1 146
Suscriptores
-224 horas
-47 días
-1930 días
Archivo de publicaciones
1 146
+7
ዕለተ ሐሙስ መጋቢት 18/2017 ዓ.ም
የብረታ ብረትና እንጨት ስራ ስልጠና ዘርፍ በትምህርት ክፍሉ የተዘጋጀውን የተቋም ውስጥ ምዘና አስመዘነ ።
በተፈፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የብረታ ብረትና እንጨት ስራ ስልጠና ዘርፍ በ2016ዓ.ም የደረጃ 4 ሜካኒክስ ሰልጣኞች ከደረጃ 2 ወደ ደረጃ 3 የሚሸጋገሩ 14 ሠልጣኞች ሲሆኑ 12ቱ የተመዘኑ ሲሆን 12 ቱም ማለትም 100% ውጤታማ በመሆን ወደ ቀጣዩ ደረጃ ተሸጋግረዋል።
ምዘናው ሠልጣኞች ወደ ቀጣዩ ደረጃ ሲሸጋገሩ በራስ መተማመናቸው እንዲጨምር የሚያግዛቸው መሆኑን የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዋ ወ/ሮ እታገኝ ውብሸት ገልፀዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም
15ኛውን የቴ/ሙ ሳምንት አስመልክቶ ተግባራዊ የጥናት እና ምርም ውድድር በኮሌጅ ደረጃ ተካሄደ።
''ብሩህ አዕምሮ ፣ በክህሎት የበቁ ዜጎች'' በሚል መሪ ቃል ለ15ኛው ቴክናኒክና ሙያ ሳምንት የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ተካሄደ። የኮሌጁ የጥናትና ምርምር የስራ ክፍል በ2ኛዉ ሩብ አመት የሰጠውን ስልጠና ተከትሎ ፕሮፖዛላቸውን አቅርበው ተቀባይነት ያገኙ የኮሌጃችን አሰልጣኞች የተግባራዊ ጥናትና ምርምራቸውን የመጨረሻ ውጤት በዛሬው ዕለት አቅርበዋል።
በዕለቱ 5 ተግባራዊ ጥናትና ምርመሮች የቀረቡ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 2 ጥናቶች ከአውቶ መካኒክ ት/ክፍል፣ ከሆቴል እና ቱሪዝም ፣ ከኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ እና ከከተማ ግብርና ት/ክፍል እንደቀረቡ ለማወቅ ተችሏል።
በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ት /ክፍል የአሰልጣኞችን ውጤታማነት ማሻሻል ፣ በሆቴል እና ቱሪዝም ት/ክፍል የግቢውን የካፌ መስተንግዶ አገልግሎት ማሻሻል ፣ በአውቶ መካኒክ ት/ክፍል የደረጃ 4 ሰልጣኞች ከትምህርት ገበታ ማቋረጥ (dropout) እና የደረጃ 3 ተማሪዎችን አቅም ማሻሻል ፣ በከተማ ግብርና ት /ክፍል ደግሞ በተሻለ አመጋገብ የደሮ እርባታ ምርትን መጨመር በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ጥናቶች እንደቀረቡ የኮሌጁ የጥናትና ምርምር የስራ ክፍል አስተባባሪ ሰላማዊት ይርጋ ለክፍላችን ገልጸዋል።
የተግባራዊ ጥናቱ ዓላማ የራስ ችግርን በራስ አቅም መፍታት እንደሆነ ጠቅሰው ፣ ችግር የመፍታት ሂደቱ የተጋነነ የፋይናንስ እና የቁሳቁስ ወጭ እንደማይጠይቅም አስረድተዋል።
የጥናትና ምርምር የስራ ክፍል አስተባባሪዋ እንዳሉት በጥናትና ምርምር ውድድሩ አንደኛ የወጣው አጥኝ እና ተማራማሪ በክላስተር ደረጃ ለሚደረገው የጥናትና ምርምር ውድድር ኮሌጁን በመወከል ይቀርባል ብለዋል።
በዕለቱ የኮሌጁ አካዳሚክ ማኔጅመንት አባላት እንዲሁም ከስራና ክህሎት ቢሮ ታዛቢ የተገኘ ሲሆን በውድድሩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ እና አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ደግሞ የጥናትና ምርምር ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው በጥናቱ ለተሳተፉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል ። በተመሳሳይ የኮሌጁ ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ምክትል ዲን መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኮሌጃችን አሰልጣኞች በተግባራዊ ጥናትና ምርምር በመሳተፍ ችግርን በራስ አቅም የመፍታት ሂደት እንዲያጎለብቱ እንደዚሁም ማንኛዉንም ቴክኒካዊ ድጋፍ የኮሌጁ የጥናትና ምርምር የስራ ክፍል እንደሚያደርግ አስተባባሪዋ ሰላማዊት ይርጋ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+4
ዕለተ ሐሙስ መጋቢት 2017ዓ.ም
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር በሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፍ ለሚሠለጥኑ ሰልጣኞች ኦረንቴሽን ተሰጠ።
በመክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ሰልጣኞቹን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት አስተላልፈው ይህ አንጋፋ ኮሌጅ በመደበኛም ሆነ በአጫጭር ስልጠና ሠልጣኞችን ተቀብሎ የሚያሰለጥን መሆኑን ጠቅሰው ሰልጣኞች ለስልጠና ሲመጡ መከተል ስላለባቸው መመሪያና ደንብ ገለጻ አጽርገዋል ።
ስልጠናው ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር በሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፍ በሆቴል ማኔጅመንት፣ በምግብ ዝግጅት እና በመስተንግዶ ዘርፎች ላይ ለተሰማሩ ዜጎች የስራላይ ስልጠና /Refreshment ስልጠና እንደሆነ አብራርተዋል ። በተመሳሳይ የስልጠና ዘርፉ አስተባባሪ አቶ ጅብሪል የስልጠና ቆይታው እንደየ ዘርፉ የሚለያይ መሆኑን እና ሰልጣኞች በሚቀመጥላቸው ፕሮግራም ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ለ COC ምዘና ተመዝነውና ብቃታቸውን አረጋግጠው እንደሚወጡ ለዛም መዘጋጀት እንደሚጠበቅባቸው መልእክት አስተላልፈዋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 146
+5
መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም
የተማሪዎች ስፖርት ክበብ ተቋቋመ።
በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የተማሪዎች ስፖርት ክበብ ተቋቋመ ። ክበቡ በአሁኑ ሰዓት ከ60 በላይ አባላቶች ያሉት ሲሆን ማንኛውም ፍላጎት ያለዉ የኮሌጁ ተማሪ አባል መሆን እንደሚችል የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ናሆም ግሩም ለክፍላችን ተናግሯል ።
የተማሪዎች ስፖርት ክበብ ንቁ ፣ ጤናማ እና በስፖርት ዲሲፕሊን የተገነባ ዜጋን ለመፍጠር እንዲሁም በተማሪዎች መካከል መተዋወቅ እና ሕብረት ለመፍጠር አስፈላጊ መሆኑን የኮሌጁ የስልጠና እና አካዳሚክ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የተናገሩ ሲሆን ይህን የተማሪዎች የስፖርት ክበብ ኮሌጁ አቅሙ በፈቀደዉ መጠን ሁሉ እንደሚደግፉ ገልጸዋል።
ክበቡ በቀጣይ በዲፓርትመንቶች መካከል ውድድር ለማዘጋጀት ዕቅድ እንዳለው ገልጾ በውድድሩም ኮሌጁን የሚወክሉ ተማሪዎችን በመመልመል የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የተማሪዎች የእግር ኳስ ቡድን እንደሚመሰረት ታዉቋል። በተያያዘም የተማሪዎች ስፖርት ክበብ የሴት ተማሪዎች የመረብ ኳስ ቡድን ለመመስረት እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል።
ሁሉም የኮሌጃችን ት/ክፍል ተጠሪዎች እና አሰልጣኞች ሰልጣኞቻቸውን የተማሪዎች ስፖርት ክበብ አባል እንዲሆኑ እንዲያበረታቱ ፣ ንቁና ጤናማ ዜጋን የመፍጠር ሂደትን እንዲቀላቀሉ እንዲሁም ኮሌጁን የሚወክሉ የተማሪዎች የስፖርት ቡድን መቋቋም እንዲደግፉ የኮሌጁ የስልጠና እና አካዳሚክ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ናሆም ተናግረዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 16 /2017 ዓም
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሁለት መንግስታዊ ተቋማት ለመልካም አገልግሎቱ የዕውቅና የምስክር ወረቀቶች ተሰጠው።
የመጀመሪያውን የዕዉቅና የምስክር ወረቀት ያገኘዉ ከሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የመሀንዲስ መምሪያ ሲሆን ኰሌጁ በሰርቬይንግ ስልጠና ዘርፍ ለ11 የመምሪያው አባላት ለ20 ቀናት ሲሰጥ የቆየውን ሥልጠና መጠናቀቁን ተከትሎ ነው ። የመሃንዲስ መምሪያው ለኰሌጁ፣ለስልጠና ዘርፉ እና ለአሠልጣኞቹ የዕውቅና የምስክር ወረቀት አበርክቷል። በተመሳሳይ ስልጠናቸውን በአግባቡ ላጠናቀቁ ሠልጣኞች የሥልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የስልጠና ማጠናቀቂያ የምስክር ወረቀት ሰጥተዋቸዋል። ከሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ሌ/ጀነራል ደስታ አብቾ እና አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ንግግር መረዳት እንደሚቻለው የተቋማቱ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ፍላጎት መኖሩን የሚያመላክት ነው።
ኰሌጃችን ሁለተኛውን የምሥክር ወረቀት ያገኘው ደግሞ ከጉለሌ ክፍለ ከተማ የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ሲሆን የበጀት ዓመቱ መንፈቅ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ መሠረት በማድረግ ነው። ጽ/ቤቱ እንደገለፀው የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባለፉት 6 ወራት ለበርካታ ወጣት ሴቶች እና ወንዶች ክህሎት መር አጫጭር ሥልጠና በመስጠት ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ላበረከተው የላቀ አስተዋጽኦ የዕውቅና የምሥክር ወረቀት ተሰጥቷል።
እንደ ሀገራችን አባባል " ያዘጋጀውን ምግብ ተጋባዦች ሲበሉለት፤የወለደውን ልጅ ሲስሙለት" ደስ ይላል። ኮሌጁ ላበረከተው አስተዋጽኦ ምስጋና መቸሩና የዕውቅና የምስክር ወረቀት በማግኘቱ እንኳን ደስ ያለን የዝግጅት ክፍላችን መልእክት ሆኖ የበለጠ ለማገልገል እውቅና ማግኘቱ በስንቅነት እንደሚያገለግል እናምናለን።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
መጋቢት 16 ቀን 2017 ዓ.ም
የኤች አይ ቪ ፣ የጡት እና የማህፀን በር ካንሰርን
በተመለከተ የግንዛቤ መስጫ መድረክ ተካሄደ።
የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮ የኤች አይ ቪ ሜን ስትሪሚንግ ክበብ ከማቲወስ ወንዱ ኢትዮጵያ የካንሰር ሶሳይቲ ጋር በመተባበር የኤች አይ ቪ ፣ የጡት እና የማህጸን በር ካንሰርን ለመከላከልና ችግሩ ተከስቶ ሲገኝ መደረግ ባለባቸው ጉዳዮች ላይ የግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሄደ።
ግንዛቤዉን የፈጠሩት ዶ/ር ቬሮኒካ ዝናቡ ከማቲወስ ወንዱ ኢትዮጵያ የካንሰር ሶሳይቲ እንዳሉት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የጡትና የመሃፀን ጫፍ ካንሰር ለመከላከል ዋነኛው መፍትሄ በአቅራቢያ ወደሚገኙ ጤና ተቋማት በመሄድ ምርመራ ማድረግ ሲሆን ከዚህ ባሻገር በተለይ የጡት ካንሰርን ለማወቅ በቤት ውስጥ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም እራስን መቃኘትና ጥርጣሬዎች ሲኖሩ ወደ ጤና ተቋማት መሄድ ይገባል ብለዋል።
በዓለማችን በየዓመቱ 2.3 ሚሊዮን ሰዎች በጡት ካንስር በሽታ ሲጠቁ 666,103 ሴቶች ደግሞ ህይወታቸውን ያጣሉ። በሀገራችን ደግሞ በየዓመቱ 16,904 ሴቶች በጡት ካንሰር ሲያዙ 9,626 የሚሆኑ ስዎች ደግሞ ህይወታቸውን እንደሚያጡ የዓለም አቀፍ የጤና ድርጅት (WHO) የ2022 ሪፖርት ያመለክታል። የጡት የካንሰር ሴቶችን በመግደል ቅድሜያውን የሚወስድ የካንሰር በሽታ ዓይነት መሆኑን ከጤና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
በግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኩ ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎች ተነስተው ምላሽ የተሰጠባቸዉ ሲሆን የጡት ካንሰርንም ሆነ የመሃፀን ጫፍ ካንሰርን ቶሎ በመታከም ከበሽታው መዳን እንደሚቻል ገልጸው በመርሃ-ግብሩ የታደሙ ሴቶች ከራሳቸው አልፈው በአከባቢያቸውና በሥራ ቦታቸው ለሚገኙ ሴት እህቶቻቸው ግንዛቤን የመፍጠር ሥራ ሊሠሩ እንደሚገባ ዶ/ር ቬሮኒካ ዝናቡ በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ አሳስበዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዜና : እረፍት ።
……,,,,,………..
የኮሌጃችን : የስራ : ባልደረባ : የሆነችው : መታሰቢያ : ኪዳነወልድ : ባደረባት : ህመም : በህክምና : ስትረዳ : ቆይታ : ቅዳሜ : መጋቢት : 13 , 2017 ዓ.ም. አርፋለች ።
የቀብሯ : ሥነ- ሥርዓት : ነገ : እሁድ : ከ6 : 30 : እስከ 7 : 00 ሰዓት : ሳሪስ : ዮሴፍ : ቤተክርስትያን : ይከናወናል ።
ነፍስ : ይማር ።
1 146
+5
ዕለተ ሐሙስ መጋቢት 11/2017 ዓ.ም
የሰው ኃይል ስምሪት ምጥጥንን አስመልክቶ
ውይይት ተካሄደ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዛሬው ዕለት የተካሄደው የግንዛቤ መፍጠሪያ ጭብጡ የሰው ኃይል ስምሪቱን ማመጣጠን እንደሆነ የሰው ኃይል አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ተጠሪዋ ገልጸዋል ።
በግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኩ ላይ እንደተገለጸው ምጥጥኑ 40/60 በሚል ስልት ይካሄዳል ፤ ስልቱ በዳይሬክቶሬት ወይም በቡድን ስር ባለው የሰው ኃይል ሲከናወን የቆየውን ስራ በተመረጠ 60% የሰው ሃይል ብቻ እንዲከናወን ማድረግ እንደሆነ እና 40% ደግሞ በተመሳሳይና በሚመጥነው ሌላ የስራ መደብ ተወዳድሮ እንዲሸጋሸግ የሚደረግ ሲሆን ካልተቻለ ለአዲስ አበባ ሲቪል ሰርቪስ የሚተላለፍ ይሆናል ። በዚህ የአሰራር ስልት የሚዳሰሱት የአስተዳደር ሰራተኞችና የስራ መደቦች በከፊል ሲሆኑ በኃላፊነት ደረጃ ያሉት ዳይሬክቶሬቶች እና ቡድን መሪዎች እንደማይካተቱ ከተሰጠው ማብራሪያ ለመገንዘብ ተችሏል። ይህ የትግበራ ስልት በኮሌጃችን ብቻ ሳይሆን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጀት የሚተዳደሩ መስሪያ ቤቶችም እንደሚፈጸም ለማወቅ ተችሏል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 9/2017ዓ.ም
በመግባቢያ ሰነድ ፊርማ የታጀበ የምክክር ስብሰባ ተካሄደ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በጉለሌ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ስር የሚገኙ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በጋራ የመስራት ዕቅድ ላይ ግንዛቤን በመፍጠር አቅጣጫን የማኖር የምክክር ስብሰባ በኮሌጁ አዳራሽ ተካሂዶ በመግባቢያ ሰነድ ፊርማ ተቋጭቷል ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ አብዱል በር መሐመድ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ። ንግግራቸውን በመቀጠል በትምህርትና ስልጠና ላይ የጋራ አጀንዳ ያላቸው መንግስታዊ ተቋማት ተመካክረውና ተደጋግፈፈው መስራታቸው በአጠቃላይ ለትምህርትና ስልጠና ዓላማ መሳካት የሚኖረው አስተዋጽኦ ትርጉም ያለው እንዲሆን ከማስቻሉም ባሻገር የሃገርን ሃብት በተገቢው መልኩ ለመጠቀም የሚኖረው ድርሻ ቀላል የሚባል አይደለም ብለዋል። የኮሌጁ ዲን ኮለጃቸው አቅም በፈቀደ ሁሉ ድጋፍ እንደሚሰጥ ጠቁመው ፕሮግራሙን ለሚያቀርቡት የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬን ጋብዘዋል ።
የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲኑ የTVT መሠረታዊ ጉዳዮች ብቁና ተወዳዳሪ ሠልጣኝ ማፍራትና ተወዳዳሪ ኢንተርፕራይዞችን ማፍራት ላይ አተኩሮ የሚሰራ ነው ብለዋል ። በመቀጠል የቴክኒክና ሙያ አዲሱ እሳቤ ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተውበታል።
ተሳታፊዎቹም በርእሰ ጉዳዩ ላይ በተሰጠው ማብራሪያና ባደረጉት ምክክር በቂ የሚባል ግንዛቤ ስለ TVT ማግኘታቸውን በመግለጽ የበለጠ ሰፍቶ ወደ ተግባር ለመቀየር ከፍተኛ ፍላጎት በማሳየት በትብብር ስምምነቱ ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት መምህራንን ጨምሮ ግንዛቤ እንዲያገኙና በጋራ የሚሰሩ ዝርዝር ተግባራት በስምምነቱ ውስጥ እንዲካተቱ የበኩላቸውን ሃሳብ ሰንዝረዋል ።
በመቀጠልም የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱል በር መሐመድ በቀረቡ ሐሳብ አስተያየቶች ላይ ማብራሪያ ከሠጡ በኋላ ትምህርት ቤቶቹ እና ኮሌጁ የጋራ ስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል ።
በተጨማሪም ኮሌጁ ካለው ሪሶርስ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መሠጠት ለጀመሩት የሙያ መስኮች ለማጣቀሻ አገልግሎት የሚውሉ መጻህፍትንና የጽህፈት መሳሪያዎችን በስጦታ አበርክተውላቸዋል ።
በመጨረሻም ተሳታፊዎች በኮሌጁ የትኩረት አቅጣጫ የተመረጡ ስልጠና ዘርፎች ላይ ጉብኝት አካሂደዋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
Surprise🎉🎉🎉🎉🎉🎉
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የመጀመሪያው የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሴት ሰራተኞች የእግር ኳስ ጨዋታ😲😲😲😲
አሰልጣኞች ከ አስተዳደር ሰራተኞች
ቀን ፡ መጋቢት 25
ሰዓት : 6:00
ስለ ወገኔ ስፖርት ፌስቲቫል
⚽️የጨዋታ ፕሮግራሞች፣ ውጤቶች፣ የደረጃ ሰንጠረዥ፣ የበጎ አድራጎት ስራዎች ...
እና ሌሎች ማንኛውንም መረጃ ከፈለጉ የወገኔን የቴሌግራም ግሩፕ ይቀላቀሉ
https://t.me/Wegeneintms
🤝 ኑ የግሩፓችን ቤተሰብ ይሁኑ
እኛም በአቅማችን ለወገናችን!!!
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
