1 148
Suscriptores
-124 horas
-27 días
-1830 días
Archivo de publicaciones
1 148
ነሐሴ19/2017 ዓ/ም
ወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ ፕሮግራም በኮሌጅ ዲን አቶ አብድልበር መሀመድ የተከፈተ ሲሆን አቶ ነገሰ ተፈረደኝ መጠነ ሰፊ የስራ ልምዳቸውን "የተግባር ሰው" በሚል መሪ ቃል ለኮሌጅ ሰራተኞች አካፍለዋል። የኮሌጅ ማህበረሰብ በልብ ቅንነት የሚጠበቅባቸውን እንዲሰሩ ምክር አዘል መልክታቸውን አስተላልፈዋል ።
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 148
ሰኞ ነሐሴ 12/2017 ዓ.ም
የመጀመሪያው "ወርቃማ ሰኞ "በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፤
በሳምንቱ መጨረሻ ያሉትን ሁለት የእረፍት ቀናት ተከትሎ የሚመጣው የሳምንቱ የስራ መጀመሪያ ቀን ሰኞ ንቁና ደስተኛ ሆነን ስራችንን ስንጀምር ውጤታማ ስራ እንድንሰራ ከማገዙም በላይ ለሚቀጥሉት የስራ ቀናት ግብአት ሆኖ የተሟላ ዝግጅት እንድናደርግ ስለመርዳቱ የሚያጠራጥር አይሆንም በዚህ መንፈስ ስራችንን ስናከናውን ለሰኞ ቀን ያለን አመለካከት ወይም ሰኞ ለሌሎች የስራ ቀናት ያለው አስተዋጽኦን እውቅና ለመስጠት ወርቃማ ተብሎ ቢሰየም ተገቢነት አለው ማለት ይቻላል።
ሰኞ ከአሉታዊ እሳቤ /አመለካከት ተላቆ የስራ ቀናት አውራ ሆኖ እሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ለሌሎች የስራ ቀናት እንዲያበረክት መንግስት ወርቃማ ሰኞ የመጀመሪያ የስራ ሰዓት ምክክር የሚደረግበት፣ ልምድና መረጃ የሚጋራበት እንዲሆን ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በዛሬው ዕለት አቶ ሚካኤል ጎኣ የ ISO አስተባባሪ ልምዳቸውን በማጋራት አሃዱ ብለው ስለጀመሩት ፋና ወጊ ሆነው በኮሌጁ ታሪክ ተመዝግበዋል ።
ይህ የወርቃማ ሰኞ ጅምር ወደ ባህልነት እስኪያድ ቀጣይነት ባለው መልኩ እንደሚተገበር በመግቢያ ስነ ስርዓት ላይ ክቡር አቶ አብዱልበር መሐመድ ተናግረውታል ።
ኮሌጃችን ወርቃማ ሰኞን ያደመቀበት ሁለተኛው አንኳር ስራ ለ2018በጀት ዓመት የተዘጋጀው ረቂቅ የዕቅድ ሰነድ ለውይይት የቀረበበት አጋጣሚ ነበር ። ረቂቅ ሰነዱ በሁለት ዋነኛ ምሰሶዎች ( ቁልፍ ተግባራትና ዓበይት ተግባራት 6 ግቦች ፣ 24ዓማዎቾ እና 97 ተግባራት ተሸንሽኖ የቀረበ ነበር ። በተጨማሪም የዕቅድ መነሻ ሃሳብ አስፈላጊነት ፣መልካም አጋጣሚና ስጋቶች ፣ የክትትልና ድጋፍ አግባብ ወ.ዘ.ተ ያካተተ ነበር ። የሰነዱ አቅራቢ ወ/ሮ ንግስት ገ/ህይወት ሰነዱን ካጠናቀቁ በኋላ የተከተለውን ውይይት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መርተውታል።
ውይይቱ በአወንታም በአሉታም የተነሱ ሐሳቦች ተስተናግደውበታል።
በመጨረሻም ዲኑ መካተት ያለባቸው ሃሳቦች እንደሚካተቱ ከላይ ወደ ታች በመመሪያ የተወሰዱት እንዳለ እንደሚቀጥሉ ገልፀው ስብሰባው ተጠናቋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
+9
ነሐሴ 6/2017ዓ.ም
የኮሌጁ ሦስት ዘርፎች በስራቸው ካሉ ዳይሬክቶሬቶች፣ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች እና አስተባባሪዎች ጋር
የ2017/18 በጀት ዓመት ዕቅድ እና ትግበራ ላይ ያተኮረ የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ ።
በኮሌጁ የተቋማት አቅም ግንባታ ፣ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን እንዲሁም የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን ከዳይሬክቶሬቶች፣ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች እና አስተባባሪዎች ጋር በበጀት ዓመቱ አቅዶ የሚያከናውኗቸውን ተግባራት በግዜና በመጠን ያካተተ ሲሆን ሥራዎችን ቆጥሮ መስጠትና ቆጥሮ መቀበል በሚያስችል አገባብ የተቀመጡ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።
በተመሳሳይ እያንዳንዱ ተፈራራሚ በስሩ ከሚገኙት የሴክሽን ተጠሪዎች፣ ቡድን መሪዎች እና በተዋረድ ከፈጻሚዎች ጋር በመፈራረም ወደ ስራ እንደሚገባ ለመረዳት ተችሏል።
1 148
ነሐሴ5/2017ዓ.ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባለሙያዎች ቅንጅት ተሰርቶ ለሽያጭ የበቃ የቴክኖሎጂ ውጤት
በኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ፣ የGMF እና የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ አሠልጣኞች ቅንጅት ለምርት አገልግሎት የበቃው የወተት ማርጊያ የቴክኖሎጂ ውጤት በብር 37,600 ብር ሽያጭ ለወተት እና የወተት ተዋጽኦ አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ ዶ/ር መላኩ እና ጓደኞቻቸው የከብት እርባታ ማህበር ተላልፏል።
በኮሌጁ ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍና ክትትል ከሚደረግላቸው ኢንተር ፕራይዞች አንዱ ዶ/ር መላኩ እና ጓደኞቻቸው የከብት እርባታ ማህበር የወተት ምርቱን በማርጋት ለገበያ ለማቅረብ ከ3-4 ቀናት የሚፈልግ በመሆኑ ምርቱን በሚፈለገው ልክ እና ጥራት ለማቅረብ የሚቸገሩ መሆናቸውን በድጋፍ ወቅት በባለሙያዎች ክትትል ተለይቷል ። ይህንን ተግዳሮት ለመቅረፍ ሂደቱን ማሳጠር የሚቻልበት መንገድ ካለ ኢንተር ፕራይዙ ድጋፍ እንዲደረግለት ባቀረበው ጥያቄ መሠረት የኮሌጁ ከተማ ግብርና ስልጠና ዘርፍ አሠልጣኝ አቶ በፍቃዱ ባህሩ ወተቱን በአጭር ግዜ ማርጋት የሚያስችል ቴክኖሎጂ ከውጭ የሚገባው ከ80 ሺህ ብር በላይ መሆኑን ጠቅሰው ወጪውን በመቀነስ ይህንን ሊተካ የሚችል የወተት ማርጊያመስራት እንደሚቻል ገልፀዋል። የኮሌጁ ሜካኒካል እና ኤሌክትሪካል ባለሙያዎች ተቀናጅተው በራሳቸው ዲዛይን እና ከአካባቢው በሚገኝ ማቴሪያል መሳሪያውን መስራታቸውን አሠልጣኝ ልደቱ ያዩ መረጃውን አጋርተውናል ።
ከተለያዩ ሙከራዎች በኋላም ውጤታማነቱን አረጋግጠዋል ። በመቀጠልም ለጥያቄ አቅራቢው ኢንተር ፕራይዝ መገልገያ መሳሪያውን አስተላልፈዋል፤ የኢንተርፕራይዙ ባለቤት እንደሚሉት ከዚህ ቀደም ከ3-4 ቀናት የሚፈጀውን የማርጋት ሂደት በተሰራልኝ ቴክኖሎጂ ከ6-12 ሰዓታት ውስጥ የማርጋት ሂደቱ ለማከናወን አስችሎኛል። በምርቱ ደስተኛ ነኝ በግዢ ወስጄ እየተገለገልኩበት እገኛለሁኝ ብለዋል ።
እኛም እንደዚህ አይነት ችግር ፈቺ፣ ወጪና ግዜን የሚቆጥቡ መሳሪያዎችን በመቅዳት በቀጥታ ወደ ስራ የሚያስገባ አሰራር መበረታታት አለበት ስንል ይህ ተምሳሌታዊ ስራ ሌሎችም ዘርፎች እንደሚከተሉት እምነታችን የጸና ነው ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
+8
ነሐሴ 5/2017ዓ.ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች የ2017/18 በጀት ዓመት ዕቅድ እና ትግበራ ላይ ያተኮረ የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ ።
የኮሌጁ ኮር አመራሮች ከዋና ዲኑ አቶ አብዱልበር መሐመድ ጋር የተፈራረሙት የስምምነት ሰነድ ያካተተው በበጀት ዓመቱ ኮሌጁ አቅዶ የሚተገብራቸው ዋና ዋና ግቦችና ተግባራት በጊዜ እና በሀላፊነት ደረጃ ተደራጅተው የተዘጋጁ መሆናቸው ታውቋል። እነዚህ ሥራዎች ቆጥሮ መስጠትና ቆጥሮ መቀበል በሚያስችል አገባብ የተቀመጡ ከመሆናቸውም በላይ የክትትል ሥርአት ተዘርግቶላቸዋል። አፈጻጸሙም ግልጸኝነትን በማስፈን ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የሚረዳ ነው ።
በአጠቃላይ ኮሌጁ የተቋቋመበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ያስችል ዘንድ በ10 ነጥቦች የተቃኘ ስልጣንን፣ ኃላፊነትን እና ተጠያቂነትን ያሰናሰነ የስምምነት ሰነድ ከስልጠና ጉዳዮች አስተባባሪ፣ ከተቋማትና አሠልጣኝ ልማት ም/ዲን ፣የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ም /ዲን እንደዚሁም ከሽሮ ሜዳ ካምፓስ ም/ዲን ጋር ተፈራርመዋል።
በተመሳሳይ እያንዳንዱ ተፈራራሚ በስሩ ከሚገኙት በየደረጃው ካሉት አካላትና አባላት ጋር የሚተገበር ዕቅድና አተገባበሩን ያካተተ የስምምነት ሰነድ አዘጋጅቶ በመፈራረም ወደ ስራ እንደሚገባ ለመረዳት ተችሏል፤ይጠበቃልም።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በትምህርት ሥራ አመራር ስርዓት (ISO 21001፡2018 Educational Organization Management System) ሰርተፊኬት አገኘ
ኮሌጁ በትምህርት ሥራ አመራር ስርዓት ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን ማሟላቱን አረጋግጦ ሰርተፊኬቱን መስጠቱን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አስታውቋል፡፡
ኮሌጁ ሰርተፍኬቱን ማግኘቱ የሚሰጠው የስልጠና አገልግሎት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭ እንዲሆኑ አስቻይ ሚና እንደሚጫወት የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ መግለፃቸውን ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሥሩ የሚገኙ ተቋማት ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎችን ያሟሉና የሚሰጡት አገልግሎት ፈጣን፣ ቀልጣፋና በሁሉም ደረጃ ተቀባይነት ያለው እንዲሆን በትኩረት እየሠራ ይገኛል፡፡
ከኢትዮጲያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል፡፡
በዚህም 47 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት እና የሁሉም ክልሎችና የሁለቱም ከተማ አስተዳድሮች የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ኤጀንዎች ወደ ሥራዓቱ የሚገቡበት አቅጣጫ ተቀምጦ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡
በእስካሁኑ ሂደትም የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት፣ የተፈሪ መኮንን እና የደብረ ብርሃን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆችን ጨምሮ አስር የሚሆኑ የስልጠና ተቋማት የዓለም አቀፉ የትምህርት ተቋማት ሥራ አመራር ስርአትን በማሟላት ሰርተፊኬት ተሰጥቷቸዋል፡፡
ነሐሴ 3/2017 ዓ.ም
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ በሚከተሉት የማህበራዊ ትስስር ገፆች ይከታተሉን፡
Website: 🌐 http://mols.gov.et
Facebook: 📱 https://www.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: 📱 https://t.me/fdre_mols
TikTok: 📱 tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: 📱
https://twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
1 148
ሐምሌ 30/2017ዓ.ም
በኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ሁለት ዘርፎች ላይ ለተዋቀሩ 4 ቡድኖች ኦረንቴሽን ተሰጠ።
በቴክኖሎጂ ዘርፍ የተዋቀሩት ቡድኖች የቴክኖሎጂ ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በኢንተርፕራይዞች እና በኢንደስትሪዎች የሚፈለጉ የቴክኖሎጂ አይነቶችን ይለያሉ ፤ የተለዩቱ ቴክኖሎጂዎች ተመርተው ወደ ገበያው ይገባሉ።
ሌላኛው ዘርፍ የቴክኖሎጂ ፋይዳ ዳሰሳ ጥናት ቡድን በ2017በጀት ዓመት በኮሌጁ ተቀድተው የተሸጋገሩ ቴክኖሎጂዎች በኢንተርፕራይዙ ላይ ያመጣው ለውጥ /ያስገኘው ፋይዳ ምንድነው ? የሚለውን የሚያጠና ሲሆን ዓላማውም በቀደመው ስራ ላይ የነበረውን ክፍተት በመለየት ክፍተቱን የሚሞላና የቀጣዩን ለማሻሻል ማገዝ ነው ።
በተመሳሳይ በዚህ ክፍል ላይ የኢንተርፕራይዝ ድጋፍን የሚመለከት ሲሆን በዚህ ዘርፍም ሁለት ቡድኖች ተዋቅረዋል ። የመጀመሪያው ቡድን በ181 የነባር ኢንተርፕራይዞች የድጋፍ ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሲሆን ኢንተርፕራይዞቹ ከአራቱም የድጋፍ ማዕቀፍ በየትኛው ላይ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ይፈልጋሉ? የሚለውን በጥናት በበመለስ በፍላጎታቸው ላይ ተመስርቶ ድጋፍ ለመስጠት የሚያስችል ነው ።
ሁለተኛው ቡድን በLMIS ላይ የተመዘገቡትን 1664 ኢንተርፕራይዞች ከክፍለ ከተማ ባለሙያዎች ጋር በመሆን የአካል ርክክቡን ፎርም በማስሞላት የሚያከናውን ቡድን ሲሆን ኢንተርፕራይዞቹ ለ2018 ዓ.ም የሚፈልጉትን የድጋፍ አይነት እና መቼ እንዲደገፉ ይፈልጋሉ ? የሚለውን በድጋፍ አይነትና ግዜ በመለየት ያስቀምጣል ።
በአጠቃላይ በነዚህ ሁለት ዘርፎች ውጤታማ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የኢንተር ፕራይዝ ድጋፍ ለማድረግ ከተለያዩ ስልጠና ዘርፎች የተውጣጡ አሰልጣኞች ፣ ከክፍለ ከተማና ከወረዳ የተወከሉ ባለሙያዎች በተገኙበት የኮሌጁ ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን አቶ ወንድም ሲያኝረኝ መኮንን እና የዘርፍ ኃላፊዎች የየዘርፋቸውን ሰፊ ማብራሪያና የጋራ የስራ ስምሪት ሰጥተውበታል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን።
1 148
+4
ሐምሌ 30/2017ዓ.ም
የE-school ትግበራን አስመልክቶ
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
የE-school ሲስተም ምንድ ነው ? E-school ሲስተም ምን ምን ጉዳዮችን ይይዛል? ምን ጠቀሜታስ አለው ? በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ለኮሌጁ አሠልጣኞች ፣አስተባባሪዎች፣ የሬጅስትራር ባለሙያዎች የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተዘጋጅቷል።
E-school ሲስተም ከመማር ማስተማሩ ባሻገር አስተዳደራዊ ስርዓትን ውጤታማ የሚያደርግ ፕላት ፎርም በመሆኑ አሰራርን ለማዘመን፣ተደራሽ ለማድረግና የክፍለ ዘመኑን አሰራር በመቀላቀል ውጤታማ ማድረግ የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል። ስራው በሚፈለገው ልክ ተግባራዊ እንዲሆን ለማስቻል በቀጣይ በየስልጠና ዘርፉ ለሁሉም አሰልጣኞች ስልጠናው ተጠናክሮ የሚሰጥ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ።
በስልጠናው ማጠናቀቂያ በነበረው ውይይት የስልጠናው አቀራረብና አስፈላጊነት ከመዘግየቱ ውጪ አጠያያቂ አይደለም ያሉት ተሳታፊዎቹ በየስልጠና ዘርፉ ያለው የኮምፒውተር እጥረት እና የኔትወርክ ተደራሽነት ለውጤታማነቱ ተግዳሮት እንዳይሆን ከወዲሁ ቢታሰብበት በማለት አስተያየት ተሰጥቷል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
+5
ሐምሌ 29/2017 ዓ.ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዓመታዊ የገ/ቁ/ኅ/ሥራ/ማኅበር ጉባኤ ተካሄደ።
"ዘወትር ቆጥቡ ለቁም ነገር ተበደሩ በግዜ ክፈሉ"
የ2016/17በጀት ዓመት ዕቅድ ክንውን ሪፖርት ፣ያጋጠሙ ችግሮች እና የ2017/18በጀት ዓመት ዕቅድ በማህበሩ ስራ አስፈፈጻሚ ለጠቅላላ ጉባኤው ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ። በተጓዳኝ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ማህበራት ማደራጃ የኢንስፔክሽን አመራሮች
ወ/ሮ ያይኔ አበባ እና አቶ ደሞዝ የኦዲት ሪፖርታቸውን አቅርበዋል ። በሪፖርቱ አንዳንድ መስተካከል አለባቸው የተባሉ ጉዳዮች የቀረቡበት ሲሆን በሁለቱም አካላት የቀረበው ሪፖርት የሚጣጣም እንደነበር ለመታዘብ ተችሏል።
በተካሄደው ውይይት በአዲሱ የበጀት ዓመት መሻሻል ያስፈልጋቸዋል የተባሉትን ጉዳዮች ማለትም
- ዓመታዊ የተቀማጭ ወለድ ከ6% ወደ 7%
እንዲያድግ
- የብድር ወለድ ደግሞ ከ9%. ወደ 10% ከፍ እንዲል ከመወሰኑ በተጨማሪ የዓመት በዓል ብድር ከብር 10,000 ወደ ብር 15,000 እንዲያድግ እና የወለድ ምጣኔው ከ10% ወደ 15% ከፍ እንዲል የጠቅላላ ጉባኤውን ይሁንታ አግኝቷል ።
ከእያንዳንዱ ዓባል የሚቆረጠው መዋጮ ግን በነበረበት ዝቅተኛው 10% ሆኖ እንዲቀጥል መወሰኑን ለመገንዘብ ተችሏል።
በተያያዘም ያለፈው በጀት ዓመት የትርፍ ክፍፍል ደግሞ የአባላቱን ድርሻ /ሼር ለማሳደግ እንዲውል አባላቱ ወስነዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ የኮሌጁ ስያሜ ከመቀየሩ ጋር ተያይዞ የማህበሩ መጠሪያ ስያሜ እንዲቀየር የተነሳውን ሃሳብ አባላቱ በሙሉ ድምጽ እንዲቀየር ተወስኖ ጉባኤው ተጠናቋል።
"ዘወትር ቆጥቡ ለቁም ነገር ተበደሩ በግዜ ክፈሉ"
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
+7
ሐምሌ28/2017ዓ.ም
በቢዝነስ ስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና ተካሄደ።
በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ በቢዝነስ ስልጠና ዘርፍ በጽህፈትና ቢሮ አሰተዳደር ከደረጃ ሁለት ወደ ደረጃ ሦስት የሚሸጋገሩ ሰልጣኞች የተቋም ውስጥ ምዘና አካሄዱ።
በትምህርት ክፍሉ የተዘጋጀና በስልጠና ዘርፉ ፀደቆ የቀረበው ምዘና በጠዋቱ ክፍለ ግዜ የቲዎሪና ከሰዓት የተግባርን ያጣመረ ሲሆን ለምዘና የተቀመጡት 26 ሴት ሰልጣኞች መሆናቸውን ከትምህርት ክፍሉ ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል።
ለተመዛኞች መልካም ዕድል እንመኛለን።
የኮሙንኬሽን ቡድን
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
