ብዕሬ ስትቀልም ✍
ቀለም ካለ በቀለም 📝 ካለቀም ሀሳቤን በእንጨት እጽፋለሁ ✍ ብዕሬም ቀለም እኔም ሀሳብ ከጨረስኩ 🙆🙆😔እኔም አልቄ ይሆናል 🤷♀ ከእድሜዬ ጋር ሀሳቤን አርዝምልኝ🙏 ~~~ እስክናልቅ ተቀላቀሉን😂🥰~~~
Mostrar más434
Suscriptores
Sin datos24 horas
-87 días
-2730 días
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
ስሙኝማ ባልና ሚስት ለዓመታት አንድ ላይ ሲኖሩ ልጅ የልጅ እያፈሩ ቤተሰብ ዘመድ ለራሳቸው እያበዙ ኖረው ኖረውም ያቺ ዘሩን ያስቀጠለችለት ረዳትና ያ የእርሷና የቤቷ ራስ የሆነው አባወራ በግዜ ብዛትም ቢሆን አለመዛመዳቸው ይገርማል።
ግን አንድ ቃል ይሄን ብሽቅ ሀሳቤን በኩርኩም መታውና ፍቅርን አገዘፈብኝ
“ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ፤ ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም።”
— ማርቆስ 10፥8
ለካስ አንድ ሥጋ ከራሱ ጋር አይዛመድም!🤷♀
😁 3🤔 2💯 1
11840
Repost from Tomarit seliniya📝
።።።።ፅሃይ ነበረችኝ።።።።።
እኔ ገና ልጅ እያለሁ በጣም የምወዳት ፅሃይ ነበረችኝ፣ ሁልግዜም አወጣጦን ድምቀቷን ለማየት የምጓጓላት ፣ ሁልግዜም ፍካቷን የምናፍቅላት ። ግን ሳድግ ጮራነቷ አለፈ እና ንዳድነቷ ተንሰራፋ አይኔ እያየ የምወደው ብርሃኗ ጨረር ሁኖ አይኔን ወጋኝ ፣ብርሃኖ በዛና ሰቀቀኗ ባሰኝ፣ጊዜው በሄደ ቁጥር በሷ ላይ ያለኝን ተስፋ እና እምነቴን አጣሁኝ
☀️እመት ፅሃየ ምነው ምነው ብርሃንሽን ቀነስ አድርገሽ ወደቀድሞው ደስታችን ብንመለስ😒😒
#ጦማሪት_ሰሊኒያ
👍 2🥰 2
8110
ማቱሳላ 😎
"አለመኖርን መኖርኮ ዕድል ነው። " ይለኛል ስለእሱ ለማወቅ ስፍጨረጨር እያየኝ እሱን ከማወቄ በፊት በየሰዉ ዓለም አለመኖር ምን እንደሆነ አይገባኝም ነበር በመኖር ከመረሳት ባለመኖር መታወስ የእሱ መርህ ነው መረሳትን አይፈቅድም ሁለ ነገሩ እርሱን አያስረሱትም ግን አወቅኩት ባሉት ሰዎች በቅጽበት ከዓለማቸው መኖሩን ይቀማል አለመኖርን ሲኖር አያስፈቅዳቸው ተላምደውት በየቀን ውሏቸው የራሱን ሀውልት ከሰራ በኋላ ከእምጥ ይግባ ከማጥ ማንም ሳያውቅ በቅጽበት ይሰለባል መንፈስም ያረገዋል መሰል ዓለም እሱን ፍለጋ ሲባዝን ባለመኖር ውስጥ ይመሸጋል ከዛን ድንገት ምንም በማያውቁት ሰው መኃል እንደ አዲስ መኖርን ይጀምራል የዓላማቸው ተጋሪ የህፃን የአዋቂው ልብ ማረፊያ የአይረሴ ትዝታቸው ባለቤት የትንሽ ትልቁ የመጨረሻ መኃላ ማቱሳላን ብዬ አልዋሽም ማለት ሲጀማምራቸው ነፍስ ገድሎ ቢያዝ እንኳ በስሙ ከማለ የሚታመንበት ማቱሳላን ብሎ የዋሸ ሀገር የካደ ያክል የሚቆጠርበትን ወቅት ለመፍጠር ዓመታት አይፈጅበትም ደም የተቃባ ማቱሳላ ካሸማገለ ይቅር ለእግዜር በሚል ፈንታ ይቅር ለማቱሳላ ይል ይመስል በእሱ ተሸምግሎ ያልታረቀ ተፈርዶበት ያልከወነ በመንደሩ እስኪጠፉ መኖሩን በግድ ግቶ እንዲቀበሉ ያረጋቸውና በአንዴ መማያ ያሳጣቸዋል ግን ማቱሳላን የማያውቅ ትውልድ እስኪነሳ ድረስ የእርሱ ሰም የሀገሬው መተማመኛ ቃል ሆኖ ይዘልቃል ማቱሳላን!። የጠፋ ሌት ማንም እሱን የማግኘት ስልጣን አይኖረውም ነበር ለማለት ለትውልድ የሚያሳዩት ዱካ እንኳ ሳያስቀር በየሰዉ ልብ የማይፍቁት አሻራውን አኑሮ ይሰለባል በቁስ መታወስ ሞቱ ነው የሟችን ቤት እያዩ ፈረሱን ዉሃ የምትቀዳበትን ማድጋ ባዩ ቁጥር ማስታወሱ ያበሽቀዋል እንደውም ሰው ከመሞቱ በፊት ሀብቱን ምንም በማያውቁት ህዝብ መንደር በምሽት ከብቶቹን ፈረሱን ሁሉ እየነዳ ጨክኖ ጥሎ መምጣትን አስለምዷል በቁስ ብቻ የሚታወስ ሰው መኖርን አያውቀውም ይል ነበር እናም ህዝብ ቤቴ ባይኖር ማን ያስታውሰኝ ነበር እያለ የሞተ ሰው ቤት ይቃጠላል ወይም ፈርሶ ለእርሻ ይሰጣል እንኳን የኖረን ሰው ዱካ ዶሮ የጫረችበትንም ቦታ እንዳልነበር አርጎ ማጥፉት አይቻልም ግን ቢያንስ ነበር የሚያስብል የቁስ አሻራ ይደብዝዝና ሰውን በልብ እናስታውስ ከዛን ቤቱ ፈርሶ በቆሎ ቢዘራበት እንኳ ይሄኮ የእከሌ ቤት ነበር ብለን ብናልፍ እንኳ ግድ የለውም ይል ነበር እናም የእርሱ መጥፉትም እንደዛ ነው ለማንም ቅሪት አያስቀርም ያንን ያየ ሰው መንፈስ ነው ክፉ በሆነበት ቦታ ከወደቁት መላዕክት ሰይጣን ልኮት ነው ደግነቱን ያዩ ደሞ ፈጣሪ መላዕክቱን ልኮልን ነው ማለታቸው አልቀረም።...
ይቀጥላል ..
✍ቱሪስት
@GLARAT
አላለቀም ግን አለው ለማለት ያክል
እጅ ከምን እንዳልባል በሚል☺️
39920
Repost from ብዕሬ ስትቀልም ✍
Photo unavailable
በመሞት ፀደቅኩ
ዛፍ ላይ ያለ ዘር ሀይለኛ ንፋስ ያለው ዝናብ ቢዘንብ ውሃውን ቢፈልግ እንኳ ለእርሱ እንደሌሎቹ የዛፉ ክፍሎች አስደሳች አይሆንም ዘር ራሱን ሆኖ አይደለም የሚቀጥለው ወይ ፍሬ አልያም ሌላ ዛፍ መሆን ይኖርበታል። የዛፍ ቅጠል ቅጠል ከመሆን በቀር ሌላ ነገ የለውም ግንዱም ባለበት መወፈር እንጂ ስር ሆኜ ልደግ አይልም ስር ለወደፊት ከስር በቀር የሚሆነው ነገር የለውም ዘር ግን ነገ አለው እሱ ቢጠፉ ነገዎቹም እንደሚጠፉ ያውቃል ሲለዝህ አሁን ብቻ ካላቸው ተለይቶ ከዝናቡና ንፋሱ ሁለት ነገር ይጠብቃል አንድም እሱን ሳይነኩት መሬቱን አረስርሰውለት እንዲሄዱ አልያም ንፉሱ ለም መሬት ላይ እንዲጥሉት ፍሬ ወይንም ዛፍ መሆን አለበት ከመውደቁ በላይ ለሚወድቅበት ይጠነቀቃል "መውደቂዬን አሳምርልኝ አይነት ነገር " ቅጠል ተቀንጥሶ ቢወድቅ ሌላ አፈር ፣ ግንድ ደሞ ማገዶ ይሆን ይሆናል ለማገዶነትም ለአፈርነትም መውደቂያ ያን ያህል ዋጋ የለውም ዘር ስትሆን ግን መውደቂያህም ያሳስብኀል መሬት ለወደቀ ዘር የሚረግጥ እግርን የመሰለ ነገር የለም ገፍታሪ ንፋስ የሰጠ አምላክ ረጋጭ እግር አይነፍገውም! ወደ መሬቱ እስኪጠልቅ ይረግጡታል ደግ አይደሉ ለሞቱ ያፈጥኑታል ታዲያ አሁንም መዝነቡ አይቀርም መሬት ላይ ከተደላደለ ኃላ ዝናብ የምስራቹ ነው ቦታና ጊዜውን የጠበቀ ነገር ሁሌም ውብ ነው እድሜ ለገፈተረው ንፉስና ሳይታክቱ ለረገጡት እግሮቹ ብቻ እርሱ ይሙት እንጂ የወደቀ ዘር በሞቱ ይፀድቃል አምላክም ዝናብ አይነፍገውም።
✍ቱሪስት
@GLARAT
10310
Photo unavailable
My toxic trait is that i don't know how to ask for help, I just disappear and come back when Im feeling better
12000
🙅♀🙅♀🙅♀🙅♀🙅♀🙅♀
የሰው ብቻ እኮ ነው ማሰቢያው ሚያዘግመው፣
አምላክ ሰው አይደለም ረሳኝ እንድንለው🤨!
✍ቱሪስት
@GLARAT
75770
Repost from የሄኖክ አሸብር ግጥሞች እና ወጎች
✍ እኔ እንደምወድሽ ❤❤❤✍
*****
(👉 እኔ ራሴ ሲበዛ የምወደው ግጥም....ተባረኩበት)
ይሄውልሽ ውዴ.......
ያን ጊዜ በእንባሽ ፣ እግሬን ባታርሽም
የብልቃጡን ሽቱ ፣ ሰብረሽ ባታፈሽም
ከበውኝ ቁጭ ያሉት ፣ "እሷ'ኮ" ባይሉሽ
በሹክሹክታ ጩኸት ፣ እያለሽ ባያሙሽ
የተማርሽበትን ፣ ፍቅር ባትገልጭም
እግሮቼን በፀጉርሽ ፣ በ'ንባሽ ባታብሽም
አብ እንደሚወደኝ ፣ እኔ እንደምወደው
በዛኑ መጠን ነው ፣ አንቺን የምወደው!!
ስሚኝማ ውዴ.......
ዘማዊ ናት ብለው ፣ እንውገራት ባይሉሽ
ጻድቃኖች ቢሆኑ ፣ አመንዝራ ያሉሽ
መሬት ላይ በጣቴ ፣ ጎንበስ ብዬ ባልፅፍ
ካንቺ በቀር ሌላ ፣ ሰው ህጉን ባያልፍ
ከከሳሾችሽ ላይ ፣ ክፋትን ባላገኝ
ያለም ሁሉ ሀጥያት ፣ ያንቺ ሆኖ ቢገኝ
እኔ እወድሻለሁ ፣ አብ እንደሚወደኝ!!
እናልሽ ውዴ ሆይ.......
ባል ባልሆኑ ባሎች ፣ ቢቃጠል ዘመንሽ
ገደብን ቢያበጅም ፣ ሳምራዊ መሆንሽ
ውሀ ልትቀጂ ፣ ብትመጭም ባትመጭም
ከ'ኔ ጠጪ ስልሽ ፣ ብ'ጠጪ ባ'ጠጪም
እኔን በልብሽ ውስጥ፣ ብትወጂም ባትወጂም
እኔ እንደምወድሽ ፣ አንቺ አንቺን አትወጂም!!
♥♥♥ እኔ እወድሻለሁ ♥♥♥
#ሄኖክ_አሸብር
https://t.me/joinchat/RrbSCabYHAXQ6nx7
14340
Elige un Plan Diferente
Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.