cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

እዚህ Channel ላይ ኦርቶዶክሳዊ ስብከት ፣መዝሙር ፣ኬነጥበቦች እና መፅሕፍት ይለቀቁበታል "ጌታ ሆይ እናትህን ማን ብለን እንጥራት? እናት ብቻ እንዳንላት ድንግል ሆና አገኘናት ፣ ድንግል እንዳንላት ልጅ ታቅፋ አየናት። ጌታ ሆይ እናትህን ለመጥራት እንዲህ የሚያስቸግር ከሆነ አንተን ከቶ ምን ብለን እንጠራሃለን??" ቅዱስ ኤፍሬም

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
2 148
Suscriptores
-2024 horas
+1857 días
+1 00530 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

[ ስንክሳር ሐምሌ - ፲ - ] .mp34.75 MB
🕊 [ †  እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን።  † ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † 🕊   †  ቅዱስ ናትናኤል  †   🕊 † በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ከቅዱሳን ሐዋርያት መካከል ዘግይቶ ሰማዕትነትን የተቀበለ ይህ ቅዱስ ሐዋርያ ነው:: ቅዱሱ ሐዋርያ የተወለደው ከእሥራኤላውያን ወላጆቹ ጌታችን በተወለደበት ዘመን አካባቢ ነው:: ይህ በምን ይታወቃል ቢሉ እርሱ ሕፃን እያለ ሔሮድስ 144,000 ሕፃናትን ሲፈጅ እርሱ ግን በእግዚአብሔር ጥበብ ተርፏል:: እናቱ በቅርጫት ውስጥ አድርጋ የበለስ ዛፍ ላይ አስቀምጣው ተደብቃ ታጠባው ነበር:: ለሐዋርያው ወላጆቹ ያወጡለት ስም ስምዖን ሲሆን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ናትናኤል ብሎታል:: በባልንጀሮቹ ሐዋርያት ደግሞ የቃናው ስምዖን [ገሊላ ቃና አካባቢ ስላደገ] አንዳንዴም ቀናተኛው ስምዖን ይሉት ነበር:: ምሑረ ኦሪት ነበርና ዘወትር ለሕግ ይቀና ነበር:: በገሊላ ቃና ሰርግ የደገሰው ዶኪማስ የቅዱስ ናትናኤል የአጎት ልጅ ነው:: ጌታና ደቀ መዛሙርቱን ዶኪማስ የጠራበት አንዱ ምክንያትም ይሔው ነው:: ቅዱስ ናትናኤል ኦሪትን ከገማልያል ተምሮ: ከበለስ ቁጭ ብሎ ይተክዝ ነበር:: "መሲሕ ምነው ቀረህ?" እያለም ይተክዝ ነበር:: ማዕምረ ኅቡዓት አምላካችን ክርስቶስ ይህንን አውቆ በፊልጶስ አማካኝነት ጠርቶታል:: ናትናኤል ለጊዜው ተከራክሮ ነበር:: በኋላ ግን የጌታችንን ማንነት በደቂቃዎች ተረድቶ አምኗል:: ጌታችንም "ክዳት ሽንገላ በልቡ ውስጥ የሌለበት ንጹሕ እሥራኤላዊ" ሲል አመስግኖታል:: ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ከጌታችን እግር ሥር ምሥጢረ መንግስተ ሰማያትን ተምሮ: በጸጋ መንፈስ ቅዱስም ሰክሮ: ብዙ አሕዛብን ከጨለማ [ጣኦት አምልኮ] ወደ ብርሃን [አሚነ ክርስቶስ] መልሷል:: እጅግ ብዙ መከራንም ተቀብሏል:: የጌታችን ወንድም የተባለ ቅዱስ ያዕቆብ በአይሁድ ከተገደለ በኋላም ቅዱስ ናትናኤል የኢየሩሳሌም ሁለተኛ ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ አገልግሏል:: ከአይሁድም ዘንድ ብዙ መከራ ደርሶበታል:: በመጨረሻም በዚህች ዕለት በሰማዕትነት አልፏል:: በገድለ ሐዋርያት ላይ እንደተጠቀሰው ቅዱሱ ሰማዕት የሆነው በመቶ ሃምሳ ዓመቱ ነው:: ያ ማለት ደግሞ ከሐዋርያት አባቶች በመጨረሻ ያረፈው እርሱ ነው ያሰኛል:: 🕊   †   አባ ብስንዳ   †     🕊 † ዳግመኛ በዚህ ቀን ታላቁ አባ ብስንዳ ይታሠባል:: አባ ብስንዳ በዘመነ ጻድቃን ምድረ ግብጽ ውስጥ ከነበሩ ታላላቅ አበው አንዱ ነው:: ቅዱሱን ከገድሉ ጽናት የተነሳ መላእክት በእጅጉ ይወዱት ነበር:: "እኔ ልሸከምህ - እኔ ልሸከምህ" እያሉ ይሻሙበት: በተራ በተራም ተሸክመውት ይውሉ ነበር:: እርሱም ለበርካታ ዓመታት ውኃ የሞላበት ጉድጓድ ውስጥ ገብቶ ይጸልይ ነበር:: እንደ እሳት በሚባላው በረዶ ውስጥ ገብቶ መጸለዩ የፈጣሪውን ሕማማት ለመሳተፍ እና ለኃጥአን ምሕረትን ይለምን ዘንድ ነው:: ሁሌም በዘጠኝ ሰዓት መላእክት ተሠብስበው ይመጡና በብርሃን ሠረገላ ይሸከሙታል:: ከመሬትም ዘጠኝ ክንድ ከፍ ያደርጉት ነበር:: ከብዙ ዓመታት ተጋድሎ በኋላም በዚህች ቀን ዐርፎ ወደ ፈጣሪው ሒዷል:: † እግዚአብሔር በቅዱስ ናትናኤል ምልጃ ሃገራችንን ከጥፋት: ሕዝቦቿንም ከመቅሰፍት ይሰውርልን:: ከሐዋርያው እና ከጻድቁ አባ ብስንዳ በረከትም አይለየን:: 🕊 [  †  ሐምሌ ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] ፩. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ [ቀናተኛው ስምዖን] ፪. ታላቁ አባ ብስንዳ ጻድቅ ፫. አባ ከላድያኖስ ሊቀ ጳጳሳት [   †  ወርኀዊ በዓላት   ] ፩. ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ፪. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ ፫. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ ፬. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ እልፍዮስ] ፭. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት ፮. ቅዱስ ዕፀ መስቀል † " ጌታ ኢየሱስ ናትናኤልን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ 'ተንኰል የሌለበት በእውነት የእሥራኤል ሰው እነሆ' አለ:: ናትናኤልም 'ከወዴት ታውቀኛለህ?' አለው:: ጌታ ኢየሱስም መልሶ 'ፊልጶስ ሳይጠራህ ከበለስ በታች ሳለህ አየሁህ' አለው:: ናትናኤልም መልሶ 'መምሕር ሆይ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ:: አንተ የእሥራኤል ንጉሥ ነህ' አለው::" † [ዮሐ. ፩፥፵፰-፶፩] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
Mostrar todo...
01:41
Video unavailableShow in Telegram
                       †                         - የካህን ሀገሩ የት ነው  ? !       የካህን ርስቱ ምንድን ነው ? !    የካህን ወገኑ ማን ነው  ? !       🕊                        💖                     🕊
Mostrar todo...
6.51 MB
Photo unavailableShow in Telegram
💛 ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 🕊     ም ክ ረ     ቅ ዱ ሳ ን     🕊 ▷  ❝ ሸ ክ ማ ች ሁ   የ ከ በ ደ ! ❞ [ 💖 [ " ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ " ] 💖 ]  [                        🕊                        ] --------------------------------------------------- " እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ፥ ወደ እኔ ኑ ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።" [ ማቴ . ፲፩ ፥ ፰ ] 🕊                       💖                   🕊
Mostrar todo...
[ + ሸክማችሁ የከበደ + ] .mp36.51 MB
                         †                           [      🕊  ፍኖተ ቅዱሳን   🕊      ] [ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ] ▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬ [  ተርእዮን [ መታየትን ] አለመውደድና ለታይታ ብሎ ምንም ነገር አለማድረግ !  ] 🕊 "  በእንዲህ ያለ ያረጀ ልብስ .... !  " ........ አባ ዮሴፍ እንዲህ አለ ፦ " በደብረ ሲና ሳለሁ አርአያው ደስ የሚል በመልካም ተጋድሎ የሚኖር አንድ ወንድም ነበር። ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመጣ ያለቀና እሳት የበላው የማቅ ዕራፊ እንደለበሰ ነበር። ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ሲገባ አየሁትና አንድ ቀን ፦ ' ወንድሜ ሆይ ፣ ወንድሞች በጸሎት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ሲቆሙ በአምሳለ መላእክት ሆነው አታያቸውምን ? አንተ እንዴት በእንዲህ ያለ ያረጀ ልብስ በመካከላቸው ትሆናለህ ? እባክህ ልብስህን ለውጥ ' አልኩት። እርሱም ፦ " አባ ፣ ይቅርታ አድርግልኝ ፣ ሌላ ልብስ ስለሌለኝ ነው። " አለኝ። ያን ጊዜም ወደ ማደሪያዬ ወሰድኩትና ልብስና ሌላም የሚያስፈልገውን ሁሉ ሰጠሁት። ከዚያ በኋላ ሌሎቹ መነኰሳት እንደ ለበሱት ለበሰ። ከዚህ ጊዜ በኋላ ከአኃው መካከል ለገዳሙ ጉዳይ ወደ ንጉሡ የሚላኩ አባቶችን በፈለጉ ጊዜ አብሯቸው ይሄድ ዘንድ ይህን ወንድም መረጡት። እርሱ ግን ይህን ነገር ባወቀ ጊዜ አባቶችን ፦ " ስለ እግዚአብሔር ስትሉ እባካችሁ ይቅርታ አድርጉልኝ ፣ እና ከዚያ አገር ታላላቆች ሰዎች መካከል የአንዱ ባሪያ ነበርኩ ፣ ምናልባት ሲያየኝ እንዳያውቀኝና እንዳይጣላኝ ፣ ወደ ባርነትም እንዳንመልሰኝ እፈራለሁና ተዉኝ " ብሎ ለመናቸው። አበውም እንዲህ ባላቸው ጊዜ ተውት። ከዚያ በኋላ ቀድሞ የሚያውቀው ሰው ወደ ገዳሙ መጣ ፤ እንዲህም አላቸው ፦ " ይህ ሰው ከንጉሥ መኳንንት አንዱ ነበር ፤ ክብሩም ታላቅ ነበር ፤ ነገር ግን የነበረውን ሁሉ ትቶ ወደዚህ ቦታ መጣ። ባሪያ ነበርኩ ያለውም እንዳያውቁትና ነገሩ በቁስጥንጥንያና በአገሩ እንዳይታወቅበት ነው። " የአባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡ †                       †                         † 💖                    🕊                     💖
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.