es
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

Ir al canal en Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

Mostrar más
3 316
Suscriptores
+724 horas
+267 días
+11030 días
Archivo de publicaciones
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የልማት እና ማሀበራዊ አገልግሎት ኮሚሽን(ልማአኮ) ከአጋሩ የኪንደርኖትሂልፍ(KNH) መንግስታዊ ያልሆነ የልማት ተቋም ጋር በጋራ በመሆን በተለያዩ የኢትዮጲያ አከባቢዎች የተሰሩ የልማት ስራዎችን የሚዘክር 50ኛ አመታት በዓል በማክበር ላይ ይገኛል። አጋር ተቋሙ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በልጆች እና ወጣቶች ላይ የሚሰራ ሲሆን ባለፉት 50 አመታት(1966 - 2016) ከቤተክርስቲያኒቱ ልማአ ኮምሽን ጋር በጋራ በመሆን ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ልጆችና ወጣቶች ሙሉ አቅማቸው ተጠቅመው ውጤታማና ምርታማ ዜጎች መሆን ይችሉ ዘንድ ዘፈብዙ ፕሮጀክቶችን በመንደፍ የትምህርት እድሎችን እና የሙያ ስልጠናዎችን ሲሰጥት ቆይቷል። በዓሉም በጉዲና ቱምሳ ሁለንተናዊ የስልጠና ማዕከል በተለያዩ ዝግጅቶች እና በኤግዚቢሽን በዛሬው እለት በመከበር ላይ ይገኛል። በመክፈቻ መርሀግብሩም ላይ የቤተክርስቲያኒቱና የልማት ተቋማቱ አመራሮችን ጨምሮ የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። - - - - - Komiishiniin Misoomaa fi Hawwaasummaa Waldaa Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus (KMHWKWWMY) Dhaabbata deggersa Misoomaa bu'aaf hin hojjennee fi hidhata hojii isaatii ta'e Kindarnootihiilfi (KNH) jedhamu waliin ta'uudhaan hojii Misoomaa biyyattii keessaa bakka garaa garaatti hojjetaman kan leellisu ayyaana waggaa 50ffaa ayyanessaa jira. Dhaabbatni deggersaa kun kan inni irratti xiyyeeffatee hojjetu ijoollotaa fi dargaggoota irratti yammuu ta'u; waggoottan 50 (bara 1966- 2016) keessatti Komiishinii Misoomaa fi Hawwaassummaa Waldattii waliin ta'uudhaan ijoollotaa fi dargaggoota balaaf saaxilamanii fi hawaasa keessatti qoodamuun (moggaatti dhiibamuun) irra ga'e jabaatanii hojjechuudhaanlammii bu'a qabootaa fi ija godhatan akka ta'aniif projectoota garaa garaa qopheessee leenjii oogummaa kennuu fi carraa barumsa kennaafii tureera. Ayyaanni kun Giddu Gala Leenjii Walii Galaa Guddinaa Tumsaatti qopheewwan garaa garaa fi Egzibiishiniidhaan ayyaaneffamuu guyyaa har'aa jalqabeera. Sirna baniinsa Ayyana kanaa irrattis geggeessitootni dhaabbata Misoomaa Waldattii fi keessumootni waamichi godhameef argamaniiru. - - - - - EECMY-DASSC together with its partner Kinder Not Hilfe (KNH) is celebrating 50 years anniversary of the development works done in various parts of Ethiopia. The partner organization focuses on children and youth, and in the past 50 years (1973-2023) together with DASSC, has been providing educational opportunity and vocational trainings, devising various projects in order for the venerable and marginalized children and youth’s, use their full potentials to become productive citizens. With different events and exhibition the celebration is holding today, at GTWTC. The opening program was also attended by invited guests, partner organization and church leaders.

ከሁሉ አስቀድማ ቤተ ክርስቲያን በገጠማች ችግር ለቤተ ክርስቲያን ድምፅ በመሆን እና በጸሎት ከጎንዋ የቆሙትን ሁሉ ታመሰግናለች። ሆኖም ከቀናት በፊት የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የድሬዳዋ ማህበረ ምዕመናን ይዞታን አስመልክቶ ከቤተ ክርስቲያን በተሰጠው መግለጫ ላይ ጉዳዩ የማይመለከተው አካል ተብሎ የተጠቀሰው በአንዳንድ ወገኖች ዘንድ ቅሬታን ፈጥሯል። እናም በጉዳዩ ሂደት ዙሪያ መግለጫ የመስጠት ሀላፊነት ያላቸው የራስዋ የቤተክርስቲያኒቱ አመራሮች፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት፤ ካልሆነም የድሬዳዋ ማህበረ ምዕመን እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል እንደሆኑ ለመግለጽ እንጂ የድሬዳዋ ወንጌላውያንን አስተዋፆ ከማሳነስ አንፃር እንዳልሆነ ቤተ ክርስቲያን ማስገንዘብ ትፈልጋለች። የኢት/ወ/ቤ/ክ መካነ ኢየሱስ * * * * Waldaan Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus waan hundumaa dursitee rakkoo ishee mudate keessatti qaamotaa ishee cina dhaabbachuudhaan sagalee ta'aniif in galateeffatti. Kanumaan wal qabsiisee guyyoota muraasa dura Waldaan Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus waa'ee galma Waaqeffannaa fi qabiyyee Waldaa Amantootaa Dirree Daawwaa ilaalchisee iba isheen kennite irratti "qaama dhimmi isaa hin ilaaltne" jedhamee inni ibsame sun qaamota tokko tokko birati mufannaa uumeera. Nutis dhimma kana irratti ibsa kennuudhaaf geggeessitootniWaldattii itti gaafatama qabnu dhimmi kun kan ilaallatu; qaamota mootummaa, Waldaa Amantoota Dirre Daawwaa fi Tokkummaa Waldoota Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa ta'uu isaa ibsuuf irraan kan hafe ga'ee Tokkummaan Waldoota Kiristiyaanaa Dirree Daawwaaba'e hir'isuuf akka hin taane Waldattiin cimsitee hubachiisuu barbaaddi. W/K/W/W/M/Yesuus Itiyoophiyaa

የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መሪዎች የህብረት: የስልጠና: እና የምክክር ጊዜ - ( ቀን 1) Yeroo Tokkummaa, Leenjii fi Marii Gaggeessitoota Tajaajajila Ijoollee fi Dargaggoo (Guyyaa 1ffaa) === === የኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢየሱስ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ አዳዲስ ለተመሰረቱ ሲኖዶሶች እና በነባር ሲኖዶሶች አዳዲስ ለተመረጡ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መሪዎች ስልጠና በጉዲና ቱምሳ ሁለንተናዊ የስልጠና ማዕከል እየሰጠ ይገኛል:: ስልጠናው በመምሪያው ተቀርጾ እየተሰራበት ባለው ሁለንተናዊ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ እና የፖኬጁ የዕቅድ: የአፈፃፀም ክትትል እና ሪፖርት ቼክሊስት ዙርያ ትኩረት በማድረግ ተጀምሯል:: በአጠቃላይ ከሁለንተናዊ ፓኬጁ በተጨማሪ ከፓኬጁ በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ተጨማሪ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል: ነገም የሚቀጥል ይሆናል። የሥራው ባለቤት እግዚአብሔር ይመስገን! ''...ሥራው ታላቅና ሰፊ ነው...።'' ነህምያ 4:19 ''...የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን...'' ነህምያ 2:20 === === === YEROO LEENJII TAJAAJILTOOTA IJOOLLEE FI DARGAGGOO SINOODOOSOTA WWWMYI WKWWMakaana Yesuus Itoophiyaa, Qajeelchi Tajaajila Ijoollee fi Dargaggoo tajaajiltootaa fi gaggeessitoota tajaajilichaa sinoodoosota haaraa irraa dhufanii fi sinoodoosota buleeyyiitti warra haaraa filamaniif leenjii Paakeejii Hundagaleessa Ijoollee fi Dargaaggootaa, Cheekliistii Karooraa, Hordoffii Raawwii fi Gabaasaa irratti xiyyeefate kennuudhaan jalqabameera. Paakeejii hunda-galeessa dabalatee, mata duree paakeejicha keessaa filataman irrattis leenjiin dabalataan tajaajiltootaan kennamuu jalqabeera, guyyaa borus kan itti fufu ta'a. Abbaan Hojichaa Waaqayyo galataa fi ulfina haa fudhatu! ''....Hojichi guddaadhaa fi bal'aadha...'' Nahimiyaa 4:19 ''..."Nuuyi garboonni Isaa kaanee ijaaruu in jalqabna Waaqayyo Gooftaan bantii waaqaa immoo nuuf qajeelcha...'' Nahimiyaa 2:20 === === ከሲኖዶሶች የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መሪዎች ጋር የህብረት (Fellowship): የስልጠና: እና የምክክር ጊዜ በጉዲና ቱምሳ ሁለንተናዊ የስልጠና ማዕከል, አዲስ አበባ ሁለንተናዊ አገልግሎት ለልጆች እና ወጣቶች ሁለንተናዊ ለውጥ እና ዕድገት YEROO TOKKUMMAA, LEENJII FI MARII TAJAAJILTOOTA IJOOLLEE FI DARGAGGOO WWWMAKAANA YESUUS SINOODOSOTARRAA DHUFAN WALIIN, Giddugala Leenjii Hundagaleessaa Guddinaa Tumsaatti, Finfinnee === Fellowship, Training & Consultation Time of Children & Youth Ministry Leaders of EECMY Synods, @Gudina Tumsa Wholistic Training Center (Day 1) The EECMY Children and Youth Ministry Department is providing training for newly established synods and newly elected children and youth ministry leaders at Gudina Tumsa Wholistic Training Center. The training is mainly focused on the Wholistic Ministry Package of Children and Youth, designed and being implemented by the department since the 1st quarter of 2022. In addition to the wholistic ministry package, additional training on selected topics from the package has been started and will continue tomorrow. ''...The work is great and extensive...' Nehemiah 4:19 ''...The God of heaven, He will prosper us; therefore we His servants will arise and build...'' Nehemiah 2:20 Soli Deo Gloria! = Glory to God Alone! 👇👇👇 https://t.me/eecmyyouthministry https://t.me/MYSundaySchool #EECMY #Children #Youth #MekaneYesus #Ethiopia The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus

The Aira General Hospital water system that was built by missionaries three decades ago is used by the residents of the Hospital and the area around it. However, due to a considerable rise in the town's population and a decrease in water discharge as a result of climate change, the plan was unable to meet the needs of the community. As a result, the program only benefits the community six months out of the year. Therefore, the community were required to travel 70 minutes for a round trip to gather water from a river to meet their household's daily water consumption requirements of 120 liters. Most of the family members, especially the children, were significantly impacted by water-born infections because they were drinking river water. In addition to being time-consuming, fetching water takes up time that they should be spending working. Above all, they found their life to be arduous due to the hospital's water deficit. In the hospital, they claimed, "there was no water to the point where patients couldn't find water to take the pills." Everything has changed since then. "We appreciate EECMY-DASSC, Neverthirst's and its back donor's unwavering efforts to provide us with clean water." The hospital now has water service for all of its facilities, and cleanliness and hygiene have greatly improved. They continued by saying that we must concentrate on finding ways to maintain the services and pay for the upkeep and operation of the water schemes. ከሶስት አስርተ አመታት በፊት በሚስዮናውያን የተገነባው የአይራ አጠቃላይ ሆስፒታል የውሃ አቅርቦት ስርዓት ለሆስፒታሉ እና ለአካባቢው ነዋሪዎች ጥቅም ሲሰጥ ቆይቷል። ነገር ግን የከተማው ህዝብ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ በመምጣቱ እና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የውሃ መጠን በመቀነሱ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የስድስት ወር ብቻ አቅርቦት በመስጠቱ የህብረተሰቡን ፍላጎት ማሟላት አልቻለም። በመሆኑም ህብረተሰቡ በቀን የሚፈልገውን 120 ሊትር የውሃ ፍጆታ ለማሟላት ከወንዝ ውሃ ለመቅዳት የ70 ደቂቃ ጉዞ ለማድረግ ተገዷል። አብዛኛዎቹ የቤተሰብ አባላት በተለይም ህጻናት የወንዝ ውሃ ስለሚጠጡ በውሃ ወለድ ኢንፌክሽን ከፍተኛ የጤና እክል አጋጥሟቸዋል። ውሃ መቅዳት ብዙ ጊዜ ከመውሰዱ የተነሳ ለሥራ የሚያውሉትን ጊዜ አቃጥሎባቸዋል። ከሁሉም በላይ በሆስፒታሉ በተከሰተው የውሃ እጥረት የተጠቃሚዎች ህይወት ችግር ገጥሞታል። በሆስፒታሉ ውስጥ ታካሚዎች ክኒኖችን ለመውሰድ እንኳ የውሃ እጥረት ተከስቶ እንደነበር ተጠቃሚዎች በማስታወስ አሁን ላይ ሁሉም ነገር ተለውጦ EECMY-DASSC፣ Neverthirst እንዲሁም ከጀርባ ሆኖ ይህንን ንጹህ ውሃ በመለገስ ያላሰለሰ ጥረት ውስጥ የተሳተፉትን አካላት ሁሉ ያመሰግናሉ። ሆስፒታሉ አሁን ለሚያከናውነው ስራ በሙሉ የውሃ አገልግሎት ያለው ሲሆን ንፅህናን በተመለከተም እጅግ ተሻሽሏል ። ይህንን አገልግሎት ለማስቀጠል እንዲሁም ጥገናን በተመለከተ ለወደፊቱ መንገድ መቀየስ እንደሚገባም ተናግረዋል ።

የድሬዳዋ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናንን ወቅታዊ ሁኔታ በመሚመለከት ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የተሰጠ መግለጫ፤ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ፤ የድሬዳዋ ማህበረ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያን ህንጻና ሌሎች ተያያዥ ህንጻዎች ያሉበትን ይዞታ ለሌላ አገልግሎት ለማዋል በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ካብኔ የተላለፈው ውሳኔ ቤተ ክርሰቲያናችንን ብቻ ሳይሆን መላውን ህዝበ ምዕመን በእጅጉ አስደንግጧል፡፡ እናም ውሳኔው እንደገና እንዲጤን ቤተ ክርስቲያኒቱ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር ብርቱ ክትትል በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡ የከተማው አስተዳደርም በተለይም ክቡር ከንቲባው ሁኔታውን በጥንቃቄና በሃላፊነት ስሜት እየተከታተሉ ሲሆን ከቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር ጋርም ለመምከር ቀጠሮ ተይዟል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ጉዳዩ የማይመለከተውና በየትኛም መንገድ ድርሻ የሌለው አንድ አካል፤ ችግሩ መፍትሔ እንዳገኘ አድርጎ በዛሬው ዕለት በራሱ ማህበራዊ ገጽ (Facebook) የተሳሳተ መረጃ አውጥቷል፡፡ ይህን የፈጸመው አካል ይህንን ስህተት በአስቸኳይ እንዲያርም ጥብቅ ማሳሰቢያ የደረሰው መሆኑን እየገለጽን ቤተ ክርስቲያኒቱ እስከምታውቀው ድረስ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ምንም ዓይነት ውሳኔ ያልተሠጠ መሆኑንና ለወደፊትም ቤተ ክርስቲያኒቱ በራስዋ አሠራር ኦፊሴላዊ መረጃ እስከምትሰጥ ድረስ ህዝበ ምዕመኑ በትዕግስትና በጸሎት እንዲጠባበቅ እናሳስባለን፡፡ እግዚአብሔር አገራችንን ይባርክ፤ ይጠብቃትም! የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ

የአርባ ምንጭ እናት ማህበረ ምዕመናን የተመሰረተችበትን 50ኛ የወርቅ ኢዬቤልዩ በዓል በታላቅ ኮንፍራንስ አከበረች * * * * በአርባ ምንጭ ከተማ ለሚገኙ 12 ማህበራነ ምዕመናን እና አጠቃላይ በአከባቢው ላለው የወንጌል አገልግሎት እናት የሆነችው የአርባ ምንጭ ማህበረ ምዕመናን ከጥቅምት 16-18 በተዘጋጀ የምስጋና ኮንፍራንስ 50ኛ አመት የምስረታ በዓልዋን አክብራለች። አርብ ጥቅምት 16 በከተማዋ ጎዳናዎች የእግር ጉዞ፣ የፀሎትና የጀማ ስብከት በማድረግ የተጀመረው ኮንፍራንስ እሁድን ቀጥሎ የዋል ሲሆን በበዓሉም ላይ የቤተ ክርስቲያኒቱና የሲኖዶስ መሪዎች፣ ከኖርዌይ ሉተራን ሚሲዬን አገልግሎት የመጡ እንግዶች እና የከተማዋ ወንጌላዊያን አማኞች በተገኙበት በአምልኮና በታላቅ ምስጋና ተከብሯል። የማህበረ ምዕመኗ ምስረታ የኖርዌይ ሉተራን ሚሲዬን ለከተማዋ እና ለአከባቢው ማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ የአርባ ምንጭ ተግባረ ዕድ ት/ቤትን እና የአርባ ምንጭ ሆስፒታልን ከ1958-1961 ማቋቋሙን ተከትሎ በተፈጠረው የወንጌል በር አማካኝነት ወደ ጌታ ለመጡ ወገኖች አገልግሎት ለመስጠት በ1963 በታነጸ የአምልኮ አዳራሽ በታናሽ ጅማሮ የተጀመረ አገልግሎት ሲሆን ባለፉት 50 ዓመታት ብዙ ተግዳሮቶችን በማለፍ፣ በታላቅ እድገት እና ብዙ ፍሬዎችን በማፍራት እዚህ ደርሳለች። በተለይም ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ስደት ውስጥ ባለፈችበት የደርግ ዘመን ሁሉንም የወንጌል አማኞችን አቅፋ በመያዝና በማገልገል መለኮታዊ ጥሪዋን የተወጣች እናት ማህበር ነች። ሌላው በአሉንም ድርብ የሚያደርገው የኖርዌይ ሉተራን ሚስዬ በኢትዮጲያ የሚስዬን አገልግሎት የጀመረበትን 75ኛ አመት በጋራ መከበሩም ሲሆን በበዓሉም የማጠቃለያ ቀን ማህበረ ምዕመኗ ለኖርዌይ ሚስዮን ማህበር፣ ረጅም አመታት ላገለገሉ ሚስዮናዊያን፣ ለአንጋፋ አገልጋዮች፣ ለቤተ ክርስቲያን ዋናው ጽሕፈት ቤት እና ለማህበሯ እድገት አስተዋፆ ላበረከቱ አካላት እውቅና ሰጥታለች።

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus Development and Social Services Commission (EECMY-DASSC) 101th Regular Board meeting is taking place at Elili International Hotel, Addis Ababa. የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ-ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የልማትና መህበራዊ አገልግሎቶች ኮምሽን 101ኛ መደበኛ የቦርድ ስብሰባ በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል አዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። #EECMY_DASSC

Today Oct 28,2023 EECMY-CES Theological College has successfully graduated 64 students from the Adama Bole congregation center. What a wonderful celebration! Congratulations to the graduates! Go in peace and serve the Lord! በዛሬው ዕለት ጥቅምት 17 ቀን 2016 EECMY-CES- ሥነ -መለኮት ኮሌጅ በአዳማ ከተማ በቦሌ መካነ ኢየሱስ ማ/ምዕመን ሲማሩ የነበሩትን 64 ተማሪዎች አስመርቆአል ። እጅግ የሚያስደንቅ ውብ ጊዜ ነበረን ወደ አለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ!! እንኳን ደስ አላችሁ!!! EECMY-CES-Kolleejjiin Ti'ooloojii barattoota 64 kan Adamaatti waldaa Booleetti baratan eebbisuu danda'eera .yeroo ajaa'ibaa Dinqisiisaa dabarsinee . baga gammaddan !!! Gara biyya lafaa hundumaa dhaqaa! Uumama hundumaattis wangeela lallabaa!

Since the day of receiving the letter asking the congregation to vacate from her property, the leaders of the church and the Central Ethiopian Synod have been paying special attention to the matter and are communicating concerning bodies. Hoping to receive prompt response, the church would like to extend her gratitude to all those who stood by her side over social media and various ways and those who requested to give professional assistance. The church urges the owner of the decision to reconsider the matter and inquires christians, gospel believers, and members of the church to pray for the congregation. May God grant peace to our country and its people! EECMY