es
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Ir al canal en Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Mostrar más
1 160
Suscriptores
-124 horas
+17 días
+530 días
Archivo de publicaciones
🌟ዛሬ ጠዋት 2:30 እግሮች ሁሉ ወደ አቅሷ መስጂድ ያመራሉ!! 📌 ታላላቅ እንግዶች የሚታደሙበት፤ 📌 ለአመታት አብረዉን የቆዩ የጊቢያችንን ሙስሊም ተማሪዎችና የህብረታችን ልጆች የምንሸኝበት፤ እ
🌟ዛሬ ጠዋት 2:30 እግሮች ሁሉ ወደ አቅሷ መስጂድ ያመራሉ!! 📌 ታላላቅ እንግዶች የሚታደሙበት፤ 📌  ለአመታት አብረዉን የቆዩ የጊቢያችንን ሙስሊም ተማሪዎችና የህብረታችን ልጆች የምንሸኝበት፤ እና 📌የተለያዩ ቁም-ነገር አዘል ትምህርቶችን የምንቀስምበት ፕሮግራማችን እነሆ ተሰናድቶ ታዳሚውን በመጠባበቅ ላይ ነው ታላቁ የዳዕዋ እና የሽኝት ፕሮግራም  ሊጀመር ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ቀርቶታል! 🕔 ታላቅ ፕሮግራም በታላቁ አል-አቅሷ መስጂድ፣ 02፡30 ጀምሮ! ሁሉም የአአዩ ተማሪዎች እንዲታደሙ ተጋብዘዋል!

🌟 1 ቀን ብቻ ቀረው🌟 ታላቅ የዳዕዋ እና የሽኝት ፕሮግራም! ነገ ጠዋት 2:30 እግሮች ሁሉ ወደ አቅሷ መስጂድ ያመራሉ!! 📌 ታላላቅ እንግዶች የሚታደሙበት፤ 📌 ለአመታት አብረዉን የቆዩ የጊቢ
🌟 1 ቀን ብቻ ቀረው🌟 ታላቅ የዳዕዋ እና የሽኝት ፕሮግራም! ነገ ጠዋት 2:30 እግሮች ሁሉ ወደ አቅሷ መስጂድ ያመራሉ!! 📌 ታላላቅ እንግዶች የሚታደሙበት፤ 📌  ለአመታት አብረዉን የቆዩ የጊቢያችንን ሙስሊም ተማሪዎችና የህብረታችን ልጆች የምንሸኝበት፤ እና 📌የተለያዩ ቁም-ነገር አዘል ትምህርቶችን የምንቀስምበት ፕሮግራማችን እነሆ ሰዓታት ብቻ ቀርተውታል ታላቁ የዳዕዋ እና የሽኝት ፕሮግራም የአንድ ቀን እድሜ ብቻ ቀርቶታል! 🕔 ታላቅ ፕሮግራም በታላቁ አል-አቅሷ መስጂድ፣ ነገ ከጠዋቱ 02፡30 ጀምሮ! ሁሉም የአአዩ ተማሪዎች እንዲታደሙ ተጋብዘዋል! @aaumsu

💡ዲንን አጥብቆ በመያዝ፣ በመተግበር ላይ ባይተዋርነት ሊያጋጥም ይችላልና ትዕግስት አድርግ! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿طُوبىٰ لِلغُرباء؛ قيل: وَمَن الغُرَباء يا رَسول الله؟ قال: ناسٌ صالِحون قَليلٌ في ناسِ سَوْءٍ كَثير؛ مَنْ يَعصيهِمْ أكثَرُ مِمّن يُطيعُهُم﴾ “ባይተዋሮች ጀነት አለችላቸው። አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! እነማን ናቸው ባይተዋሮቹ? ሲባሉ። ከብዙ ክፉ ሰዎች መሃል ያሉ ጥቂት ደጋግ ሰዎች ናቸው። ከሚታዘዛቸው ይልቅ የሚያምፃቸው ይበዛል።” 📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ፡ 1619

🌟አሰላሙ ዓለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካቱህ!! የዛሬው የጉብኝት መርሃ-ግብር ማስታወሻ፦ ​🕗 ሰዓት፦ ጠዋት 3:00- 6:00 ​📍 ቦታ፦ የሲር ላና የበጎ አድራጎት ድርጅት ​🚎 ትራንስፖርት፦ በጀመዓው ተዘጋጅቷል ስንመጣ በግል አልባሳት መስጠት የፈለግን መያዙን አንርሳ እና በገንዘብ መሳተፍ የምትፈልጉም በዚሁ የባንክ አካውንት ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ፦ ​የንግድ ባንክ (CBE): 1000580172214 ስም: Masud Wubetu @fivekjemaa

🌟አሰላሙ ዓለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካቱህ!! የዛሬው የጉብኝት መርሃ-ግብር ማስታወሻ፦ ​🕗 ሰዓት፦ ጠዋት 3:00- 6:00 ​📍 ቦታ፦ የሲር ላና የበጎ አድራጎት ድርጅት ​🚎 ትራንስፖርት፦ በጀመዓው ተዘጋጅቷል ስንመጣ በግል አልባሳት መስጠት የፈለግን መያዙን አንርሳ እና በገንዘብ መሳተፍ የምትፈልጉም በዚሁ የባንክ አካውንት ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ፦ ​የንግድ ባንክ (CBE): 1000580172214 ስም: Masud Wubetu @fivekjemaa

"እኛ አፋሮች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና በአክሱም ሙስሊሞች ላይ የሚደርሰውን በደል እንቃወማለን። ኒቃቧንም ትለብሳለች፤ ትምህርቷንም ትማራለች።" በአፋር ካሉ ሙስሊም ወንድሞች አመሻሹን የተላከ የ
"እኛ አፋሮች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና በአክሱም ሙስሊሞች ላይ የሚደርሰውን በደል እንቃወማለን። ኒቃቧንም ትለብሳለች፤ ትምህርቷንም ትማራለች።" በአፋር ካሉ ሙስሊም ወንድሞች አመሻሹን የተላከ የአብሮነት መልዕክት ነው። ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው። ከአፋር ጀምሮ እስከ ሶማሌ፤ ከባሌ ጀምሮ እስከ ደሴ ያለውን ሙስሊም ይመለከታል። የእምነት፣ የማንነት፣ የክብር ጉዳይ ነውና። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! @aaumsu

የጊዜ ገደቡ ተጠናቋል፤ ሰበቦቹ ግን ቀጥለዋል! ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ የመንግስት አካላት እና የዩኒቨርሲቲው አመራሮች አፋጣኝ የውይይት መድረክ እንደሚያዘጋጁ ቃል መግባታቸው ይታወሳል። እኛም የተገባውን ቃል በማክበር ይህንን ሳምንት እንደ የመጨረሻ የትዕግስት ጊዜ ሰጥተን ነበር። ነገር ግን ዛሬ ጁምዓ (ግንቦት 14) ቢደርስም፣ ከተማሪዎች እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ምንም አይነት ቀጥተኛ ውይይት እስካሁን አልተካሄደም። በውይይት ጠረጴዛ ዙሪያ ከመቀመጥ ይልቅ፣ የሚመለከታቸው አካላት አሁንም የተለያዩ ሰበቦችን እየደረደሩ ይገኛሉ። አቋማችን አሁንም የፀና ነው፤ መብቱን የጠየቀን ንፁህ እና ሰላማዊ ተማሪ በቢሮክራሲ ማድረቅና ማሸማቀቅ አይቻልም። ለሚመለከታችሁ አካላት ሁሉ የምናስተላልፈው መልዕክት አጭርና ግልጽ ነው፦ ህጉን አስተካክሉ እንጂ መፍትሔን አታዘግዩ! ለተማሪዎቻችን:- የሰጠነው የጊዜ ገደብ አብቅቷልና ንቃታችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ እናሳስባለን። ከዚህ በኋላ ለሚፈጠረው ማናቸውም ነገር ኃላፊነቱን የሚወስዱት ቃላቸውን ያጠፉት አካላት ናቸው። ቀጣዩን አቅጣጫ እና የትግል እርምጃ በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል! አሁንም ጥያቄ አለን! ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ! @aaumsu

የአረፋ ቀን ፆም ታላቅ ምንዳ ​የአንድ ቀን ፆም የሁለት አመት ወንጀል የሚያብስበት አስደናቂ ቀን! 🌙 ​ከአስሩ ቀናት ውስጥ 9ኛው ቀን (የአረፋ ቀን) ለአላህ እጅግ ተወዳጅ የሆነ ቀን ነው። ሐጅ ላይ የሌለን ሰዎች ይህንን ቀን መፆም ትልቅ እደል ነው። የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ስለ አረፋ ቀን ፆም ሲጠየቁ እንዲህ አሉ። "የአለፈውን አመትና የመጪውን አመት (ትናንሽ) ወንጀሎች ያስምራል።" (ሶሒህ ሙስሊም)

🌙✨ ዛሬ ሁለት ታላላቅ ነገሮች 🎉✨✨ ተሰብስበዋል… 🕌 የጁምዓ ቀን 🌿 የዙልሒጃ ታላላቅ ቀናት 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ }    ✨✨   ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ  ✨✨ 💻 በስራ ብንጠመድም 📝 በፈተና እና በድካም መካከል ብንሆንም 🤍 ልባችንን ከአላህ ዚክር አናርቅ ✨ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ “በእነዚህ ቀናት የሚሰራ መልካም ስራ ከሌሎች ቀናት ይበልጥ በአላህ ዘንድ ተወዳጅ ነው” 🌿 ምናልባት… ዛሬ የምናደርገው ትንሽ ሰለዋት ወይም አንዲት “الله أكبر” ወይም ከልብ የወጣች ዱዓ በአላህ ዘንድ ትልቅ ሚዛን ልትሆን ትችላለች … ✨ ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣ ሰለዋት  ጭንቀትን ይቀንሳል፣ ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣.........በነቢዩ ﷺ ላይ            ሰለዋትን እናብዛ✨✨ ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ ‣ በመጨረሻው ሰአት (ከአስር በኋላ ) ዱዓ ማድረግ- እስልምናን ለማስከበር ለሚታገሉ እህት/ወንድሞቻችን በዱዓ እናስታውሳቸው ፣ ይህ መታደል ነውና አላህ እኛንም ከሚታገሉት እንዲያደርገን ዱዓ እናብዛ !! اللَّهُمَّ اجعلنا من الذين يثبتون على صراطك، وثبت قلوبنا على طاعتك، وانصرنا على أنفسنا وأعدائنا، واجعلنا من المجاهدين في سبيلك بالعلم والعمل، ومن الداعين إلى كتابك وسنة نبيك ﷺ، وارزقنا الصدق والإخلاص والثبات على الدين حتى نلقاك 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

🌙✨ ዛሬ ሁለት ታላላቅ ነገሮች 🎉✨✨ ተሰብስበዋል… 🕌 የጁምዓ ቀን 🌿 የዙልሒጃ ታላላቅ ቀናት 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِي
🌙✨ ዛሬ ሁለት ታላላቅ ነገሮች 🎉✨✨ ተሰብስበዋል… 🕌 የጁምዓ ቀን 🌿 የዙልሒጃ ታላላቅ ቀናት 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ }    ✨✨   ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ  ✨✨ 💻 በስራ ብንጠመድም 📝 በፈተና እና በድካም መካከል ብንሆንም 🤍 ልባችንን ከአላህ ዚክር አናርቅ ✨ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ “በእነዚህ ቀናት የሚሰራ መልካም ስራ ከሌሎች ቀናት ይበልጥ በአላህ ዘንድ ተወዳጅ ነው” 🌿 ምናልባት… ዛሬ የምናደርገው ትንሽ ሰለዋት ወይም አንዲት “الله أكبر” ወይም ከልብ የወጣች ዱዓ በአላህ ዘንድ ትልቅ ሚዛን ልትሆን ትችላለች … ✨ ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣ ሰለዋት  ጭንቀትን ይቀንሳል፣ ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣ ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ ‣ በመጨረሻው ሰአት (ከአስር በኋላ ) ዱዓ ማድረግ- እስልምናን ለማስከበር ለሚታገሉ እህት/ወንድሞቻችን በዱዓ እናስታውሳቸው!! اللَّهُمَّ اجعلهم مِنَ الَّذِينَ يَثْبُتُونَ عَلَى صِرَاطِكَ، وَثَبِّتْ قُلُوبَهُمْ عَلَى طَاعَتِكَ، وَانْصُرْهُمْ عَلَى أَنْفُسِهِمْ وَأَعْدَائِهِمْ 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

🌟 ታላቅ የዳዕዋ እና የሽኝት ፕሮግራም! 🌟 ⭐️ Grand Da'wa and Well Go Program ⭐️ በአላህ ﷻ ፈቃድ ልቦች ለአላህ ሲሉ የሚገናኙበትና ፈጽሞ ሊያመልጥዎት የማይገባ ታላቅ የዳዕ
🌟 ታላቅ የዳዕዋ እና የሽኝት ፕሮግራም! 🌟 ⭐️ Grand Da'wa and Well Go Program ⭐️ በአላህ ﷻ ፈቃድ ልቦች ለአላህ ሲሉ የሚገናኙበትና ፈጽሞ ሊያመልጥዎት የማይገባ ታላቅ የዳዕዋ እና የሽኝት ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ይጠብቅዎታል። በተከበሩ እንግዶቻችን መገኘት የምንማርበትና የምንነቃቃበት፣ እንዲሁም ለዓመታት የህብረታችን አካልና የጉዟችን አጋር የነበሩትን ውድ ሙስሊም ወንድሞችና እህቶቻችንን በታላቅ ክብርና ፍቅር የምንሸኝበት ልዩ ዕለት ነው። ይህ ፕሮግራም መጪው እሑድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ል (May 24, 2026) በአል-አቅሷ መስጂድ የሚካሄድ ሲሆን፣ በአላህ ፈቃድ ከጠዋቱ 2፡30 (08:30 AM) ሰዓት ላይ የሚጀምር ይሆናል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ ለመማር፣ ለማስተንተንና መንፈስን ለማደስ በዚህ ፕሮግራም ላይ እንድትገኙ በታላቅ አክብሮት ተጋብዛችኋል። ሁላችሁም ተጋብዛችኋል! ✨ @aaumsu

ኑ በነዚህ ውብና የተወደዱ ቀናት ወደኸይር እናቅና ! 🌟አሰላሙ ዓለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካቱህ በአላህ ፍቃድ በመጭው ቅዳሜ  የሲር ለና የበጎ አድራጎት ድርጅትን ልንጎበኝ ከናንተ ጋ ቀጠሮ ይዘናል። በኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ አማካኝነት ተመስርቶ ዋና አላማውን የቲም ልጆችን መንከባከብ በማድረግ ፣ አረጋውያን እናትና አባቶችን፣ ስራ ያጡ ወንድምና እህቶችን ከዚህ ባሻገር በቋሚነት በስሩ ሚመግቧቸው ፣ሚያለብሷቸው እናቶች የቲሞች እንዲሁም በእስር ላይ የሚገኙ ጠያቂ ያጡ ሰዎችን በስሩ በማጠቃለል እየሰራ ያለ ድርጅት ነው ።ከዚህም ተጨማሪ በተለያዩ መጥፎ ሱሶች ላይ የተዘፈቁ ወጣቶችን በመርዳትና በብቁ ባለሙያዎች የሙያ ስልጠናዎችን በመስጠትም ለወጣቱም አለሁኝ እያለ ነው ። 💡 ታዲያ ሙስሊም ክርስቲያን ሳይል ለመደገፍና ለመለወጥ እየሰራ የሚገኘውን የሲር ለናን ለመዘየር ከኛጋ ለመምጣት ፈቃደኛ ነዎት❓ ፍቃደኛ ከሆኑ ቅዳሜ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ቀጠሮዎትን ከኛ ጋ ያድርጉ። ታዲያ ስንጎበኝ ባዶ እጃችንን መሄድ የለብንም ብለን ስላሰብን፤ ከእናንተ ከ5 ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች አንዳንንድ ነገሮችን ልንይዝ አስበናል። በመሆኑም የቻለ ልብስ ያልቻለ ደግሞ ጥሬ ገንዘብ  በመስጠት ሰደቃ ማድረግ ይችላል። በገንዘብ መሳተፍ የምትፈልጉ በዚሁ የባንክ አካውንት ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ፦ ​የንግድ ባንክ (CBE): 1000580172214 ስም: Masud Wubetu ➡️ ለወንዶች ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉ በዚ ስልክ ብትደውሉ  (0905877461) ካሉበት መተን እንቀበላችኃለን አልያም ዶርም ቁጥር 302 መታችሁ መስጠት ትችላላችሁ። ➡️ ለሴቶች በሴቶች በኩል የሚቀበሉ ስላሉ ለነሱ መስጠት ትችላላችሁ። ​የቅዳሜው የጉብኝት መርሃ-ግብር ማስታወሻ፦ ​🗓 ቀን፦ ቅዳሜ ግንቦት 15/2018 (May 23, 2026) ​🕗 ሰዓት፦ ጠዋት 3:00- 6:00 ​📍 ቦታ፦ የሲር ላና የበጎ አድራጎት ድርጅት ​🚎 ትራንስፖርት፦ በጀመዓው ተዘጋጅቷል ​አሁኑኑ ይመዝገቡ! አብረውን ለመሄድ ከታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ። ‼️የምትደግፉትን የብር መጠን መመዝገብዎን አይርሱ፦👇 https://forms.gle/eD8h1yftiDCkscEq8@fivekjemaa

photo content

በነዚህ የተከበሩ ቀናቶች ወንጀልን መራቅ አለብን ኢብኑ ረጀብ እንድህ ይላሉ:- «ወንጀልን ተጠንቀቁ እርሷ በምታዘንባቸው አጋሚዎች መሀርታን ትከለክላለች» «ወንጀል(አላህን ማመፅ) ከአላህ እዝነት የመራቅ እና የመባረር ሰበብ ስለሆነች ተጠንቀቁ» [ለጧኢፉል መዓሪፍ (254)]

🌟 Second Round Charity Field Trip 🌟 🤍 “The best hearts are the ones that care for others.” After the beautiful memories from our first visit, we are once again preparing for a special journey of compassion and brotherhood/sisterhood. 📅 Saturday, May 23, 2026 📍 Yesir Lena Charity Organization3:00 – 6:00 LT ✨ This visit comes during the first 10 days of Dhul Hijjah, the most beloved days to Allah for righteous deeds. 🌱 A small donation. 🌱 A small effort. 🌱 A small smile. May become something huge in the sight of Allah. ✨ Why join? • Help others directly • Share meaningful moments together • Gain reward during these blessed days of Dhul Hijjah 🎁 Donations & Registration 👕 Clothes will be collected by rounding through dormitories, and students may directly bring donations during the visit. 📝 Registration is required. Please fill out the registration form and include the amount of birr you wish to donate. 🚌 Transportation will be available. ✨ Let us make this second visit warmer and more impactful than the first one. Come with your friends. Come with sincerity. Come with a heart ready to give. 🤍

photo content

ለዩኒቨርስቲ ጀመዓዎች፤ ለኸጢቦች፤ ለኢማሞች፤ ለኡስታዞች እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕናዎች፦ ባለፈው ጁምዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሚገኙ ሙስሊም ተማሪዎች በኒቃብ ምክንያት እየደረሰባቸው ያለውን የመብ
ለዩኒቨርስቲ ጀመዓዎች፤ ለኸጢቦች፤ ለኢማሞች፤ ለኡስታዞች እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕናዎች፦   ባለፈው ጁምዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሚገኙ ሙስሊም ተማሪዎች በኒቃብ ምክንያት እየደረሰባቸው ያለውን የመብት ጥሰት እና እንግልት አቤት ለማለት ከዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ቢገኙም ጥሪያቸውን የሚሰማ ጠፍቶ እስከ ምሽት 4:30 ብርድ እና ፀሐይ ከፌደራል ማስፈራሪያ ጋር እየተፈራረቀባቸው መቆየታቸው የሚታወስ ነው። መጨረሻ አካባቢ ለማናገር የመጡ ኡስታዞች፣ የሰላም ሚኒስቴር ሰዎች፣ የሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ አመራሮች ወዘተ ... መጥተው ውይይት ለካሂዶ ዘላቂ መፍትሔ እንደሚመጣ ቢገልፁም እስካሁን ባለው የተባለው ውይይት አልተካሄደም። የዩኒቨርስቲው አካላትም በጀመሩት የመብት ጥሰት እንደቀጠሉ ናቸው።   ስለሆነም በመጪው ጁምዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ላሉ ሙስሊም እህት ወንድሞቻችሁ ዱዓ እንድታደርጉ፤ እየደረሰባቸው ስላለው ነገር በኹጥባዎቻችሁ እንድታደርሱ እንዲሁም አጋርነታችሁን እንድታሳዩ እንጠይቃለን። @aaumsu

💥 ደርስ ማስታወሻ ::::::::::::::::::::::: 🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ 👋👋👋 🔵 ጠያቂ : ሸይኽ አሰላሙ አለይኩም ⚫️ ሸይኽ : ወዐለይኩሙ ሰላም ተፈደሊ ምን ልርዳሽ 🔵 ጠያቂ : ጓደኛዬ አግብታለች እኔ ላገባ ነበር... ⚫️ ሸይኽ : ማሻአላህ ደስ ይላል... እና 🔵 ጠይቅ : የባሎችን ሀቅ እና ከነሱ ጋር እንዴት መኖር እንዳለብን ምክር ፈልጌ ነበር እንደው ካላስቸገርኩኝ ⚫️ሸይኽ : መርሀባ አብሽሪ የ4ኪሎ ተማሪ ከሆናችሁ በቃ ዛሬ የተማሪዎች መስጂድ የሚሰጥ ደርስ አለ እሱ ላይ ጋብዤሻለው 🔵 ጠያቂ : ሹክረን ⚫️ ሸይኽ : ደርስ ላይ የባል እና የሚስት ሀቅ እናያለን ሌሎችንም ጋብዢ መግቢያ ዋጋ አሰላሙ አለይኩም ማለት ብቻ ነው መስጂድ ስትገቢ 🔵 ጠያቂ : መርሀባ 📚ሙዳራቱ ዘውጅ 📌የቂርዐት ቦታ ፦ 4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ ⏰የቂርዐት ሰዐት፦ ከመጝሪብ እስከ ዒሻ

🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋 ✅ኢንሻአላህ ዛሬ (እሮብ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ።  5ኪሎ እና 6ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል  ቡዙ እናተርፍለን። "مَنْ سَلَكَ طَرِيقًا يَلْتَمِسُ فِيهِ عِلْمًا، سَهَّلَ اللَّهُ لَهُ بِهِ طَرِيقًا إِلَى الْجَنَّةِ" «በሱ ውስጥ እውቀትን ለመፈለግ ብሎ መንገድ የጀመረ  ሰው አላህ የጀነትን መንገድ ያገራለታል» ነብዩ ﷺ ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ ቦታ፡ አቅሳ መስጅድ 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/durus_at_aqsa ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934 @fivekjemaa

🌟 ያለንበትን ወቅት እናስተውል! ለዱኒያም ለአኼራም በማይጠቀም ነገር ራሳችንን ቢዚ አናድርግ! ባለንበት ወቅት የምንሰራው ኢባዳ ከሌላው ግዜ በላቀ አላህ ዘንድ የተወደደ ነውና! 🕋 አላሁ አክበር! አላሁ አክበር! አላሁ አክበር! ላኢላአሃ ኢለላህ! አላሁ አክበር አላሁ አክበር ወሊላሂልሃምድ! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿ما أَهَلَّ مُهِلٌّ قطُّ إلّا بُشِّرَ، ولا كَبَّرَ مُكَبِّرٌ قطُّ إلّا بُشِّرَ، قيل: بالجنةِ؟ قال: نَعَمْ﴾ “ድምፁን ከፍ በማድረግ ኢኽላል የሚያደርግ (ላኢላአሃ ኢለላህ የሚል) አንድም አይኖርም ብስራት የሚደረግ ቢሆን እንጂ። እንዲሁም ድምፁን ከፍ በማድረግ ተክቢር የሚያደርግ (አላሁ አክበር የሚል) አንድም አይኖርም ብስራት የሚደረግ ቢሆን እንጂ። እንዲህ ተባሉ፦ ብስራቱ ጀነት ነውን? አዎን! አሉ።” 📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ፡ 1621