cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

[[UMMA LIFE የእውቀት ማዕድ (ከሀዲስና ቁርዐን)

=>መስጂድ ላይ የሚሰጡ ዳዕዋ እና ደርስ መስጫ >>channel 🗞ይህን የማካፈል ስራ ስንሰራ ላቅ ያለ ደስታ ይሰማናል https://t.me/yewqt_mad🗞>> 🗞@ABU_USMAN2 ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ። ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ! طلب العلم (من الحديث والقرآن)

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
412
Suscriptores
-224 horas
-67 días
-930 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

Photo unavailableShow in Telegram
ለመረጃ ያክል እንዲሆናችሁ… ይህ ትናንት የተመረቀው የዓይነ ስውራን ማዕከል ስሙ በሚዲያዎች አለመዘገቡ ብቻ አይደለም ችግሩ። ከአመታት በፊት ልክ እንደዚሁ አንድ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬትስ (UAE) ዜጋ የሆነ ሙስሊም ባለሃብት በራሱ ፋውንዴሽን ስም «አል-መኽቱም» የተሰኘ ት/ቤት እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ አስገንብቶ አስመርቆ ነበር። ጀሞና ጋርመንት አካባቢ! ግን ያኔ ስሙን ቢለጥፉትም ከ2 አመት በኋላ ስሙን ቀይረው «ቡርቃ ዋዩ» ብለው ቀይረውታል። ሙስሊሙ ባለሃብት ምናልባትም ይህ ት/ቤት በጎድን መድረሳ፣ በጎድን አካዳሚ እንዲሰጥበት ቢያቅድም፤ ግን ሙስሊም ተማሪዎች ሒጃብ እንዳይለብሱ ጫና የሚደረግበትና ሶላት የሚከለከልበት ጭምር ሆኗል አሉ። ታዲያ ከዚህ ተጨባጭ አንፃር ሰዎቹ ነውር ብርቃቸው አይደለምና ዛሬም በዛው በUAE መሪ ባለቤት ስም የተገነባው የዓይነ ስውራን ማዕከል ገና ከወዲሁ ስሙ ያልተዘገበው ከትንሽ ቆይታ በኋላ ሊቀይሩት ታስቦ ይሆን? የሚል ጥያቄ ያስነሳል። ይህ ብቻ ሳይሆን በእንዲህ አይነት የአካል ጉዳተኞች ማዕከል ውስጥ የአክፍሮት ኃይላት የግላቸውን ሚሽን ያስፈፅማሉ። ወደ ኋላ የአንድ ወንድም ታሪክ ትዝ አለኝ። አንድ ዓይነ ስውር ወንድማችን ነበር አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ የማውቀው። በፊት የተማረው ሻሸመኔ ነበር። ሻሸመኔ ላይ የዓይነ ስውራን ማዕከል አለ። ሌላ አማራጭ የሌላቸው ሙስሊም ዓይነ ስውራንም እዛ ሲገቡ፤ ገና በለጋነታቸው ጀምሮ መዝሙር እንዲዘምሩና ስብከታቸውን እንዲታደሙ ይደረጋሉ። አንዳንዱን መዝሙር ያኔ ራሱ አልረሳውም። በድጋፍ ስም ብዙ ተልዕኮ ያላቸው አሉ። ይህ አላማቸው በኛው ሰዎች በተሰጠ ገንዘብ ከተፈጸመ ደግሞ ችግሩ የኛው ነው። ዐረቦቹ መስጠታቸውን እንጂ በዚህ መልኩ ይጠቀሙታል ብለው አያስቡም። እነዚህኞቹም እኛ ይናገራሉ ብለው አያስቡም። ይታሰብበት!
Mostrar todo...
💯 1
~በሕይወት እስካላችሁ ድረስ፣ልባችሁ እስከመታች ድረስ፣እስትንፋሳችሁ እስካልተቋረጠች ድረስ… ራሣችሁን አትመኑ።ፈተና እንደማይደርስባችሁ እንዴት አወቃችሁ!? ሃጢኣት በሚሠራ ሰው አትሳቁ፣የሰዉን ነውር አትከታተሉ፣የሰዉን ዉርደት አታነፍንፉ፣በራሣችሁ አትመፃደቁ፣ነገ ምን እንደምትሆኑ ላታውቁ እኔ እኮ እንዲህ እንዲህ ነኝ አትበሉ፣ራሳችሁ ላይ አተኩሩ ነፍሲ ነፍሲ በሉ። ትኩረታችሁ ስለ ኻቲማችሁ ይሁን እንደተሠተራችሁ ትኖሩ ዘንድ አምላኬ ሆይ ሰትረኝ በሉ፡፡ @yewqt_mad
Mostrar todo...
👍 1
በታሪክ እጅግ በጣም ከባዱ የሐዘን አጋጣሚ፤ እናታችን ዓኢሻህ መጋረጃውን ከፍታ ለሶሐቦች «የአላህ መልዕክተኛ ሞቱ!» ያለችበት አጋጣሚ ነው። أشد لحظات التاريخ حزناً: عندما فتحت عائشة الستار وقالت للصحابة: "مات رسول الله" ፊዳከ አቢ ወ ኡሚ ያ ረሱሉ-ል'ሏህ! اللهم صلي وسلم وزد وبارك على نبينا وحبيبنا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً إلى يوم الدين @yewqt_mad
Mostrar todo...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
አላህ ይዘንለት የነብያት ተልእኮ የሆነውን ጥሪ ለማድረስ የደከመው ድካሙን አላህ ቆጥሮለት ከነብያት፣ከሳሊሆች ጋር ከሚቀሰቀሱት ያድርገው ኢና ሊላሂ ወኢና ኢላይሂ ራጂዑን በተለያዩ ከተሞች በመዘዋወር የጎዳና ላይ ዳዕዋ ያደርግ የነበረው ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ ወደ አኼራ ሄደ! ... (ሀሩን ሚዲያ፦ግንቦት 06/2016) ... በተለያዩ ከተሞች እየተዘዋወረ በተለይ በአሳሳ፣ሮቤ፣አዳማ ፣ አርሲ ፣ባሌ፣ሻሸመኔ ፣ሀረር፣ድሬዳዋ፣አዲስአበባን በመሳሰሉ ከተሞች በወዘዋወር የጎዳና ላይ ዳዕዋ ያደርግ የነበረው ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ በዛሬው ዕለት በሻሸመኔ ከተማ በድንገት ወደአኼራ መሻገሩ ተሰምቷል። .. ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ ምንም የማይፈራ ሙጃሂድ ከልጅነት እስከ ወጣትነትና ጎልማሳነት ምናልባት እስካዛሬዋ እስከመጨረሻዋ የዱንያ ላይ ቀኑ ድረስ ሐያቱን በሙሉ በደዕዋ አሳልፏል፡፡ኢስላምን ለማድረስ ብዙ የለፋ የጎዳና ላይ ዳዕዋ የሚያደርግበት ስፒከሩ በተዳጋጋሚ ታስሮበት በተለያዩ የሀገሪቷ ከተሞች በሚገኙ የፖሊስ ጣቢያቢያዎች በመንከራተት ብዙ መስዋዕትነት ይከፍል እንደነበረ "ኑ ወደ አላህ"እያለ በሚያደርገው ጥሪ ብዙ ድብደባ እና እስርና እንግልት ይፈፀምበት እንደነበርም ወዳጆቹ ገልፀዋል። ... ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ እሁድ ዕለት ግንቦት 4/2016 ዓ.ል በሻሸመኔ ከተማ የተካሄደውን የቁርአን ውድድር ታድሞ የነበረ ሲሆን ዛሬ ሻሻመኔ ላይ ድንገት ወደአኼራ መሄዱ ተሰምቷል። ... ¤ሀሩን ሚዲያ አላህ ለእርሱ ጀነትን ለወዳጅዘመዶቹ ሰብርን እንድወፍቃቸው ይመኛል! ... ©ሀሩን ሚዲያ -@yewqt_mad
Mostrar todo...
~ራስህን ለማስተካከል ከራስህ ጋር የምትታገል ከሆነ አንተ መልካም ሰው ነህ። ምክንያቱም በተበላሸ ቀልብ ለፅናት መታገል ከቶውኑ አይታሰብና። ኢላሂ! በዲንህ ላይ መፅናት የሚሻን ቀልብ ሁሉ አግዝ!» t.me/+CL_1nL1UHLFhZjU8
Mostrar todo...
👍 4
~ወዳጆቼ! በምድር ላይ ኑሮ ማግኘት ይሁን ማጣት የትርፍ አልያም የኪሣራ ምልክት አይደለም። ትልቁ ማግኘት አላህን ማግኘት ሲሆን ትልቁ ማጣትም አላህን ማጣት ነው። ከሰው ልጆች ሁሉ አላህ ዘንድ ትልቅ ክብር ያለው በአላህ አምኖ እሱን የፈራ ሙእሚን ነው።  ከአላህ ጋር መነገድ ከፈለግን እሱ ዘንድ ትልቅ ዋጋ የሚያወጣልን ነገር ኢማን ነው። ምድር ላይ ስንኖር በርካታ  ድሎችን ልንቀዳጅ እንችላለን፣ ትልቅ ድል አስመዝግበናል ብለን በልበሙሉነት መናገር የምንችለው  ነፍስያችንን አሸንፈንና ተቆጣጥረን በእጃችን ያስገባናት እንደሆነ ነው። ያ ረብ! እየወደቅንም እየተነሳንም ወዳንተ መጓዝ፤ ካንተ መድረስ ነውና ህልማችን አንተ እገዘን! = t.me/+CL_1nL1UHLFhZjU8
Mostrar todo...
👍 2
መትን ኡሱሉ ሰላሳህ እየተነበበ በማራኪ ድምፅ https://t.me/nhwdr
Mostrar todo...
👍 1
ተመልከት ይህንን ነጥብ‼ ================== ✍ ውዱ ነቢይ ﷺ እንዲህ ይላሉ፦ "አላህ ለሙሳ እንዲህ የሚል ወሕይ አወረደለት፦ «…يَا مُوسَى قُلْ لِلْمُذْنِبِينَ النَّادِمِينَ : أَبْشِرُوا ، وَقُلْ لِلْعَامِلِينَ الْمُعْجَبِينَ : اخْسَرُوا) «ሙሳ ሆይ! ለነዛ ወንጀል ሠርተው ለተፀፀቱ "አብሽር" በላቸው። መልካም ሥራ ሠርተው ግን በነፍሳቸው ለተገረሙ (በራሳቸው ለተደነቁ) "ክሰሩ" በላቸው።»" [" الحلية " (5/45 و7/127) ] ♠ ዾዒፍ ነው የሚሉ ቢኖሩም መልዕክቱን ግን አስተውለው! ወንጀል'ኮ አልሠሩም፣ እንዳውም መልካም የሚባል ሥራ ሠርተዋል። ግን ጉራና ኩፈሳ ስላለበትና ኢኽላስ ስለሌለው ክሠሩ ተባሉ። ለዛምኮ ነው ኢብኑ-ል-ቀይ'ዩም «ኢኽላስ ከሌለህ አትድከም!» የሚለው። እነዚህኞቹ ደግሞ መልካም ሥራ አልሠሩም'ኮ፣ እንዳውም ወንጀል ሠርተዋል። ግን ከልባቸው ተፀፀቱና ወደ አላህ ተመለሱ። ከዚያስ ምን ተባሉ? "አብሽሩ!" አላሁ አክበር‼ «የውስጤን እሳት ለማጥፋት ፥ ወደ ዓይንህ ባ'ላይም፣ ነፍሴም ልቤም ወዳንተ ፥ ማማተሩን አይተውም።» አላህ "አብሽር!፣ ምንም ማዘንና መተከዝ የለባችሁም!" ከሚባሉት ባሮቹ ያድርገን፣ ኢኽላስንም ይወፍቀን። || t.me/MuradTadesse
Mostrar todo...
Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹

ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦ 1) ከቁርኣን፣ 2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ] 3) ከታማኝ ዑለማዎችና 4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል። √ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ። √ አላማዬ በዲኔ ላይ ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው። ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @Murad_Tadesse ላይ አስፍሩት። ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ። ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ!

👍 2
መስጂዳችን በዚህ ሁኔታ ላይ ይገኛል ። አሁን አሻራችሁን አሳርፉ! @yewqt_mad
Mostrar todo...
↩ وعَلَيكَ بقِلَّةِ الكَلامِ يَلِينُ قَلبُكَ ، وعَلَيكَ بطُولِ الصَّمتِ تَملِكُ الوَرَعَ ، 👅 ንግግር በማሳጠር ላይ አደራህ, ቀልብህን ይለሰልሳል፣ ዝምታን አብዛ, ጥቡቅነትን ትወርሳለህ(ትላበሳለህ)‼️ @yewqt_mad
Mostrar todo...
👍 2