1 146
Suscriptores
Sin datos24 horas
-37 días
-1830 días
Archivo de publicaciones
1 146
የአካል ጉዳተኝነትን አስመልክቶ የግንዛቤ መፍጠሪያ
መድረክ ተካሄደ።
ቱጌዘር በተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ዓይነ- ስውርነትን አስመልክቶ ያለውን የተሳሳተ አመለካከት ለማስተካከልና ዓይነ ስውራንን ለመርዳት /ለማገዝ እንዲሁም መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና በተለያዩ ጉዳዮች ወደ ኮሌጃችን የሚመጡ ማየት የተሳናቸውን ወገኖች እንዴት መርዳት እንዳለብን እንዲሁም መደረግ ስላለበት ቅደም ተከተል ውይይት ተካሂዷል።
አቶ መአዛ ሃይማኖት ወርቁ የህዳሴ አካል ጉዳተኞች ማህበር ሊቀመንበር ዓይነ ስውራን በሚፈልጉት እና በሚመጥናቸው ስልጠናዎችን ካገኙ እና ከተደገፉ ማንኛውንም ስራ መስራት የሚችሉ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተመሳሳይ የድርጅቱ ባልደረባ ወ/ሮ ማርታ ድርጅቱ የሚሰጠውን አገልግሎትና ተደራሽነቱን ጠቁመው ሴትነት እና ዓይነ-ስውርነት ያለውን ተደራራቢ ጫና አስመልክተው በቡና ጠጡ ፕሮግራም ማብራሪያ ሰጥተውበታል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+6
ዕለተ ማክሰኞ ሐምሌ 2/2016ዓ.ም
በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ ለሰለጠኑ ሰልጣኞች በከተማ ደረጃ የተዘጋጀ ምዘና ተጀመረ ።
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ ሠልጥነው የተቋም ምዘና የተመዘኑ የማርኬቲንግ እና የሴክሬተሪ ሙያ እጩ ተመራቂ ሰልጣኞች በከተማ ደረጃ የተዘጋጀውን ሞዴል ምዘና ከሐምሌ 2/2016 - ሐምሌ 4/2016ዓ.ም እንደሚቆይ የገለጹት የምዘና አስተባባሪው አቶ ይሳቅ አበራ ምዘናው በጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር የሚመራ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ተመዛኞች በጠዋቱ ክፍለ ግዜ የቲዎሪ /ለጽሁፍ ፈተና የተቀመጡ ሲሆን በሁለተኛው መርሃ ግብር የተግባር ፈተናውን እየተመዘኑ መሆናቸው ተገልጿል።
የዝግጅት ክፍላችንም ለተመዛኞች መልካም ዕድልን እንመኞለን ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ሰኞ ሰኔ1/2016ዓ.ም
ለመዛኞች እና ሱፐር ቫይዘሮች ኦሬንቴሽን ተሠጠ።
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ ስልጠናቸውን ለጀመሩ ሰልጣኞች በከተማ ደረጃ የተዘጋጀውን ሞዴል ምዘና ለመስጠት ያስችል ዘንድ የተመረጡት አሠልጣኞችና ሱፐርቫይዘሮች በአዲሱ ፖሊሲ ተመዝነው ብቃታቸውን ያረጋገጡ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፤ በዛሬው ዕለትም ልዩ ኦሬንቴሽን በኮሌጁ ሥ/አካ/ጉ/ም/ዲን እና በምዘና ፎካል ፐርሰን ኦረንቴሽኑ ተሰቷል።
በ2016 ዓ.ም ከሚመረቁ የአዲሱ ፖሊሲ ሠልጣኞች ስልጠናቸውን ያጠናቀቁና የተቋም ምዘና የተመዘኑ የማርኬቲንግ እና የሴክሬተሪ ሙያ እጩ ተመራቂ ሰልጣኞች በከተማ ደረጃ የተዘጋጀውን ሞዴል ምዘና በግንባር ቀደምትነት ማክሰኞ ሀምሌ 2/2016 ዓ.ም እንደሚጀምሩ ተጠቁሟል።
በመቀጠል ም/ዲኑ እጩ ተመራቂ ሰልጣኞች ጊዚያቸው ሳይባክን የተዘጋጀውን የመጀመሪያ ሞዴል ምዘና ለሚያስመዝኑ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪ እና አሰልጣኞች እንዲሁም በቅርቡ ለማስመዘን ዕቅድ ለያዙ በሙሉ በኮሌጁ ስም ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቀርበዋል።
በመጨረሻም ለተመራቂ ሰልጣኞች መልካም ዕድል እንዲገጥማቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የጥሬ ገንዘብ እና ንብረት ቆጠራን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ.ም
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የዉስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት በየአመቱ በሚያዘጋጀዉ የጥሬ ገንዘብ እና ንብረት ቆጠራ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በዛሬዉ እለት ስራቸዉ ከንብረት እና ገንዘብ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ላላቸዉ ለኮሌጁ የንብረት ቆጠራ ኮሚቴዎች ፣ ፋይናንስ ፣ ግዥ እና ንብረት አስቆጣሪ ክፍሎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል።
በስልጠናዉ ላይ ስለ ንብረት እና ሰነድ አያያዝ፣ አቆጣጠር ፣ አመዘጋገብ እና ሪፖርት ግንዛቤ ተፈጥሯል። ንብረት በትክክለኛው የመቁጠሪያ መለኪያ (መመዘኛ) በትከክል መቁጠር እንደሚገባ፣ የንብረት ክምችት ሁኔታን መለየት ፣ ሰነዶች ላይ በቆጠራ የተደረሰበት ረፖርት በፊርማ ማጋገጥ ፣ እና ወቅታዊ ሪፖርት ማድረግ እንደሚገባ በስልጠናዉ ላይ ተገልጿል።
ተሳታፊዎቹ ስልጠናዉ ግንዛቤያቸውን እንዳዳበረላቸዉ ገልጸዉ ነገር ግን የንበረት ክምችት መብዛት ፣ የጥቅማጥቅሞች (የደንብ ልብስ እና የንጽህና መጠበቂያ ግብአቶች ) አለመሟላት ፣ ግዥ ያልተፈጸመባቸዉ ግበአቶች መኖራቸዉ እንደ ሳንካ ጠቅሰዋል።
የኮሌጁ ኮሙኒኬሽን ቡድን
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
