወዳድሮ ለማስተላለፍ ዝግጁቱ አጠናቆ ተወዳዳሪዎችን ማወዳደር ይፈልጋል።
የኢንጌ ማዘጋጃ ቤት የ9ኛ ዙር የሊዝ የመሬት ጨረታ ይመለከታል
1.የመኖራያ ብዛት 20 የጨረታ ሰነድ መግዥያ ዋጋ 500 የሊዝ መናሻ ዋጋ 125 ሲሆን $.ጨረታው የሚጀመርበት ቀን 18/ 07/2018 ዓ.ም ጨረታው የሚዘጋበት /የሚያልቅበት ቀን 01/08/2018 ዓ.ም እስከ 10:30 ሰዓት ነው።
የጨረታው አሸናፊ የሚለይበት 05/08/2018 ዓ.ም 3:00 ሰዓት መሆኑን እናሳውቃለን!!!
ለተጨማሪ ዝርዝር መረጃ በምስሉ ላይ መመልከት ይችላሉ ሲል መረጃው ያደረሰን የኢንጌ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ነው።
መጋቢት 18/2018 ዓ.ም
በነዳጅ ምርቶች ግብይት ላይ ስለሚፈጸሙ ህገ-ወጥ ድርጊቶችና የሚያስከትሏቸው ጠንካራ የወንጀል ቅጣቶችን ምን ያህል ያውቃሉ?
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የነዳጅ ምርቶች የግብይት ስርዓትን ለመደንገግ በወጣው አዲስ አዋጅ ቁጥር 1363/2017 መሰረት፣ በዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመግታት የሚያስችሉ ጠንካራ የቅጣት እርምጃዎች መዘርጋታቸው ይታወቃል።
በአዋጁ መሰረት በዋናነት የተለዩት ወንጀሎችና ቅጣቶች የሚከተሉት ናቸው፦
1. ህገ-ወጥ ክምችትና የግብይት ስርዓትን መጣስ
የነዳጅ ውጤቶችን ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ያከማቸ ወይም ከግብይት ስርዓቱ ውጭ ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ሰው፦
👉 የተያዘው ነዳጅ እንዲወረስ ይደረጋል፤
👉ከ3 እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እና፤
👉ከ350 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር በሚደርስ መቀጮ ይቀጣል።
2. ነዳጅን ከባዕድ ነገር ጋር መቀላቀል
የነዳጅ ውጤቶችን ሆን ብሎ ከባዕድ ነገሮች ጋር በመቀላቀል ለግብይት የሚያቀርቡ ግለሰቦች፦
👉 ነዳጁ እንዲወገድ ተደርጎ ከ 5 እስከ 7 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት፤
👉ከ 350 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይጠብቃቸዋል።
3. ከመደበኛው የዋጋ ተመን በላይ መሸጥ
መንግስት ከተመነው የመሸጫ ዋጋ በላይ የሚሸጡ የግብይት ተዋናዮች፦
👉 ለመጀመሪያ ጊዜ ጥፋት፦ ከ300 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር መቀጮ፤
👉ለተደጋጋሚ ጥፋት፦ ከ3 እስከ 5 ዓመት ጽኑ እስራት እና ከ300 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር መቀጮ።
4. የኮንትሮባንድና የማጓጓዣ መስመር ጥሰት
ነዳጅን ከተፈቀደው መስመር ውጭ ማጓጓዝ፣ ካልተፈቀደ ቦታ ማራገፍ ወይም ወደ ጎረቤት ሀገር በኮንትሮባንድ ማሸጋገር፦
👉ነዳጁ ተወርሶ ከ 5 እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት፤
👍 ከ400 ሺህ እስከ 700 ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል።
5. የቴክኒክና የዲጂታል አሰራር ማጭበርበር
👉የልኬት መሣሪያዎች (ሜትር) ማጭበርበር፦ ፕሎምፕ የቆረጠ ወይም ልኬት ያዛባ ከ 3 እስከ 7 ዓመት ጽኑ እስራትና እስከ 500 ሺህ ብር መቀጮ።
👉 የዲጂታል ስርዓት መጣስ፦ እስከ 2 ዓመት እስራትና እስከ 300 ሺህ ብር መቀጮ።
ህጉ በዋናነት የታለመው በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ያለውን ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውር ለመግታትና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሲሆን፤ በተለይም የዲጂታል ግብይት ግዴታ መደረጉ ለቁጥጥሩ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
በዘርፉ ላይ የተሰማሩ የንግዱ ማህበረሰብ አባላትም ሆኑ ግለሰቦች፣ አዋጁን አክብረው በመስራት ራሳቸውን ከእስራትና ከከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ መጠበቅ ይገባል።
የህግ የበላይነትን ማክበር የሁሉም ግዴታ ነው።
መጋቢት 18/2018 ዓ/ም
በሰባተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ (ኮኪር ምርጫ ክልል) የሚወዳደሩ እጩዎች በመሀል አምባ ከተማ ተገኝተው የመራጭነት ካርድ ወሰዱ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህጻናት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ነጅብያ ማህሙድ ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ ስራስኪያጅ አቶ አ/ሃፊዝ ሁሴን ፣የጉራጌ ዞን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን ሴቶችና ህጻናት ኃላፊ ወይዘሮ ፈትያ መህዲ በሰባተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የመራጮች ካርድ በሚወዳደሩበት የምርጫ ክልል ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ወስደዋል።
ሁሉም ዜጋ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት ለመምረጥ ፈጥኖ የምርጫ ካርድ መያዝ እንደሚጠበቅበት ገልፀዋል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በእጩነት በሚወዳደሩበት በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ (ኮኪር ምርጫ ክልል) የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ሁሉም ዜጋ የወደፊት እጣ ፈንታውን መወሰን እንዳለበትም ተወካዮቹ አስገንዝበዋል።
ምርጫው ሰላማዊ፣ዴሞክራሲያዊና ታአማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሁሉም ዜጋ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
መጋቢት 16/2018 ዓ/ም
የ5ተኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከመጋቢት 18 እስከ 21/2018 ዓ.ም ለተከታታይ አራት ቀናት
ቤት ለቤት እንደሚሰጥ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ጽ/ቤቱ በወረዳው ለሚሰጠው 5ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ አስመልክቶ ለጽ/ቤት ባለሙያዎችና ለሱፐቫይዘሮች ኦረንቴሽን መስጠቱን አክሎ ገልጿል።
በወረዳው ከ23 ሺ 061 በላይ እድሜያቸው ከ5 አመት በታች ለሆኑ ህፃናት 5ተኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በቤት ለቤት ዘመቻ እንደሚሰጥ ተመላክቷል።
በዘመቻው ከፖሊዮ ክትባት ባሻገር ሌሎችም ክትባት ጀምረው ያቋረጡ ና ክትባት ያልጀመሩ ህፃናት መለየትና እንዲከተቡ ማድረግ፣የከንፈርና የላንቃ መሰንጠቅ፣ የቆልማማ እግር ችግር ፣የማህፀን ውልቃትና የፊስቱላ ችግር ያለባቸው እና የስርአተ ምግብ ልየታ ፣zero dose እና under dose በዘመቻው ተቀናጅቶ የሚሰጥና ህክምና እንዲያገኙና ከዚህም ጎን ለጎን የመለየት ስራ የሚሰራ ይሆናል።
መጋቢት 15/2018 ዓ/ም
የማህበረሰቡን ንጹህ መጠጥ ውኅ ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ውኅና ማዕድንና ኢነርጂ ጽ/ቤትገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ውኅና ማዕድንና ኢነርጂ ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ሩብ ዓመት የዜጎች ቻርተር እና የህዝብ ክንፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ።
የዕለቱ የመወያያ ሰነድ በፅ/ቤቱ ልማት ዕቅድ ባለሙያ በወ/ሮ አበራሽ ታደሰ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓበታል።
የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ውኅና ማዕድን ኢነርጂ ፅህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሙደሲር ንጉሴ በመድረኩ እንደገለጹት በተቋሙ በግማሽ አመቱ በማዕድን ፣በመስኖ ልማት ፣ በንጹህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት እና በታዳሽ ሀይል በሌሎችም ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
የወረዳው ማህበረሰብ ንጹህ የመጠጥ የውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት የንጹህ የመጠጥ ውሀ ሽፋን በማሳደግ ህዝቡ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አመላክተዋል።
የወረዳው የውሃ አቅርቦት ሽፋን ለማሳግ የወረዳው መንግስት፣ ከባለሀብት ፣ከረጂ ድርጅቶች እና መንግስት በጀት በመመደብና በጋራ በመስራት በወረዳ ያሉ ጥልቅ የውሀ ጉድጓድ ከመብራት በማገናኘት ፣ መስመሮች በማስፋትና በመጠገን ከፍተኛ ስራ በመስራት የማህበረሰቡን የንጹህ ውሃ ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለመፍታት እየተሰራ ነው ብለዋል።
አቶ ሙደሲር አክለውም በየቀበሌው በሚወጡ የማዐድን ገቢ ቁጥጥር ማድረግ ፣ለመስኖ ልማት ግንባታ፣ ማህብረተሰቡ የንጹህ ውሀ አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ እና በሌሎችም በጽ/ቤቱ ታቅዶ በሚሰሩ ሰራዎች ባለድርሻ አካላት እገዛ ሊያደርግ እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በተለያዩ ቀበሌዎች ተበላሽተው የነበሩ ባዮጋዝ ተጠግጠው ወደ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ፣የመስኖ ስራ አዳዲስ ቀበሌዎች መስፋፋት አንዳለበት ፣ንጹህ የመጠጥ ውሀ ምርመራ ማድረግ እንደሚያስፈልግ በመግለጽ የማህበረሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሀ ችግር ለመፍታት ከባለሀብቶችና ከረጂ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ ያለው ስራ የተሻለ በመሆኑ በቀጣይም በሌሎች አካባቢዎች ችግሮች እንዲፈቱ የበለጠ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት እንዲሁም በማዕድን ዘርፍ የተሰማሩ አካላት በአግባቡ ስራቸው እንዲሰሩ የማድረግና ለወረዳው መንግስት ገቢን በአግባቡ እንዲገባ ከማድረግ አንጻር ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ እንደሚገባ ገልጸዋል።
በመድረኩ የዜጎች ቻርተር እና የህዝብ ክንፍ አባላት እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
መጋቢት 13/2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሂደት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የሚደረገው የመራጮች ምዝገባ በዲጂታልና በመደበኛ ማንዋል በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች የምዝገባ ሂደቱ በተጠናከረ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል።
መጋቢት 12/2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ውስጥ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች፣7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ ይገኛል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የወረዳው ነዋሪዎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም ወደ መራጮች መመዝገቢያ ጣቢያ በመሄድ የመራጮች ካርድ እየወሰዱ ነው።
መጋቢት 11/2018 ዓ/ም
ለምርጫ የተመዘገቡ ዜጎች ቁጥር 18 ሚሊየን 556 ሺህ 337 ደረሰ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እስከ ትናንት ባካሄደው የመራጮች ምዝገባ 18 ሚሊየን 556 ሺህ 337 ተመዝግበዋል፡፡
ቦርዱ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫን የመራጮች ምዝገባ በጊዜ ሠሌዳው መሠረት ከየካቲት 28 እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በማከናወን ላይ ይገኛል።
በዚህም እስከ መጋቢት 10 ቀን 2018 ዓ.ም በማንዋልና በዲጂታል አማራጭ ባከናወነው የመራጮች ምዝገባ 18 ሚሊየን 556 ሺህ 337 መራጮች መመዝገባቸውን አስታውቋል።
ከተመዘገቡት መራጮች ውስጥ 10 ሚሊየን 133 ሺህ 639 ወንድ ሲሆኑ፤ 8 ሚሊየን 422 ሺህ 698 ሴት መሆናቸውን ቦርዱ ባወጣው መረጃ አመላክቷል።
ቦርዱ ለመራጮች ምዝገባ አወዳድሮና ገለልተኝነታቸውን በፖለቲካ ፓርቲዎች አስተችቶ ያሰለጠናቸውን 187 ሺህ 28 የምርጫ አስፈጻሚዎች ማሰማራቱንም አስታውሷል።
(ኤፍ ኤም ሲ)
የዒድ ደስታ ለሁሉም፤ የዘካተል ፊጥር ድንጋጌና ማኅበራዊ ፋይዳ
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የረመዷን ፆም መጠናቀቅን ተከትሎ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ የዒድ አል ፊጥር በዓልን ከማክበሩ በፊት ሊወጣው የሚገባው "ዘካተል ፊጥር" ሃይማኖታዊ ግዴታ መሆኑን የእስልምና አስተምህሮ ያዛል።
ይህ መልካም ተግባር ችግረኞች በዒድ ዕለት እጃቸውን ለልመና እንዳይዘረጉና የዕለቱ የደስታ ተካፋይ እንዲሆኑ ታስቦ የተደነገገ ሲሆን፣ በፆም ወቅት ለተከሰቱ ጥቃቅን ጉድለቶችም ማሟያ ሆኖ ያገለግላል።
ይህ የዘካ ዓይነት አቅም ባለው ማንኛውም ሙስሊም ላይ ግዴታ ሲሆን፣ በጾታም ሆነ በዕድሜ ሳይገደብ ለሁሉም የቤተሰብ አባላት መውጣት ይኖርበታል።
የዒድ ቀን ፀሐይ ከመጥለቋ በፊት የተወለደ ሕፃንም በዚህ ግዴታ ውስጥ የሚካተት ሲሆን፣ ለራሱና ለቤተሰቡ የዒድ ቀንና ሌሊት የሚበቃ ቀለብ ያለው ማንኛውም ሙስሊም ዘካውን የማውጣት ኃላፊነት አለበት።
ይህም ድሆችም ጭምር ተቀብለው ለሌላው የሚሰጡበትን ሁሉንም የሚያሳትፍ የልግስና ሥርዓት ይፈጥራል።
ለዘካተል ፊጥር የሚውሉ የእህል ዓይነቶች በአካባቢው ለቀለብነት የሚያገለግሉና ረዘም ላለ ጊዜ የማይበላሹ እንደ ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ቴምርና ዘቢብ መሆን ይገባቸዋል።
መጠኑም በሐዲሥ በተቀመጠው ስፍር መሠረት ወደ ኪሎግራም ሲቀየር ለአንድ ሰው በአማካይ 2.5 ኪሎ ግራም ገደማ ሲሆን፣ ለምሳሌ 10 የቤተሰብ አባላት ያሉት ሰው 25 ኪሎ ግራም እህል ማውጣት ይኖርበታል።
ልዩ አንገብጋቢ ሁኔታዎች ካልገጠሙ በቀር ዘካውን በገንዘብ ማውጣት የማይመከር ሲሆን፣ በእህል ተለክቶ ለችግረኛ ሙስሊሞች ብቻ እንዲሰጥ በጥብቅ ይመከራል።
የዘካተል ፊጥር ትክክለኛ ጊዜ የረመዷን ወር ተጠናቆ የዒድ ሌሊት ከገባበት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዒድ ሶላት መጀመሪያ ድረስ ቢሆንም፣ ለሚሰበስቡ አካላት ለማድረስ እንዲመች አንድ ወይም ሁለት ቀን ቀድሞ መስጠት እንደሚቻል ተገልጿል።
ይህ ሥርዓት ሙስሊሞች በረመዷን ያገኙትን መንፈሳዊ ጥንካሬ ወደ ተግባራዊ መረዳዳት በመቀየር፣ ማኅበራዊ ትስስርን የሚያጠናክሩበትና የበዓሉ ደስታ በሁሉም ቤት እንዲገባ የሚያደርጉበት ዋነኛው መንገድ ነው።
EBC
