1 091
Suscriptores
+324 horas
+257 días
+1730 días
Archivo de publicaciones
በአስተዳደሩ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ለሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች አመራር ፑል በአንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት ላይ የግንዛቤ መፍጠሪያና ወደ ተግባር ማስገቢያ የስልጠና መድረክ መካሄድ ጀመረ።
“አንድ እቅድ፤ አንድ ሪፖርት” የአሠራር ስርዓት ከፌ.ደ.ራ.ል በተሰጠው አቅጣጫ ተግባራዊ እንዲደረግ በተቀመጠው መሰረት እንደ አስተዳደር በአብዛኛው ተቋማት ላይ ተግባራዊ በመደረግ ላይ እንደሚገኝና ኮሌጆቹንም ወደዚህ ስርዓት ለማስገባት የስልጠና መድረኩ ተዘጋጅቷል፡፡
በዋናነት የአንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት ከዚህ በፊት የተቋማቱ ዕቅዶች በተበጣጠሰ መንገድ ሲታቀዱ የነበረበት እና ከአስቀመጡት ግብ አንጻር የማይመዘኑበት እንዲሁም ውጤትን ለመለካት የማያስችል አካሄድን በመሰረታዊነት ሊፈታ የሚችል ወጥነት ያለው የአንድ ዕቅድ እና የአንድ ሪፖርት የአሰራር ስርዓት መዘርጋት ያስችላል፡፡
በዚህም የአሰራር ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማዘመንም አዲስ ወደ በለጸገው ሶፍት ዌር ከስልጠናው መጠናቀቅ በኋላ በሁለቱም ኮሌጆች የማስገባት ሥራ እንደሚከናወን በቢሮው የፕላን እና ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ አቡ አለማየሁ አስረድተዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 7/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ " የብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ" የአምስት ወራት አተገባበርን በተመለከተ ከወረዳ አንድ ማዕከል አመራሮች እና ባለሞያዎች ጋር የውይይት እና የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡
በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ለዜጎች የሥራ እድልን በመፍጠር አሁን ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር ለመቀነስና የሥራ ባህልን በማጎልበት የሚያስፈልጓቸውን የክህሎት ስልጠናዎች በመውሰድ ወደ ሥራ እንዲሰማሩ በማመቻቸትና ራሳቸውን ከሥራ አጥነት እንዲያላቅቁ ለማድረግና ለመተግበር " የብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ" ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
በዚህም የሚመለከታቸው የቢሮው አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም የወረዳ ሥራ ክህሎት ማስተባበሪያዎች በተገኙበት " የብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ" የመጀመሪያ አመት ትግበራ የወጣቶች በኢንደስትሪዎች ላይ ባለፉት አምስት ወራት የነበረውን የሥራ ላይ ልምምድ የተሰሩ ሥራዎች አፈጻጸም ላይ ሁሉም የወረዳ አንድ ማዕከላት አፈጻጸማቸው ቀርቦ ሰፊ ውይይት በማድረግ በቀጣይ መሠራት በሚገባቸው ሥራዎች ላይ መወያየትና መግባባት መፍጠር ተችሏል፡፡
በመድረኩም ላይ በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኃላፊ አቶ ሰኢድ አሊ በቢሮ እና በአንድ ማዕከላቱ መናበብ የተሰሩ መልካም ሥራዎችን አበረታተው በቀጣይ በአምስት ወራት የተከናወነውን ውጤታማ ሥራ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ወጣቶችን ከስራ ጋር ለዘለቄታው ማስተሳሰር እንዲቻል በቀሩት ጥቂት ጊዜያት ሁሉም ተረባርቦ ሊሰራ እንደሚገባው አሳስበዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከብቃት ጎንለጎን አጠቃላይ የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራውን አጠንክሮ በማስቀጠል ምንያህል የሥራ ዕድል መፍጠር ችለናል የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ መሆን አለበት ያሉ ሲሆን በተለይም የተቋቋመውን የሥራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤቱን በመጠቀም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በመጠቀም ውጤት ለማምጣት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 6/2016 ዓ.ም
ሐረር
በድሬዳዋ አስተዳደር ከሚገኙ የግል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋር የ2016 ዓ.ም አዲስ ሰልጣኞች ቅበላ አፈጻጸም ላይ ውይይት ተደረገ።
በውይይቱ ላይ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ እና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የ2016 የስልጠና ዘመን የአዲስ ሰልጣኞች ቅበላን አስመልክቶ ሰፊ ማብራሪያና የአፈጻጸም አቅጠጫዎች ላይ ገለጻ አድርገዋል ።
በሰልጣኞች ቅበላ ዙሪያ ለሚነሱ ማናቸውም የአፈጻጸም ግድፈት ተጠያቂዎቹ ቅበላውን የሚያከናውኑ ተቋማት መሆናቸውን በማስገንዘብ ህግና ስርዓትን ተከትለው ቅበላውን በመስፈርቱ መሠረት ማከናወን እንደሚገባቸው አፅንዖት ሰጥተው አሳስበዋል።
በዚህም መሠረት የዘመኑ ቅበላ በተከናወነ አንድ ወር ጊዜ ውስጥ የሰልጣኞችን መረጃ በሀርድና በሶፍት ኮፒ ለቢሮው የጥራት ቁጥጥር እንዲያቀርቡ መመሪያ የሰጡ ሲሆን ውይይቱን ከተሳተፉ የግል ኮሌጅ አመራሮች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የሚመለከታቸው ከፍተኛ ባለሙያዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል ።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 6/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
” የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለዜጎች ዕድል ፈጣሪ አቅሞች ናቸው “
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
የሥራና ክህሎት ሚንስቴር በ2016 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ገብተው በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠና የሚወስዱ ተማሪዎች የመግቢያ ነጥብ ይፋ አድርጓል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒሰትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የመቁረጫ ነጥቡን ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳስታወቁት፣ ዜጎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚመጡት መሄጃ ስላጡ ሳይን ያላቸውን እምቅ አቅም አውጥተው መጠቀም እንዲችሉ ነው፡፡
ይህም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለዜጎች ዕድል ፈጣሪ አቅሞች እና ተጨማሪ አማራጭ የሚሰጡ ተቋማት ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡
ከባለፈው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ መሰረት ከዚህ ቀደም እስከ ደረጃ 5 ብቻ ተገድቦ የነበረው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የእድገት መሰላል እስከ ደረጃ 8 ድረስ እዲሆን ተደርጓል፡፡
ይህም ፖሊሲው ደረጃ ስድስትን ከመጀመሪያ ድግሪ፣ ደረጃ ሰባትን ከማስተርስ እንዲሁም ደረጃ ስምንትን ከዶክትሬት ዲግሪ ትይዩ እንዲሆን አድርጓል፡፡
ስለሆነም በዚህ ዓመት የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ መግባት ቢፈልጉ በደረጃ 6 ገብተው መሰልጠን እንደሚያስችላቸው አመላክተዋል፡፡
ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በደረጃ 6 የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች እንደሚስተናገዱ የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር በዚህ ዓመት በተቀመጠው መስፈርት መሰረት በክልሎች አማካኝነት የሰልጣኞች ምደባ ይካሄዳል ብለዋል፡፡
በዚህም በተያዘው የሥልጠና ዘመን 632 ሺህ በላይ ተማሪዎች የሥራ ገበያውን የሰው ሀይል ፍላጎት መሠረት ባደረገ መልኩ ከደረጃ 1-ደረጃ 5 እንደ ውጤታቸው ተመድበው እንደሚሰለጥኑም ነው ክብርት ሚኒስትር የገለጹት፡፡
በወጣው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ደረጃ አንድ እና ሁለት 110,015 ፤ በደረጃ ሦሰት እና አራት 412,557 እንዲሁም በደረጃ አምስት 110,015 እንደሚሳተፉ የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር በረደጃ ስድስት ደግሞ 2000 የሚሆኑ ሰልጣኞችን ለቀመበል ዝግጅት መደረጉን አመላክተዋል፡፡
የ2016 የስልጠና ዘመን የተዘጋጀው መቁረጫ ነጥብ የ2015 ትምህርት እና የ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12 ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ላይ ተግባራዊ ይሆናል፡፡
ከ2014 ዓ.ም በፊት ለነበሩ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ደግሞ በስልጠና ዘመኑ በነበረው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ይስተናገዳሉ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ያዘጋጀው የመግቢያ ነጥብ ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ ቀርቧል፡፡
ህዳር 6/2016 ዓ.ም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴ
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሪክቶሬት በአዲስ መልክ በአገር አቀፍ ደረጃ የኢንተርፕራይዞችን አመታዊ መረጃ መሰብሰቢያ የተዘጋጁ ቅጾች ላይ ለቀበሌ አንድ ማዕከላት አስተባበሪዎችና ባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ፡፡
በዚህም ኢንተርፕራይዞች በአዲስ መልክ ሲመዘገቡ ሊያሟሏቸው ስለሚገቡ ዝርዝር ጉዳዮች እንዲሁም የከሰሙትን መመዝገቢያ ቅጾቹን መሰረት በማድረግ ገለጻ የተደረገ ሲሆን በቀጣይም በአጭር ጊዜ ውስጥ በተጨባጭ ስራ ላይ የሚገኙ እና የከሰሙትን ለመለየት የሚያስችል መረጃዎች የሚሰበሰቡ ይሆናል፡፡
በተያያዘ ኢንተርፕራይዞችን ከመለየትና ከማደራጀት በዘለለ አቅማቸውን በማጎልበት የአንቀሳቃሾች አመለካከታቸውን ሊቀይር የሚችል ስልጠና መስጠት፣ የብድር አቅርቦትና አመላለስ ላይ ትኩረት ማድረግ ፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር በመፍጠርና ድጋፍ ማድረግ የርብርብ ማዕከል እንደሚሆን የዳይሬክቶሬቱ ተወካይ ወ/ሮ መቅደስ ከፈለኝ አሳስበዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ለተመረጡ የወረዳ አንድ ማዕከላት አጠቃላይ ግምቱ ከ400,000 ብር በላይ የሚያወጣ ኮምፒውተሮች እና ፕሪንተሮች ድጋፍ ተደረገ፤
ይህም ድጋፍ በሴቶች ባለቤትነት የሚመሩ ኢንተርፕራይዞችን ለመደገፍ የሚሰራውን ሥራ በማገዝ የሥራ ዕድል የመፍጠር አቅማቸውን ማጎልበት አላማው ባደረገው በWEDP ፕሮጀክት ተገዝተው በዛሬው ዕለት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እና በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ እንዲሁም የፕሮጀክቱ አስተባባሪ በተገኙበት ርክክብ ተደርጓል፡፡
በተያያዘ ፕሮጀክቱ ባለፉት ጊዜያት 2249 የሴት ነጋዴዎች መዝግቦ ለ 1568 መሰረታዊ የንግድ ክህሎት እና ሌሎች ሙያዊ ስልጠና እንዲያገኙ በማድረግ ለ 438 ሴት ተጠቃሚዎች 78,080,000.00 (ሰባ ስምንት ሚሊዮን ሰማንያ ሺህ ብር) ብድር ተሰራጭታል፤ በያዝነው በጀት አመትም በአጠቃላይ 950 ሴት ነጋዴ እና ሴት ኢንተርፕራይዞችን ለመመዝገብ እና በልዩ ልዩ ስልጠና ተጠቃሚ ለማድረግ ከዚህ በተጨማሪም ለሴት ነጋዴዎችን የፋይናነስ ችግር ለመቅረፍ እና በብድር ተደራሽ ለማድረግ 86 ሚሊዮን ብር በፕሮጀክት ተመድቦ እየተሰራ ይገኛል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የአሰልጣኝ ልማት ዳይሬክቶሬት የማሰልጠን ስነ-ዘዴ/ Training Methodology/ ላይ ስልጠና ላልወሰዱ ከለሁለቱ የመንግስት ኮሌጅ አሰልጣኞችና ከግል ኮሌጅ በተለያዩ ሙያዎች ለሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች ለተከታታይ 8 ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ተገኝተው መልክት እንዳስተላለፉት ወቅቱ አዳዲስ ሰልጠኝ ተማሪዎችን የምንቀበልበት ጊዜ አንደመሆኑ አሰልጣኝ መምህራኑ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እንዲችሉ ታሳቢ ያደረገ ስልጠና እንደመሆኑ በተግባር ውጤታማ ስራ ሰርተው ማሳየት እንደሚገባቸው ተናግረዋል፤
ኃላፊዋ አክለውም የስልጠና ጥራት ጋር ተያይዞ በሰልጣኞች የምዘና ውጤት ላይ የሚስተዋለው ክፍተት ለመሙላት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት ተቀራርቦ እየተሰራ ይገኛል ያሉ ሲሆን በዋናነት ግን የአሰልጣኝ መምህሩን አቅም መገንባት የስልጠና ጥራቱን ከማሻሻል አንጻር የሚጫወተው ሚና የላቀ በመሆኑ ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰው በቀጣይ በክትትልና ድጋፍ ተፈጻሚነቱ አንደሚረጋገጥ ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 4/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ለአሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
በመድረኩም ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኞች በሁለትዮሽ ማህበራዊ ምክክር ዝርጋታ እና በአሰሪና ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ላይ ገለጻ ተሰጥቷቸዋል።
በዚህም አዋጁን በመረዳት የአሰሪውንና ሰራተኛውን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 4/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
