es
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Canal cerrado
1 146
Suscriptores
-224 horas
-47 días
-1930 días
Archivo de publicaciones
photo content

photo content

ዕለተ ሐሙስ የካቲት 20/2017ዓ.ም አካል ጉዳተኝነትን አስመልክቶ የግንዛቤ መፍጠሪያ                          መድረክ ተካሄደ። ቱጌዘር በተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ዓይነ- ስውርነትን አስመልክቶ ያለውን የተሳሳተ አመለካከት ለማስተካከልና ዓይነ ስውራንን ለመርዳት /ለማገዝ እንዲሁም  መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና በተለያዩ ጉዳዮች ወደ ኮሌጃችን የሚመጡ ማየት የተሳናቸውን ወገኖች እንዴት መርዳት እንዳለብን እንዲሁም መደረግ ስላለበት ቅደም ተከተል ውይይት ተካሂዷል። አቶ መአዛ ሃይማኖት ወርቁ የህዳሴ አካል ጉዳተኞች ማህበር ስራስኪያጅ አካል ጉዳተኞች ምን ይፈልጋሉ ? በተለይ  ዓይነ ስውራን ምን ይፈልጋሉ ? በሚለው ርዕሰ ጉዳይ ላይ ዘርዘር ያለ መረጃ አስተላልፈው ድጋፋችን በምርጫቸው ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ፣ ሰብአዊ ክብራቸውን የማይነካ፣ ከአድልዎና መገለል የፀዳ፣ ውጤታማ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚያስችልና ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ምክራቸውን ለግሰዋል ።  አካል ጉዳተኞች በሚፈልጉት እና በሚመጥናቸው  ስልጠናዎችን ካገኙ እና ከተደገፉ ማንኛውንም ስራ መስራት የሚችሉ መሆኑን ጠቁመዋል። በተመሳሳይ የድርጅቱ ባልደረባ ወ/ሪት ማርታ ንጉሴ የቱጌዘር ፕሮጀክት አስተባባሪ ስትሆን ድርጅቱ የሚሰጠውን አገልግሎትና ተደራሽነቱን ጠቁመው ሴትነት እና ዓይነ-ስውርነት ያለውን ተደራራቢ ጫና አስመልክተው በቡና ጠጡ ፕሮግራም ማብራሪያ ሰጥተውበታል።  የአይነስውራንን ጫና ለመረዳት የሚያስችል ለ15 ደቂቃ አይንን በመጨፈን እና በመሸፈን ስሜታቸውን ለመዳት የሚያስችል የመማማሪያ መድረክ ተፈጥሯል። በመጨረሻም ከቤቱ ሃሳብ አስተያየት ተነስቶ ውይይት ተካሂዶበታል። ለቀጣይ ከኮሌጁ ጋር በጋራ ቢሰራበት ያሉትንም ጠቁመዋል ።               ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ሐሙስ የካቲት 20/2017ዓ.ም አካል ጉዳተኝነትን አስመልክቶ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተካሄደ። ቱጌዘር በተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ዓይነ- ስውርነትን አስመልክቶ ያለውን የተሳሳተ አመ
+7
ዕለተ ሐሙስ የካቲት 20/2017ዓ.ም አካል ጉዳተኝነትን አስመልክቶ የግንዛቤ መፍጠሪያ                          መድረክ ተካሄደ። ቱጌዘር በተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ዓይነ- ስውርነትን አስመልክቶ ያለውን የተሳሳተ አመለካከት ለማስተካከልና ዓይነ ስውራንን ለመርዳት /ለማገዝ እንዲሁም  መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና በተለያዩ ጉዳዮች ወደ ኮሌጃችን የሚመጡ ማየት የተሳናቸውን ወገኖች እንዴት መርዳት እንዳለብን እንዲሁም መደረግ ስላለበት ቅደም ተከተል ውይይት ተካሂዷል። አቶ መአዛ ሃይማኖት ወርቁ የህዳሴ አካል ጉዳተኞች ማህበር ስራስኪያጅ አካል ጉዳተኞች ምን ይፈልጋሉ ? በተለይ  ዓይነ ስውራን ምን ይፈልጋሉ ? በሚለው ርዕሰ ጉዳይ ላይ ዘርዘር ያለ መረጃ አስተላልፈው ድጋፋችን በምርጫቸው ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ፣ ሰብአዊ ክብራቸውን የማይነካ፣ ከአድልዎና መገለል የፀዳ፣ ውጤታማ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚያስችልና ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ምክራቸውን ለግሰዋል ።  አካል ጉዳተኞች በሚፈልጉት እና በሚመጥናቸው  ስልጠናዎችን ካገኙ እና ከተደገፉ ማንኛውንም ስራ መስራት የሚችሉ መሆኑን ጠቁመዋል። በተመሳሳይ የድርጅቱ ባልደረባ ወ/ሪት ማርታ ንጉሴ የቱጌዘር ፕሮጀክት አስተባባሪ ስትሆን ድርጅቱ የሚሰጠውን አገልግሎትና ተደራሽነቱን ጠቁመው ሴትነት እና ዓይነ-ስውርነት ያለውን ተደራራቢ ጫና አስመልክተው በቡና ጠጡ ፕሮግራም ማብራሪያ ሰጥተውበታል።  የአይነስውራንን ጫና ለመረዳት የሚያስችል ለ15 ደቂቃ አይንን በመጨፈን እና በመሸፈን ስሜታቸውን ለመዳት የሚያስችል የመማማሪያ መድረክ ተፈጥሯል። በመጨረሻም ከቤቱ ሃሳብ አስተያየት ተነስቶ ውይይት ተካሂዶበታል። ለቀጣይ ከኮሌጁ ጋር በጋራ ቢሰራበት ያሉትንም ጠቁመዋል ።               ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ረቡዕ የካቲት 19/2017ዓ.ም ለኮሌጁ ማህበረሰብ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተዘጋጀ ። በኮሌጁ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የEASE ፕሮጀክት ምንድ ነው ? ለኮሌጁ ያለው ጠቀሜታ ምንድ ነው ?
+8
ዕለተ ረቡዕ የካቲት 19/2017ዓ.ም ለኮሌጁ ማህበረሰብ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተዘጋጀ ። በኮሌጁ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የEASE ፕሮጀክት ምንድ ነው ? ለኮሌጁ ያለው ጠቀሜታ ምንድ ነው ?  በምን በምን ዙሪያ ላይ ይሰራል ? የትኩረት አቅጣጫው ምንድ ነው?  የፕሮጀክቱ የቆይታ ግዜ ምን ያህል ነው ?  በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ላይ  አሠልጣኝ መንክር ግርማ   ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በአጠቃላይ ከቤቱ ሃሳብ አስተያየት ቀርቦ በፕሮጀክት አስተባባሪዎች ምላሽ ተሰጥቷል ። ፕሮጀክቱ በኮሌጁም ሆነ ከኮሌጅ ውጪ የሚሰሩ ስራዎችን፣ ኮሌጁ አሁን ካለበት ደረጃ ተነስቶ በአምስት ዓመታት ውስጥ የሚደርስበትን አቅጣጫ ያስቀመጠ ሲሆን ይህን እውን ለማድረግ ሁሉም የኮሌጁ  ማህበረሰብ እንደየ ዘርፉ የሚፈለግበትን መወጣት እንዳለበት ወይም በየዘርፉ በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅ ተጠቁሟል ። ከቤቱ ሃሳብ አስተያየት ቀርቦ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶበታል ። ከዚህ በመቀጠል በመድረኩ የቀረበው ኮሌጁ የlSO 21001:2018EOMS ትግበራ እና እውቅና ለማግኘት የሚደረገው እንቅስቃሴ ከዳር ለመድረስ በሳምንታት ውስጥ  ምዘናው የሚከናወን በመሆኑ ሁሉም ሃላፊነቱን ለመወጣት መስራት እንዳለበት አቅጣጫ ተሰጥቷል። በመጨረሻም በመድረኩ ማጠቃለያ የሰጡት የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱል በር መሐመድ ፕሮጀክቱ ላይ ግልፀኝነትን ለመፍጠር አልሞ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት አሳስበዋል ።                       ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ረቡዕ የካቲት 19/2017ዓ.ም 4ኛው ዙር የወገኔ የስፖርት ፌስቲቫል ተወዳዳሪዎች በዛሬው ዕለት የመክፈቻ ፕሮግራም ውድድራቸውን አካሄዱ ። ማህበሩ የተቋቋመበትን ዓላማና እያከናወናቸው የመጡ በ
+9
ዕለተ ረቡዕ የካቲት 19/2017ዓ.ም 4ኛው ዙር የወገኔ የስፖርት ፌስቲቫል ተወዳዳሪዎች በዛሬው ዕለት የመክፈቻ ፕሮግራም ውድድራቸውን አካሄዱ ። ማህበሩ የተቋቋመበትን ዓላማና እያከናወናቸው የመጡ በጎ ተግባራትን አጠናክሮ ለመሄድ አልሞ የተዘጋጀው ስፖርታዊ ፌስቲቫል  በመክፈቻ ፕሮግራሙ  ኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፍ እፍ እና አውቶሞቲቭ ስልጠና ዘርፍን ያገናኘ ሆኗል ። የውድድር መርሃ ግብሩን በጋራ ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ እና ም/ዲኖች ሲሆኑ በመክፈቻ ፕሮግራሙ   በኮንስትራክሽን እና በአውቶሞቲቭ ስልጠና ዘርፍን ያገናኘ ሲሆን የኮሌጁ አመራሮች በተገኙበት ውድድሩ ተጀምሯል በውጤቱም ሁለቱ ቡድኖች 3 እኩል በሆነ ውጤት ተጠናቋል ። የፕሮግራሙ አካል የሆነ እና የገንዘብ ማሰባሰቢያ በማህበሩ አባላት የማስቲካ ሽያጭ አከናውነዋል። አስተባባሪው አሠልጣኝ ዮናስ  ዓላማውን እና ማህበሩ እያከናወናቸው የቆዩትን ተግባራት ካጋሩ በኋላ ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ በዚህ የተቀደሰ ተግባር ተሳታፊ  እንዲሆን እና በቀጣይ በሚኖሩ ጨወታወች ላይ በመገኘት ተጋጣሚወችን በማበረታታት ዓላማውን እንዲደግፉና እንዲሳተፉ ጥሪ አስተላልፈዋል።                          ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

ቀናት ወደ መቶኛ  ዓመት....... ⤵️⤵️

ዕለተ ማክሰኞ የካቲት 18/2017ዓ.ም ለአባላት የግንዛቤ መፍጠሪያ ስልጠና ተሰጠ። የእንጦጦ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኮ/የገ/ቁ/ብ/ኃ/የተ/የኅ/ሥራ ማህበር ለአባላቱ በማህበሩ ህግና ደንቦች ዙሪያ የግንዛቤ ማስ
+4
ዕለተ ማክሰኞ የካቲት 18/2017ዓ.ም ለአባላት የግንዛቤ መፍጠሪያ ስልጠና ተሰጠ። የእንጦጦ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኮ/የገ/ቁ/ብ/ኃ/የተ/የኅ/ሥራ ማህበር ለአባላቱ በማህበሩ ህግና ደንቦች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ ። ስልጠናው በማህበሩ ነባርና አዳዲስ ህጎች ላይ ያተኮረ ሲሆን አባላቱ ስለብድርና ቁጠባ ያላቸውን ግንዛቤ እንዲያዳብሩ ታስቦ የተሰጠ ስልጠና ነው ። የማህበሩ ትልቅ አካል ጠቅላላ ጉባኤው ነው ።  ስለዚህ  ውሳኔ ለሚሹ ጉዳዮች አብላጫው ድምፅ የሚፈለግ በመሆኑ አባሉ ስብሰባ በተጠራበት ግዜ ሁሉ መገኘት አለባችሁ የሚል መልእክት ተላልፏል ። በተጨማሪም የአክስዮን ሽያጭ ያልተጠናቀቀ በመሆኑ አክስዮን ያልገዛችሁ አባላት ማህበሩ ቀሪ አክስዮኖችን እንድትገዙ የሚል መልእክት አስተላፏል።                        ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ማክሰኞ የካቲት 18/2017ዓ.ም ለተወዳዳሪ ሠልጣኞች ኦረንቴሽን ተሠጠ። በየዓመቱ ከኮሌጅ እስከ ከተማ ጀረጃ የሚደረግ የክህሎት ውድድር ሲሆን ውድድሩ በአሰልጣኝ፣ በሠልጣኝ እና በኢንተር ፕራይ
+4
ዕለተ ማክሰኞ የካቲት 18/2017ዓ.ም ለተወዳዳሪ ሠልጣኞች ኦረንቴሽን ተሠጠ። በየዓመቱ ከኮሌጅ  እስከ ከተማ ጀረጃ  የሚደረግ  የክህሎት ውድድር ሲሆን ውድድሩ በአሰልጣኝ፣ በሠልጣኝ እና በኢንተር ፕራይዞች መካከል የሚደረግ መሆኑ ታውቋል ። ውድድሩ  በ22 የሙያ ዘርፎች ላይ የሚካሄድ ነው።    የኮሌጃችን ሠልጣኞች በ5 የሙያ ዘርፎች 1. ቴክስታይል ጋርመንት 2. ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎ 3. አውቶ ሞቲቭ 4. ሆቴልና ቱሪዝም 5. ማኑፋክቸሪንግ  ዘርፎች ላይ የሚደረግ ነው። የሠልጣኝ ተወዳዳሪዎች ብዛታቸው 24  ሲሆን  12ሴት እና 12 ወንዶች ናቸው።   መረጃውን ያጋሩን አቶ አብረሃም ገረሙ  የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ባለሙያ ናቸው ። በዛሬው ዕለት የተሠጠው ኦረንቴሽን ለሠልጣኝ ተወዳዳሪዎች ሲሆን ቀጣይ ከከተማው በሚሰጥ አቅጣጫ መሠረት  ለአሠልጣኙ እና ለአንቀሳቃሹ የሚሠጥ ይሆናል ።                     ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017ዓ.ም የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 100ኛ ዓመት ክብረ በዓል በኮሌጅ ደረጃ የመክፈቻ ፕሮግራም ተካሄደ፡፡ የመቶኛ ዓመት ክብረ በዓሉን በመጪው መጋቢት 17 ቀን 20
+9
ዕለተ ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017ዓ.ም የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 100ኛ ዓመት ክብረ በዓል በኮሌጅ ደረጃ የመክፈቻ ፕሮግራም ተካሄደ፡፡ የመቶኛ ዓመት ክብረ በዓሉን በመጪው መጋቢት 17 ቀን 2017ዓ.ም. በድምቀት ማክበር የሚጀምረው የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመክፈቻ ፕሮግራሙ በኮሌጅ ደረጃ በዛሬው ዕለት በተዘጋጀለት የጊዜ ሰሌዳና ክንውን  መሠረት በሙዚቃ ስልጠና ዘርፍ ሠልጣኞች አጃቢነት ተከናውኗል :: የክብረ በዓሉን መክፈቻ ፕሮግራም ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሃመድ እንኳን ለእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 100ኛ ዓመት ክብረ በዓል መክፈቻ ፕሮግራም አደረሰን አደረሳችሁ ካሉ ቦኋላ ‹‹ ያለፈውን ማክበር መጪውን መገንባት ›› በሚል መሪ ቃል በዓሉ እንደሚከበር ገልጸዋል፡፡ አክለውም በዚህ የመቶ ዓመት ጉዞ የአሁኑ ፖሊ ቴከኒክ ኮሌጅ የቀደሞ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንቱታን ያተረፉ ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ፖለቲከኞችና ታዋቂ ግለሰቦችን ወዘተ.  በማፍራት ለሃገራችንም ሆነ ለዓለማችን የማይተካ አስተዋጽኦ ማድረጉን ሲገልጹ የሚሰማቸው ደስታ የላቀ ነው በማለት ይህ አኩሪ ታሪክ ለቀጣይ ስራዎቻችን ስነቅ አድረገን መጠቀም በመጪው ጥረታችን የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ ብንገለገልበት የሚል ምክር ሲያስተላልፉ፤ ባለፈው ታሪካችን በመኩራራት ብቻ ለስንፍና መደበቂያ አድርገን እንዳንጠቀምበት አስምረውበታል፡፡ በቀጣይ ከተለያዩ አካላት ጋር የምናደርገው ፕሮግራም በመኖሩ ጠቁመዋል፡፡ በመጨረሻም እያንዳነዱ የኮሌጁ አባልም ሆነ ባለ ድረሻ አካል ለደማቅ የበዓል አከባበሩ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት አሳስበዋል፡፡                          ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ዓርብ ጥር 23/2017ዓ.ም የኮሌጁ የ90 ቀን ዕቅድ ትግበራ አካል የሆነው ጽዱና ውብ የስራ አካባቢ የመፍጠር የጽዳት ዘመቻ ተካሄደ ። አካባቢን ጽዱ፣ ውብና ማራኪ በማድረግ ምቹ የስራ አካባቢ
+7
ዕለተ ዓርብ ጥር 23/2017ዓ.ም የኮሌጁ የ90 ቀን ዕቅድ ትግበራ አካል የሆነው   ጽዱና ውብ የስራ  አካባቢ የመፍጠር የጽዳት  ዘመቻ ተካሄደ ። አካባቢን ጽዱ፣ ውብና ማራኪ በማድረግ ምቹ የስራ አካባቢ መፍጠር  የኮሌጁ ግንባር ቀደም ተግባር መሆኑ ሰነባብቷል። በመሆኑም በመርሃ ግብር ውስጥ ተካቶና ስራው ተጠናክሮ ከጀመረ ይህ አራተኛ ዙር የጽዳት ዘመቻ ሲሆን የኮሌጁ ማህበረሰብ በጋራ የስራ አካባቢውን የማጽዳት ተግባር አከናውኗል። በኮሌጁ ህንጻ አስተዳደር ጽ/ቤት የሚመራው የጽዳት ዘመቻ የጀመረውን ግለት እንደያዘ እንዲቀጥል እና ምቹ የስራ አካባቢን በመፍጠር በቀጣይ የምናከብረውን የ100ኛ ዓመት በዓል አከባበር እንግዶቻችንን ለመቀበል እና ከሱ ጎን ለጎን የሚሰራው የISO 21001:2018EOMS ትግበራእውቅና የማግኘት መርሃ ግብርን እውን ለማድረግ  የጽዳት ዘመቻው ተጠናክሮ እንዲቀጥል የጽ/ቤቱ ባልደረባ መልእክት አስተላልፈዋል።                                 ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ዓርብ የካቲት 14/2017ዓ.ም ለአሠልጣኞች የተከለሰ የህይወት ክህሎት ስልጠና TOT መስጠት ተጀመረ። በስልጠናው ተሳታፊ የሆኑት የህይወት ክህሎት አሠልጣኞች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። ስልጠ
+9
ዕለተ ዓርብ የካቲት 14/2017ዓ.ም ለአሠልጣኞች የተከለሰ  የህይወት ክህሎት ስልጠና TOT መስጠት ተጀመረ። በስልጠናው ተሳታፊ የሆኑት የህይወት ክህሎት አሠልጣኞች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። ስልጠናው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን ዋና ዓላማው  ወጣቶችን ለስራ ቅጥር ማዘጋጀት መሆኑን አሰልጣኙ አቶ ደሳለኝ ብርሃኑ ገልጸዋል ። " ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ" ስልጠናው በሁለት ዋና ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን ቀድመው ለየብቻ ይሰጥ የነበረው የህይወት ክህሎትና ስራ ማፈላለግ ስልጠና በጣምራ የሚሰጥ ሲሆን 1. የስራ ላይ ደህንነት 2. ፆታን መሠረት ያደረገ ጥቃትን እንዴት መከላከል እንደሚቻል እና ከተከሰተም ምን ማድረግ  እንዳለባቸው  አቅጣጫ ማመላከት ላይ ያተኩራል።  ስልጠናው በቀደሙ ግዚያት ክፍተት አለበት እየተባለ የተገመገመ ሲሆን አሁን ላይ በተከለሰው የስልጠና ስርዓት ምላሽ ያገኛል ተብሎ ይታሰባል ያሉን አስተባባሪው አቶ አለማየሁ ፈንታ ናቸው ።                          ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ዓርብ የካቲት 14/2017ዓ.ም 4ኛው ዙር የወገኔ የስፖርት ፌስቲቫል ለምድብ ድልድል እጣ የማውጣት መርሃ ግብር ተከናወነ። እስፖርት ለወዳጅነት ፣ስፖርት ለጤንነት ከሚለው መርህ ባሻገር ህጻናት
+8
ዕለተ ዓርብ የካቲት 14/2017ዓ.ም 4ኛው ዙር የወገኔ የስፖርት ፌስቲቫል ለምድብ ድልድል እጣ የማውጣት መርሃ ግብር ተከናወነ። እስፖርት ለወዳጅነት ፣ስፖርት ለጤንነት ከሚለው መርህ  ባሻገር ህጻናትን ለመደገፍና ለመርዳት ታሳቢ አድርጎ በ2008ዓ.ም በኮሌጁ ሠራተኞች የተቋቋመው የወገኔ ክበብ  የተቋቋመለትን ዓላማ ያሳካ ዘንድ ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ በዚህ የተቀደሰ ተግባር ላይ ተሳታፊ እንዲሆን ጥሪ አስተላልፈዋል። 4ኛውን ዙር ፌስቲቫል ልዩ የሚያደርገው ኮሌጃችን የ100ኛ ዓመቱን የሚያከብርበት ወራት ላይ መቃረባችን እና በዋናነት ከዚህ  የተያያዘውና ለረጅም ዓመታት በተስፋ የተጠበቀው የኮሌጁ ስያሜ ወደ ቀደመ ስሙ መመለስ ይህን የውድድር ግዜ ልዩ ያደርገዋል ፤ የክበቡ አባላት እና የኮሌጁ ማህበረሰብ የዚህ ታሪክ ተሳታፊ መሆናችን እንኳን ደስያለን በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ። እጣ የማውጣት መርሃ ግብሩን በጋራ ያስጀመሩት የኮሌጁ ም/ዲኖች ሲሆኑ በመክፈቻ ፕሮግራሙ   በኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፍ እና በአውቶሞቲቭ ስልጠና ዘርፍ መካከል ሰኞ የካቲት 17/2017ዓ.ም በደማቅ የማስጀመሪ ስነስርአት የኮሌጁ አመራሮች በተገኙበት የሚጀመር መሆኑን አስተባባሪው አሠልጣኝ ዮናስ ሃ/የሱስ መረጃውን አጋርተውናል ። በዕለቱ የኮሌጁ ማህበረሰብ ፣ሠልጣኞች ተገኝተው ተጋጣሚዎችን እንዲያበረታቱ እና በሚኖሩ የድጋፍ ማሰባሰቢያ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ።                          ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ሐሙስ የካቲት 13/2017ዓ.ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሄደ ። በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ EASE ኮንሰልቴሽን ፕሮግራም ድጋፍ ውጤታማ እንዲሆን የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ( የኢንደስትሪ አድቫይዘር ቦርድ ፣  ከሴቶችና ህጻናት፣ ከሠልጣኞች ወ.ዘ.ተ ) የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሂዷል። በዚህ የግንዛቤ ማዳበሪያ ውይይት የ EASE Consultation Program ዋና ዓላማ፣ ተደራሽ የህብረተሰብ ክፍሎች  እና ትኩረት የተሰጠባቸው ነጥቦች በአጠቃላይ እንደዚሁም በኮሌጅ ደረጃ ደግሞ በፕሮግራሙ ድጋፍ የሚደረግላቸው የስልጠና ዘርፎችን ያካተተ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ። በEASE Consultation Program ድጋፍ የሚደረግላቸው ዋነኞቹ ስራዎች የክህሎት ስልጠና ፣የስራ ዕድል ፈጠራ እና የተደራሾችን ህይወት ማሻሻል የሚል ሲሆን አወያዮቹ በውይይቱ ያነሷቸው ዝርዝር ነጥቦች እንደሚከተለው ተቀምጧል። - የቅሬታ ሰሚ ሃላፊነትና ድርሻ ፣ - የአካባቢ ጥበቃ ፣ - ልዩ ድጋፍ እና ትኩረት የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች (ሴቶች ፣ህጻናት እና የአካል ጉዳተኞች) - የድጋፍ መርሃ ግብሩ የዓለም ባንክ ህግና ደንቦችን ያከበረ ፤ በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ፣በዓለም ባንክ እና በኮሌጁ የስምምነት ነጥቦች የሚመራ እንዲሆን - በማንኛውም ስራ የጥንቃቄ ህጎች ( sefty rules) መከተል አስፈላጊ እንደሆነ እና  - ትኩረት የሚደረግባቸው የስልጠና ዘርፎች የኮሌጁ መለያ የሆኑትንና የልህቀት ማዕከል እንዲሆኑ በሚል እሳቤ ያካተተ ነው ።  የስልጠና ዘርፎቹም ኤስቴቲክስ ፣ ሆቴልና ቱሪዝም፣ ቴክስታይል ጋርመንትና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሆናቸው ታውቋል ። በመጨረሻም ከቤቱ ሃሳብ አስተያየት ተነስቶ የውይይቱ ማጠቃለያ ሆኗል ።                         ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+7

ዕለተ ሐሙስ የካቲት 13/2017ዓ.ም በኮሌጁ ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ላጠናቀቁ ስራ ፈላጊ ወገኖች የማጠቃለያ የcoc ምዘና ኦረንቴሽን ተሰጠ። ከጉለሌ ክፍለ ከተማ የተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወገኖች በመጀ
+5
ዕለተ ሐሙስ የካቲት 13/2017ዓ.ም በኮሌጁ ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ላጠናቀቁ ስራ ፈላጊ ወገኖች  የማጠቃለያ የcoc ምዘና ኦረንቴሽን ተሰጠ። ከጉለሌ ክፍለ ከተማ የተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወገኖች በመጀመሪያ የህይወት ክህሎት ስልጠና እና ሙያዊ ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ከ350 በላይ ሲሆኑ የማጠቃለያ የcoc ምዘናቸውን በአግባቡ ለመውሰድ የሚያስችላቸውን ኦረንቴሽን በምዘና አስተባባሪው አቶ ይሳቅ አበራ ተሰጥቷል። ምዘናው ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ተመዛኞች በተቀመጠላቸው ፕሮግራም ብቻ የሚስተናገዱ መሆኑን አስተባባሪው በአጽንኦት አሳስበው በምዘናው ብቁ ለሆኑት የcoc ምዘና የብቃት ማረጋገጫ እና በኮሌጅ የሚዘጋጀው የልል ክህሎት ስልጠና የምስክር ወረቀት እንደሚወስዱም አሳስበዋል።                               ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ሐሙስ የካቲት 13/2017ዓ.ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሄደ ። በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ EASE ኮንሰልቴሽን ፕሮግራም ድጋፍ ውጤታማ እንዲሆን የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ( የኢንደስትሪ አድቫይዘር ቦርድ ፣  ከሴቶችና ህጻናት፣ ከሠልጣኞች ወ.ዘ.ተ ) የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሂዷል። በዚህ የግንዛቤ ማዳበሪያ ውይይት የ EASE Consultation Program ዋና ዓላማ፣ ተደራሽ የህብረተሰብ ክፍሎች  እና ትኩረት የተሰጠባቸው ነጥቦች በአጠቃላይ እንደዚሁም በኮሌጅ ደረጃ ደግሞ በፕሮግራሙ ድጋፍ የሚደረግላቸው የስልጠና ዘርፎችን ያካተተ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ። በEASE Consultation Program ድጋፍ የሚደረግላቸው ዋነኞቹ ስራዎች የክህሎት ስልጠና ፣የስራ ዕድል ፈጠራ እና የተደራሾችን ህይወት ማሻሻል የሚል ሲሆን አወያዮቹ በውይይቱ ያነሷቸው ዝርዝር ነጥቦች እንደሚከተለው ተቀምጧል። - የቅሬታ ሰሚ ሃላፊነትና ድርሻ ፣ - የአካባቢ ጥበቃ ፣ - ልዩ ድጋፍ እና ትኩረት የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች (ሴቶች ፣ህጻናት እና የአካል ጉዳተኞች) - የድጋፍ መርሃ ግብሩ የዓለም ባንክ ህግና ደንቦችን ያከበረ ፤ በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ፣በዓለም ባንክ እና በኮሌጁ የስምምነት ነጥቦች የሚመራ እንዲሆን - በማንኛውም ስራ የጥንቃቄ ህጎች ( sefty rules) መከተል አስፈላጊ እንደሆነ እና  - ትኩረት የሚደረግባቸው የስልጠና ዘርፎች የኮሌጁ መለያ የሆኑትንና የልህቀት ማዕከል እንዲሆኑ በሚል እሳቤ ያካተተ ነው ።  የስልጠና ዘርፎቹም ኤስቴቲክስ ፣ ሆቴልና ቱሪዝም፣ ቴክስታይል ጋርመንትና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሆናቸው ታውቋል ። በመጨረሻም ከቤቱ ሃሳብ አስተያየት ተነስቶ የውይይቱ ማጠቃለያ ሆኗል ።                         ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ሐሙስ የካቲት 13/2017ዓ.ም በኮሌጁ ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ላጠናቀቁ ስራ ፈላጊ ወገኖች የማጠቃለያ የcoc ምዘና ኦረንቴሽን ተሰጠ። ከጉለሌ ክፍለ ከተማ የተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወገኖች በመጀ
+5
ዕለተ ሐሙስ የካቲት 13/2017ዓ.ም በኮሌጁ ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ላጠናቀቁ ስራ ፈላጊ ወገኖች  የማጠቃለያ የcoc ምዘና ኦረንቴሽን ተሰጠ። ከጉለሌ ክፍለ ከተማ የተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወገኖች በመጀመሪያ የህይወት ክህሎት ስልጠና እና ሙያዊ ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ከ350 በላይ ሲሆኑ የማጠቃለያ የcoc ምዘናቸውን በአግባቡ ለመውሰድ የሚያስችላቸውን ኦረንቴሽን በምዘና አስተባባሪው አቶ ይሳቅ አበራ ተሰጥቷል። ምዘናው ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ተመዛኞች በተቀመጠላቸው ፕሮግራም ብቻ የሚስተናገዱ መሆኑን አስተባባሪው በአጽንኦት አሳስበው በምዘናው ብቁ ለሆኑት የcoc ምዘና የብቃት ማረጋገጫ እና በኮሌጅ የሚዘጋጀው የልል ክህሎት ስልጠና የምስክር ወረቀት እንደሚወስዱም አሳስበዋል።                               ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ የካቲት / 2017ዓ.ም የተቀናጀ ህብራዊ የሙዚቃ ፣ የሥነ-ስዕልና የስነ-ጽሁፍ ምሽት ተዘጋጅቷል። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ የሙዚቃ፣የቲያትርና የሥነ-ስዕል
+9
ዕለተ የካቲት / 2017ዓ.ም የተቀናጀ ህብራዊ የሙዚቃ ፣ የሥነ-ስዕልና              የስነ-ጽሁፍ ምሽት ተዘጋጅቷል። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  በኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ የሙዚቃ፣የቲያትርና የሥነ-ስዕል ትምህርት ክፍል ያዘጋጁት የሙዚቃና የስነ-ጽሁፍ ምሽት  በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10:00 ጀምሮ በትንሹ አዳራሽ ተካሂዷል። ፕሮግራሙን ያዘጋጁት የ3ኛ ዓመት የሙዚቃ ትምህርት ክፍል ሠልጣኞች በፕሮግራሙ መጀመሪያ ይዘውት ከተነሱት ዓላማ የላቀ ደረጃ ላይ መድረሱን እና በሙያቸው መደጋገፍ የሚያስችላቸውን ልምድ የሚያካብቱበት ሲሆን ፕሮግራሙ በየግዜው እያደገና እየተጠናከረ የመጣ መሆኑን  አዘጋጁ ሠልጣኝ አቤሴሎም ብርሃኑ ይገልጻሉ። በፕሮግራሙ ላይ   የክብር እንግዳ አሠልጣኝና ሰዓሊ ሃይሉ ክፍሌ የህይወት ፍልስፍናውን፣ ስራዎቹን እና የተፈሪ መኮንን በሉክሰምበር የተዘጋጀላቸውን የመታሰቢያ ፕሮግራም አስመልክተው ሰፊ ማብራሪያ ሠጥቷል። በመድረኩ የተገኙት የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር ሙሐመድ እና የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት አባላት የእንኳን ደስ ያላችሁ የምስራች አብስረዋል ይህም ኮሌጁ ወደ ጥንተ ስሙ/ተፈራ መኮንን የተቀየረ መሆኑን አብስረው  ሰልጣኞች ከፊታችን ለምናከብረውን የ100 ኛ ዓመት ክብረ በዓል ከእናንተ ከሰልጣኞች ብዙ ነገር ይጠበቃል በማለት ለዚህም ከወዲሁ ጠንከር ያለ ዝግጅት ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውና  ከአሠልጣኞቻቸው ጋር በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል ።                                      ኮሙኒኬሽን ቡድን