es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 064
Suscriptores
Sin datos24 horas
-77 días
+230 días
Archivo de publicaciones
#|ዜና በኮሌጁ ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው የEASTRIP ፕሮጀክት ተቋሙን learning factory እንዲሆንና ለአካባቢው ብሎም ለኢንዱስትሪዎቹ ግብአት መሆን የሚችል ሰልጣኞችን በማብቃት ረገድ ትልቅ ስተዋጽኦ እንዳለው ተገለጸ፡፡ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር መተግበር ላይ ያለው የEASTRIP ፕሮጀክት ከአለም ባንክ፣ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ከIUCA የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት እንዲሁም ከኬንያ እና ከታንዛኒያ የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች የልህቀት ማዕከሉን አጠቃላይ የፕሮጀክት ሂደት ለመመልከትና ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ ያለመ የስራ አፈጻጸም ግምገማ በዛሬው እለት በኮሌጁ በመገኘት አከናወኑ፡፡ ለግምገማው የመጣውን ልኡክ ቡድን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እንዲሁም የኮሌጁን ሁኔታ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ትንሿ ኢትዮጵያ እና ሁሉን አቀፍ ከተማ ወደ ሆነችው ድሬዳዋ ከተማ በደህና መጣችሁ ፡፡ በኮሌጁ እየተተገበረ የሚገኘውየEASTRIP ፕሮጀክት ተቋሙን learning factory እንዲሆንና በኮሌጁ እየሰለጠኑ የሚገኙ ሰልጣኞች ለኢንዱስትሪውን እና ለአካባቢውን ማህበረሰብ ግብአት መሆን የሚችሉ ሰልጣኞችን ማፍራት እንዲችል በርካታ ስራዎችን መስራት ተቸሏል ያሉ ሲሆን አያይዘውም መምህራንን በማብቃት እንዲሁም ለኢንዱስትሪዎች ግብአት መሆን የሚችሉ ስራዎችን በመስራት ለውጦችን ማምጣት እንድንችል አድርጎናል ብለዋል፡፡ በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት በIUCA የምስራቅ አፍሪካ የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት መሪ የሆኑት ዶ/ር ኮሳም እንዳሉት የፍቅር ከተማ ወደሆነችው ድሬዳዋ ከተማ በመምጣቴ በጣም ደስተኛ ነኝ ያሉ ሲሆን አያይዘውም በኮሌጁ እየተሰራ እና እየተጠናቀቀ የሚገኘው ይህ የልህቀት ማእከል ግንባታ ከዚህ በፊት ከነበረው አፈጻጸም በላቀ ሁኔታ ለፍጻሜ ደርሶ በመመልከቴ በጣም ደስታ ተሰምቶኛል ይህ ውጤት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩና የኮሌጁ ማኔጅመንት እንዲሁም የፕሮጀክቱ ሰራተኞች በጋራ በመስራት የመጣ ውጤት ነው ብለለዋል፡፡ ከአለም ባንክ፣ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ከIUCA የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት እንዲሁም ከኬንያ እና ከታንዛኒያ የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች የልህቀት ማዕከሉን እና አጠቃላይ የኮሌጁን እንቅስቃሴ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ከመስክ ጉብኝቱ በኋላ በአቶ መሳይ ጥላሁን በቀረበው አፈጻጸም ላይ ልኡክ ቡድኑ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም እጅግ እንዳስደመማቸው እና ለፕሮጀክቱ መሳካት እየተሰሩ ያሉ ድጋፎችን አድንቀዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ነሀሴ 05/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ ስለ ኮሌጁ ትኩስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት Facebook: facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/diredawapolytechniccollege YouTube: youtube.com/diredawapolytechniccollege

#|ዜና በኮሌጁ ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው የEASTRIP ፕሮጀክት ተቋሙን learning factory እንዲሆንና ለአካባቢው ብሎም ለኢንዱስትሪዎቹ ግብአት መሆን የሚችል ሰልጣኞችን በማብቃት ረገድ ትልቅ ስተዋጽኦ እንዳለው ተገለጸ፡፡ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር መተግበር ላይ ያለው የEASTRIP ፕሮጀክት ከአለም ባንክ፣ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ከIUCA የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት እንዲሁም ከኬንያ እና ከታንዛኒያ የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች የልህቀት ማዕከሉን አጠቃላይ የፕሮጀክት ሂደት ለመመልከትና ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ ያለመ የስራ አፈጻጸም ግምገማ በዛሬው እለት በኮሌጁ በመገኘት አከናወኑ፡፡ ለግምገማው የመጣውን ልኡክ ቡድን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እንዲሁም የኮሌጁን ሁኔታ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ትንሿ ኢትዮጵያ እና ሁሉን አቀፍ ከተማ ወደ ሆነችው ድሬዳዋ ከተማ በደህና መጣችሁ ፡፡ በኮሌጁ እየተተገበረ የሚገኘውየEASTRIP ፕሮጀክት ተቋሙን learning factory እንዲሆንና በኮሌጁ እየሰለጠኑ የሚገኙ ሰልጣኞች ለኢንዱስትሪውን እና ለአካባቢውን ማህበረሰብ ግብአት መሆን የሚችሉ ሰልጣኞችን ማፍራት እንዲችል በርካታ ስራዎችን መስራት ተቸሏል ያሉ ሲሆን አያይዘውም መምህራንን በማብቃት እንዲሁም ለኢንዱስትሪዎች ግብአት መሆን የሚችሉ ስራዎችን በመስራት ለውጦችን ማምጣት እንድንችል አድርጎናል ብለዋል፡፡ በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት በIUCA የምስራቅ አፍሪካ የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት መሪ የሆኑት ዶ/ር ኮሳም እንዳሉት የፍቅር ከተማ ወደሆነችው ድሬዳዋ ከተማ በመምጣቴ በጣም ደስተኛ ነኝ ያሉ ሲሆን አያይዘውም በኮሌጁ እየተሰራ እና እየተጠናቀቀ የሚገኘው ይህ የልህቀት ማእከል ግንባታ ከዚህ በፊት ከነበረው አፈጻጸም በላቀ ሁኔታ ለፍጻሜ ደርሶ በመመልከቴ በጣም ደስታ ተሰምቶኛል ይህ ውጤት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩና የኮሌጁ ማኔጅመንት እንዲሁም የፕሮጀክቱ ሰራተኞች በጋራ በመስራት የመጣ ውጤት ነው ብለለዋል፡፡ ከአለም ባንክ፣ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ከIUCA የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት እንዲሁም ከኬንያ እና ከታንዛኒያ የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች የልህቀት ማዕከሉን እና አጠቃላይ የኮሌጁን እንቅስቃሴ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ከመስክ ጉብኝቱ በኋላ በአቶ መሳይ ጥላሁን በቀረበው አፈጻጸም ላይ ልኡክ ቡድኑ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም እጅግ እንዳስደመማቸው እና ለፕሮጀክቱ መሳካት እየተሰሩ ያሉ ድጋፎችን አድንቀዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ነሀሴ 05/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ ስለ ኮሌጁ ትኩስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት Facebook: facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/diredawapolytechniccollege YouTube: youtube.com/diredawapolytechniccollege

የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ላይ ፈቃድ ያላቸው የሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ዝርዝር

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ሶስተኛ ዙር ትግበራ ሶስተኛ ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ተካሄደ። በዚህም የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ወጣቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና ወስደው በስራ ላይ ልምምድ የገጠሟቸውን ገጠመኞች ላይ በመወያየት እርስ በእርስ አቅም የሚገነባቡበትን መድረክ ተፈጥሮላቸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ነሐሴ 3/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት የ2017 ዓ.ም ማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ አካሄደ:: በትምህርትና ስልጠና አካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የሁለተኛው ተርም
+9
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት የ2017 ዓ.ም ማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ አካሄደ:: በትምህርትና ስልጠና አካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የሁለተኛው ተርም መጠናቀቁን ተከትሎ በአመቱ የተከናወኑ ተግባራትን አፈፃፀም የሚገመግም ማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ ተካሂዷል:: በሂደቱ ሀላፊና የኮሌጁ ም/ል ዲን አቶ ኢልያስ አህመድ የተመራው የማጠቃለያ መድረኩ በሂደቱ ስር ያሉ የክፍል ተጠሪዎች በተገኙበት በአካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት በአመቱ የነበረውን የትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ፣ የትብብር ስልጠናዎች፣ የሰልጣኞች የተቋም ምዘናን ጨምሮ ለትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የተሰጡ ተጨማሪ ተልዕኮዎች አፈፃፀምን በዝርዝር መመልከት ተችሏል:: በተጨማሪም መድረኩ በከሰዓት ውሎው በዲፓርትመንቶች የቀረበውን የ2018 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ማቴሪያል የግዢ ፍላጎት ጥያቄዎች ላይ የአካዳሚክ አባላቱ በጥልቀጥ የተወያዩበት ሲሆን በቀረቡት የግዢ ፍላጎቶች ላይ አስፈላጊውን ማስተካከያ በማድረግ ለግዢና ፋይናንስ እንዲላክም ተደርጎል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ነሃሴ 1/12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

#|በዶ/ር ብሩክ ከድር የተመራ የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አባላትና ከፍተኛ አመራሮች በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘት የመስክ የስራ ጉብኝት አከናወኑ፡፡ ልኡክ ቡድን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም ኮሌጁ እንኳን ወደ ትንሿ ኢትዮጵያ ድሬዳዋ ከተማ በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን አያይዘውም ኮሌጁ ከመንግስት የተሰጠውን ተልእኮ መሰረት በማድረግ እንዲሁም የአካባቢውን ማህበረሰብና የኢንዱስትሪውን ፍለጎት መሰረት በማድረግ የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ውጤቶችን ማስመዝገብ እንደተቻለ ያብራሩ ሲሆን በመቀጠልም ከተቋማዊ ኢንተርፕራይዝ ልማት፣ከዲጂታላይዜሽን እንዲሁም ከፕሮጀክቶች አፈጻጸም ጋር ያለውን ተሞክሮ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩ ሲሆን ለዚህ ሁሉ ውጤት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ፣የኮሌጁ ማህበረሰብ፣ኢንዱስትሪዎችና ሁሉም ባለድርሻ አካለት ጋር በቅርበት በመስራት የተገኘ ውጤት እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ ልኡክ ቡድኑን የመሩት ዶ/ር ብሩክ ከድር በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም በኮሌጁ በኩል እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በተለይ ተቋሙን ተወዳዳሪና ለአካባቢው ማህበረሰብ ብሎም እንደ ሀገር ፋይዳው የጎላ ጥቅም የሚሰጥ ኮሌጅ ለማድረግ እየተሰራ ያለው ስራ በጣም አመርቂና ለሌሎች ኮሌጆችም እንደ አርአያ የሚታይ ነው ያሉ ሲሆን፡፡ አያይዘውም በኮሌጁ በኩል ያየነው የተርንኪ ፕሮጀክቶች በሌሎች አካባቢዎች እንዳሉ የተርንኪ ፕሮጀክቶች ሳይሆን ቀድሞ ወደ ምርት የገባና በአካባቢው ላሉ ኢንዱስትሪዎች ግብአት መሆን እንዲችል ተደርጎ የተሰራው ስራ እንደ ተሞክሮ ሊታይ የሚገባ ነው እንዲሁም በኮሌጁ በኩል እየተተገበረ ያለው የEASTRIP ፕሮጀክት ህንጻ ግንባታ ሂደት በጣም አስደማሚና በታሰበው ልክ እንዲሔድ የተደረገበት አሰራር የከተማ አስተዳደሩ እና የኮሌጁ ኃላፊዎች የወሰዳችሁት ቁርጠኝነት ያለው የአስተዳደር ውሳኔ ለዚህ ውጤት ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዲሁም የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ደ/ር ብሩክ ከድር እንዲሁም የኢንስቲትውቱ ኃላፊዎች በተገኙበት ከሶስቀን በፊት መከናወኑ የሚታወስ ነው፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ ስለ ኮሌጁ ትኩስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት Facebook: facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/diredawapolytechniccollege YouTube: youtube.com/diredawapolytechniccollege

ህጋዊ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት፤ ለሁለንተናዊ ተጠቃሚነት አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም፡- ዜጎቻችን በህገ-ወጥና ደህንነቱ ባልተጠበቀ መንገድ ወደ ተለያ ሀገራት ለሥራ ለመሰማራት ሲሞክሩ ለተለያዩ ችግሮች እየተጋለጡ ነው፡፡ ህገ ወጥ ስደት በዜጎቻችን ላይ ከሚያደርሰው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ባሻገር የበርካታ ዜጎቻችንን ውድ ሕይወትም እየቀጠፈ ይገኛል፡፡ ሰሞኑን በጀልባ መስጠም ምክንያት በየመን በዜጎቻችን ላይ የደረሰው ልብ ሰባሪ የሞት አደጋ የዚህ የህገወጥ ስደት አስከፊ ገጽታ ሁነኛ ማሳያ ነው፡፡ መንግስት መሰል ችግሮችን ለመቆጣጠር በሀገር ውስጥ ከሚፈጥረው ሰፊ የሥራ ዕድል በተጨማሪ ወደ ውጭ ሀገራት ሄደው መስራት ለሚፈልጉ ዜጎች ህጋዊና ደህንነቱ የተጠበቀ ስርዓት ለመዘርጋት በልዩ ትኩረት ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ስርዓቱ የዜጎችን ክብር እና ደህንነት ብቻ ሳይሆን ፍትሃዊና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ የተቀረፀ ነው፡፡ ከ2014 በጀት ዓመት ጀምሮ ሂደቱ ከሰው እጅ ንክኪ እንዲፀዳና በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በማድረግ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ብቻ ተግባረዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡ በዚህም በ2014 በጀት ዓመት 69 ሺህ 718፤ በ2015 በጀት ዓመት 102 ሺህ 076፣ በ2016 በጀት ዓመት 345 ሺህ 167 እንዲሁም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 503 ሺህ 173 ዜጎች መንግስት በዘረጋው ህጋዊ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ስርዓት ተጠቃሚ መሆን ችለዋል፡፡ መንግስት ዘርፉን ለማዘመንና የዜጎችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እያደረገ ባለው ጥረት ለውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ ዜጎችን በልዩ ሁኔታ ለማዘጋጀት የሚያስችል ስርዓተ ስልጠና ቀርጾ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡ የስልጠና ተደራሽነቱንና ፍትሃዊነቱንም ለማረጋገጥ ከመንግስት ተቋማት ባሻገር የግል ማሰልጠኛ ተቋማት በሥራው ውስጥ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡ የመዳረሻ ሀገራትን ለማስፋት በተደረገው ጥረትም ከሳዑዲ አረቢያ፣ ከተባበሩት አረብ ኤሚሬት፣ ከዮርዳኖስ፣ ከሊባኖስ፣ ከኳታር እና ከኪዌት መንግስት ጋር የሁለትዮሽ የሥራ ስምሪት ስምምነት በመፈራረም ወደ ሥራ እንዲገባ ተደርጓል፡፡ ይህም ዜጎቻችን በእነዚህ ሀገራት መብትና ደህንታቸው እንዲሁም ተጠቃሚነታቸው ተጠብቆ እንዲሠሩ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ በቀጣይም ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አስፈፃሚ አካላት ጋር በመሆን የመዳረሻ ሀገራትን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማላቅ በልየ ትኩረት የሚሰራውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ በአንፃሩ ሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎች በአሳሳች መረጃ እና በአማላይ ማስታወቂያ አሁንም ዜጎቻችንን ለከፋ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውስ መዳረጉን ቀጥለዋል፡፡ ስለሆነም ዜጎች ህጋዊ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪትን ብቻ ምርጫቸውን በማድረግ ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ካላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዲታደጉ ጥሪ እያቀረብን በየአካባቢው የሚያስተዋሉትን የህገወጥ አዘዋዋሪዎች እንቅስቃሴ በአቅራቢያቸው ለሚገኙ የሕግ አስከባሪ አካላት እንዲያሳውቁ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

የሥራ ማስታወቂያ ለሥራ ፈላጊዎች!!!
+5
የሥራ ማስታወቂያ ለሥራ ፈላጊዎች!!!