es
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

Ir al canal en Telegram

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Ethiopian Public Service University

El canal Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 12 732 suscriptores, ocupando la posición 15 756 en la categoría Educación y el puesto 2 642 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 12 732 suscriptores.

Según los últimos datos del 11 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 106, y en las últimas 24 horas de 3, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 34.72%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.17% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 419 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 058 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 27.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 12 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Educación.

12 732
Suscriptores
+324 horas
+207 días
+10630 días

Carga de datos en curso...

Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '26
+48
en 0 canales
junio '26
+131
en 0 canales
Get PRO
mayo '26
+30
en 1 canales
Get PRO
abril '26
+16
en 0 canales
Get PRO
marzo '26
+48
en 0 canales
Get PRO
febrero '26
+76
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+64
en 0 canales
Get PRO
diciembre '25
+92
en 0 canales
Get PRO
noviembre '25
+161
en 0 canales
Get PRO
octubre '25
+1 365
en 2 canales
Get PRO
septiembre '25
+967
en 7 canales
Get PRO
agosto '25
+254
en 0 canales
Get PRO
julio '25
+154
en 0 canales
Get PRO
junio '25
+280
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+318
en 2 canales
Get PRO
abril '25
+153
en 3 canales
Get PRO
marzo '25
+158
en 0 canales
Get PRO
febrero '25
+205
en 1 canales
Get PRO
enero '25
+221
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+104
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+140
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+448
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+1 009
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+1 419
en 2 canales
Get PRO
julio '24
+1 405
en 1 canales
Get PRO
junio '24
+325
en 0 canales
Get PRO
mayo '24
+305
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+286
en 0 canales
Get PRO
marzo '24
+284
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+450
en 0 canales
Get PRO
enero '24
+154
en 0 canales
Get PRO
diciembre '23
+4 040
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
12 julio+4
11 julio+3
10 julio+6
09 julio+5
08 julio0
07 julio+4
06 julio+4
05 julio+3
04 julio+3
03 julio+1
02 julio+12
01 julio+3
Publicaciones del Canal
የኢፐሰዩ ካውንስል የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የመደበኛ፣ የሪፎርም እና ቁልፍ የውጤት አመላካቾች (KPIs) ስራዎች አፈፃፀምን ገመገመ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) ካውንስል የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የመደበኛ፣ የሪፎርም እና ቁልፍ የውጤት አመላካቾች (KPIs) ስራዎች አፈፃፀምን ገመገመ፡፡ ካውንስሉ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ባደረገው ግምገማ፣ አጠቃላይ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት በስትራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ በአቶ ተፈሪ ጊሼ የቀረበ ሲሆን፣ በሪፖርቱም በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የተደረገውን ሀገራዊ የሪኦርየንቴሽን ጥናት መሰረት በማድረግ የዩኒቨርሲቲውን የአዲስ ምዕራፍ የሪፎርም ጉዞ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር የዝግጅት ምዕራፍ በይፋ መጀመሩን ተከትሎ፣ ተቋሙን የተግባር ሳይንስ (Applied Science) እና ራስ-ገዝ (Autonomous) ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት፣ የመሰረተ-ልማቶችን የማዘመን እንዲሁም ከመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ጋር በተያያዘ የተከናወኑ ስራዎች ተካተዋል። በሪፖርቱ እንደተመለከተውም፣ በዝግጅት ምዕራፉ ላይ የፖሊሲ ማዕቀፎችን ማዘጋጀት፣ አደረጃጀትን ማዘመን፣ የስርዓተ-ትምህርት ቀረጻ እና የትምህርት ጥራት ማስጠበቂያ ማዕከላት ስራዎችን በማከናወን የዝግጅት ምዕራፉ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገልጿል። ከሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙ ጋር በተያያዘም የነባር ስራ ሂደት ፍሰት፣ የኢንዱስትሪና የትምህርትና ሙያ ምድብ ጥናት፣ ከአገራዊ መስፈርቶች ጋር የተጣጣመ ስታንዳርድ፣ እንዲሁም ለስራ መደቦችና የሙያ ዘርፎች የሚሆን የሙያ ምድብ መዝገበ-ቃላት ተዘጋጅተዋል። በተጨማሪም የተሻሻለ አዲስ የስራ ሂደት ፍሰት ጥናትና አዲስ የዩኒቨርሲቲ መዋቅር ተዘጋጅቶ ለአፅዳቂ አካል የተላከ ሲሆን፤ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ የተሰላ የሰው ኃይል ፍላጎት ትመና፣ ለአዲሶቹ የስራ መደቦች በሙሉ የተዘጋጀ የስራ ዝርዝር (Job Description) ሰነድ እና በአዲሱ መዋቅር ለሚመደቡ ባለሙያዎች የሚሆን የቴክኒካል ብቃት ማዕቀፍ መዘጋጀቱም ተመልክቷል። የዩኒቨርሲቲው ወደ ሪፎርም ትግበራ ምዕራፍ ሽግግር ከተበሰረበት ከግንቦት ወር ጀምሮ ሰፋፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችና ስልጠናዎች መሰጠታቸውን ሪፖርቱ ጠቁሟል። በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ አጠቃላይ ስኬቶችን ሲያመለክትም፦ የዩኒቨርሲቲው የአዲስ ምዕራፍ የሪፎርም ጉዞ ወደ ትግበራ ምዕራፍ መሸጋገሩ፣ 18 የትምህርት ፕሮግራሞች በትምህርት ሚኒስቴር መጽደቃቸው እና 5 መሰረታዊ ኮርሶችን በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ከተለዩት የባህሪ ብቃት አመላካቾች ጋር የማጣጣም ስራ ሙሉ በሙሉ መከናወኑ ተገልጿል። በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን 1,817 ተማሪዎች መመረቃቸው፣ የዩኒቨርሲቲው ጆርናል የሆነው African Journal of Leadership and Development (AJOLD) በቅርቡ በትምህርት ሚኒስቴር ዕውቅና ማግኘቱ፣ እንዲሁም የምርምር ሥራዎችን በአገር ውስጥና በውጭ አገር የምርምር መጽሔቶች ማሳተም መቻሉ በሪፖርቱ ተመልክቷል። በተጨማሪም “ኢትዮ-ሰርቭ የንግድ እና ማማከር ኢንተርፕራይዝ” መመስረት፣ የግንባታ አመራርና ድጋፍ ወርሃዊ የሶስትዮሽ መድረክ ተቋቁሞ ለግንባታ ስራዎች የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው ዓለምአቀፋዊ የግራንት ዕድሎችን ለመጠቀም የሚያስችለው የተቋማዊ ግምገማ ቦርድ (Institutional Review Board IRB) አስፈላጊውን ሂደት አልፎ ህጋዊ ሰውነት ማግኘቱ፣ ከ12ኛ ክፍል አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር መጀመሩና የእስካሁኑ ሂደት በጥሩ ሁኔታ ላይ መገኘቱ፣ እንዲሁም የሕፃናት ማቆያ ተከፍቶ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተጠቃሽ ስኬቶች መሆናቸው ተብራርቷል። በሪፎርም ሂደቱ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችም የቀረቡ ሲሆን፤ በዕቅድ የተያዙ መደበኛ ስራዎችና የቁልፍ የውጤት አመላካቾች (KPIs) አፈፃፀምን በተመለከተ በስሌት በተደገፈ መረጃ ዩኒቨርሲቲው በከፍተኛ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ሪፖርቱ አመላክቷል። በመጨረሻም በቀረበው ሪፖርት ላይ የዩኒቨርሲቲው የካውንስል አባላት ለተነሱ ሀሳብና አስተያየቶች የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ካውንስሉም የቀረበውን ሪፖርት ገምግሞ አጽድቆታል።

2
የኢፐሰዩ ካውንስል የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የመደበኛ፣ የሪፎርም እና ቁልፍ የውጤት አመላካቾች (KPIs) ስራዎች አፈፃፀምን ገመገመ+4
የኢፐሰዩ ካውንስል የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የመደበኛ፣ የሪፎርም እና ቁልፍ የውጤት አመላካቾች (KPIs) ስራዎች አፈፃፀምን ገመገመ
2 176
3
የኢፐሰዩ ስልጠና ፋሲሊቲ ሰራተኞች በልምድ ያካበቱትን ክህሎት በምዘና አረጋግጠው በሰርተፊኬት ተመረቁ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) የስልጠና ፋሲሊቲ ስራ አስፈጻሚ ውስጥ ለረጅም ዓመታት በልምድ አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ሰራተኞች፣ ቀደም ሲል በሥራ ላይ ያካበቱት ዕውቅና የሚሰጥበትን የRPL (Recognition of Prior Learning) ደረጃ 2 ምዘና በስኬት አጠናቀው በሰርተፊኬት ተመረቁ። ከመጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በቱሪዝም ስልጠና ኢንስቲትዩት አማካኝነት ሲሰጥ በቆየው ስልጠና፣ በአጠቃላይ በአምስት ዋና ዋና የሆቴል እና ቱሪዝም የእንግዳ ተቀባይነት (Hospitality) የሙያ ዘርፎች ላይ በተካሄደው በዚህ ምዘና 139 ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን፣ 124ቱ ምዘናውን በብቃት አልፈው ሰርተፊኬታቸውን ተቀብለዋል፡፡ ሰራተኞቹ በዩኒቨርሲቲው ካፌቴሪያ፣ ላውንጅና የእንግዳ ማረፊያዎች ውስጥ ለረጅም አመታት አገልግሎት ሲሰጡ ቢቆዩም፣ ለዩኒቨርሲቲው ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ያገናዘበ እድገት እና የስራ ዋስትና አለማግኘታቸውን የተገነዘበው የዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራር ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማውጣት፣ ስልጠናውን እንዲከታተሉ እና ሀገር አቀፍ እውቅና ያለው የደረጃ II የሙያ ሰርተፊኬት እንዲያገኙ አድርጓል፡፡ ስልጠናው ለሰራተኞቹ የስራ እድገትና የደመወዝ ማሻሻያ ለመጠየቅ ሰፊ በር የከፈተላቸው ከመሆኑም በላይ፣ አገር አቀፍ እውቅና ያለው ህጋዊ ማስረጃ ማግኘታቸው የስራ ዋስትናቸውንና በራስ መተማመናቸውን ያሳድግላቸዋል፡፡ ይህንን አስመልክቶ ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ/ም በተዘጋጀው የሻይ ቡና መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ አጠቃላይ የስልጠናውን አስፈላጊነት እና ሂደት አስመልክተው ባደረጉት ንግግር፣ ዩኒቨርሲቲው በሁሉም ዘርፎች ለውጥ ላይ ከመሆኑ አንጻር ሰራተኞችንም በየሙያ ዘርፋቸው አሰልጥኖ ብቁ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ የተሰጠ ስልጠና መሆኑን ገልጸው፣ “ለዩኒቨርሲቲው ካበረከታችሁት አስተዋጽኦ ጋር ሲነጻጸር የተሰጣችሁ ስልጠና የሚገባችሁ እንጂ በቸርነት የተሰጣችሁ አይደለም፡፡” በማለት ለሰራተኞቹ የረጅም ዘመን ትጋት እውቅና ሰጥተዋል፡፡ አስከትለውም ስልጠናው የሰራተኞቹን የስራ ደረጃ እድገት ከማረጋገጡ በላይ ከፍ ያለ አፈጻጸም ሊኖራቸው እንደሚገባ በማሳሰብ፣ “ ማንኛውም ሰው ከሰለጠነ በኋላ እና ከመሰልጠኑ በፊት ባለው ብቃት ልዩነታ ማሳየት ይኖርበታል፡፡” ብለዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የተቋቋመው የኢትዮ ሰርቭ ኢንተርፕራይዝ የአስተዳደር እና ፋይናንስ ምክትል ስራ አስኪያጅ ሆኑት ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበራ በበኩላቸው፣ ሰራተኞቹ በስልጠናው ያገኙትን እውቀት እና ክህሎት አጣምረው ዩኒቨርሲቲውም ሆነ ተገልጋዩ በሚጠብቀው ልክ ውጤት ማምጣት እንደሚገባ ገልጸው፣ “በስልጠና ሳትታገዙ በቀን፣ በምሽት እና በአዳር የጎደለውን እየሞላችሁ እና አንዳንዴም እራሳችሁን አደጋ ላይ እየጣላችሁ ትልልቅ ስራዎችን ሰርታችኋል፤ በነበራችሁ ልምድ ብቻ ታግዛችሁ ይህን ያህል ውጤት ካስመዘገባችሁ አሁን ደግሞ በወሰዳችሁት ስልጠናው ታግዛችሁ ብዙ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባችኋል፡፡” በማለት ተናግረዋል፡፡ ስልጠናው በሰራተኞቹ ላይ ያመጣው የክህሎት እና የባህሪ ለውጥ አስመልክቶ የስልጠና ፋሲሊቲ ተጠባባቂ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ወ/ሮ ቤዛዊት ሰሎሞን እንደገለጹት፣ ሰራተኞቹ ከዘፈቀዳዊ አሰራር ወጥተው ደረጃውን የጠበቀ አሰራርን (Standard Operating Procedures) መከተል በመጀመራቸው፣ በምግብ ዝግጅትና መስተንግዶ ዘርፍ የጽዳት፣ የደህንነትና የጥራት አጠባበቅ ችሎታቸው በከፍተኛ ሁኔታ አድጓል፤ ከዚህም ባሻገር ለደንበኞች የሚሰጡት አገልግሎት ሙያዊ ስነ-ምግባርን የተከተለ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል፤ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲው የዓመታት ልፋታቸውን ተመልክቶ እንዲህ ያለውን አገር አቀፍ እውቅና የሚያስገኝ የሙያ ስልጠና እንዲያገኙ በማድረጉ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡
2 619
4
የኢፐሰዩ ስልጠና ፋሲሊቲ ሰራተኞች በልምድ ያካበቱትን ክህሎት በምዘና አረጋግጠው በሰርተፊኬት ተመረቁ+7
የኢፐሰዩ ስልጠና ፋሲሊቲ ሰራተኞች በልምድ ያካበቱትን ክህሎት በምዘና አረጋግጠው በሰርተፊኬት ተመረቁ
2 619
5
Sin texto...
3 494
6
በኢፐሰዩ በትምህርት ሚኒስቴር የጸደቁትን የትምህርት ፕሮግራሞች እና የመምህራን ምዘና ረቂቅ ሰነድ ለመምህራን እና ለአካዳሚክ አመራሮች ቀረበ፡፡ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአዲስ ምዕራፍ ተልእኮ ከቀረጻቸው 25 የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች ውስጥ በትምህርት ሚኒስቴር የጸደቁት 18 የትምህርት ፕሮግራሞች ዝርዝር እና ለመምህራን ምዘና በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀው ረቂቅ ሰነድ ለአካዳሚክ ሰራተኞች እና ለአካዳሚክ አመራሮች ቀረበ፡፡ ዩኒቨርሲቲው በአዲስ ምዕራፍ ተልዕኮ ለውጥ ከጀመረበት ከመስከረም 5 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በተሰጠው ተልዕኮ መሰረት ሥርዓተ-ትምህርት ቀርጾ ለትምህርት ሚኒስቴር ከላካቸው 25 የትምህርት ፕሮግራሞች ውስጥ 18 የትምህርት ፕሮግራሞች ተቀባይነት አግኝተው የጸደቁ ሲሆን፣ ይህንኑ አስመልክቶ ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ/ም በአባይ አዳራሽ በተዘጋጀው መርሀ ግብር ላይ የትምህርት ፕሮግራሞቹ ዝርዝር ይፋ ተደርጓል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር ጸድቀው የተላኩት የትምህርት ፕሮግራሞች ከአስተዳደር እና አመራር ኮሌጅ የህዝብ አመራር እና አስተዳደር፣ ማኔጅመንት እንዲሁም የልማት አስተዳደር የሚሉ 3 (ሶስት) የትምህርት ፕሮግራሞች ጸድቀዋል፤ ከሶሻል ሳይንስ ኮሌጅ ፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት የሚል 1 (አንድ) የትምህርት ፕሮግራም ፤ እንዲሁም ከኢኮኖሚክስ እና ፋይናንስ ኮሌጅ አፕላይድ ኢኮኖሚክስ፣ ፐብሊክ ፋይናንስ፣ አካውንቲንግ ኤንድ ፋይናንስ፣ ሎጀስቲክስ አንድ ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት፣ ታክስ ፖሊሲ ኤንድ አድሚኒስሬሽን፣ እንዲሁም ፕሮኪዩርመንት ኤንድ አሴት ማኔጅመንት የሚሉት 6 (ስድስት) የትምህርት ፕሮግራሞች ጸድቀዋል፤ በኮምፒውቲንግ ኤንድ ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ ኢንፎርሜሽን ሲስተም እና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ የሚሉ 2 (ሁለት) የትምህርት ፕሮግራሞች ጸድቀዋል፤ እንዲሁም በህግ ትምህርት ቤት 1(አንድ) የህግ ትምህርት ፕሮግራም ተልኮ ጸድቆ ተመልሷል፤ በተጨማሪም በከተማ ጥናት ኮሌጅ ኧርባን ፕላኒንግ ኤንድ ዲዛይን፣ ኧርባን ላንድ ማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስተም፣ ሪል ፕሮፐርቲ ኢቫሉዌሽን፣ ሰርቬይንግ ኢንጂነሪንግ እና ኧርባን ኢንጂነሪንግ የሚሉት 5 (አምስት) የትምህርት ፕሮግራሞች የጸደቁ ሲሆን፣ በድምሩ 18 (አስራ ስምንት) የትምህርት ፕሮግራሞች በትምህርት ሚኒስቴር መጽደቃቸው ታውቋል፡፡ በመርሃ- ግብሩ ላይ ተገኝተው በጸደቁት የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ገለጻ ደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ እንደተናገሩት፣ የመምህራን አቅም ግንባታ እና የተግባር ማስተማሪያ ግብዓት ዝግጁ የማድረግ ተግባር ከጸደቁት የትምህርት ፕሮግራሞች ጋር ተሳስረው የሚሄዱ ጉዳዮች በመሆናቸው፣ በዚህ ክረምት መጠናቀቅ ያለባቸው ተግባራት መሆናቸውን በመጥቀስ፣ ከወዲሁ አስፈላጊው ዝግጅት እንዲደረግ ለሚመለከታቸው የአካዳሚክ አመራሮች ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡ በማስከተልም ተዘጋጅቶ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በቀረበው የተግባር ሰይንስ ዩኒቨርሲቲ አደረጃጀት መሰረት ለሚኖረው የመምህራን ምዘና ዝግጅት የሚረዳ ረቂቅ ሰነድ በዶ/ር ንጉስ ታደሰ አማካኝነት ቀርቦ ለመምህራኑ ቅድመ ዝግጅት የሚረዳ ግንዛቤ ማስጨበጫ እና ምክረ ሀሳብ ቀርቧል፡፡ ከቀረበው ረቂቅ ሰነድ ለመረዳት እንደተቻለውም የመምህራኑ ምዘና የሚደረገው ባላቸው ፖርት ፎልዮ ላይ ተመስርቶ ሲሆን ቴክኒካዊ ብቃትን የሚመለከቱት መመዘኛ ነጥቦች፣ የመማር ማስተማር እና የስልጠና ውጤታማነት፣ የምርምር ምርታማነት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የማህበራዊ አገልግሎት አስተዋጽኦ፣ የተቋማት አቅም ግንባታ ስራዎች አስተዋጽኦ፣ የአካዳሚክ አስተዳደር ስራዎች አስተዋጽኦ እና የሙያ ልማት እና ተቋማዊ አስተዋጽኦ የሚሉት ናቸው፡፡ ባህሪያው ብቃትን የሚመለከቱ መመዘኛዎች በአስራ ሁለቱ የባህሪ ብቃት ማእቀፎች ውስጥ ተካቶ እንደሚካሄድ እና የቴክኒካዊ ብቃትም ሆነ የባህሪያዊ ብቃት ምዘና ስርዓቱ የሚካሄደው የትምህርት ሚኒስቴር በሚያቋቁመው ገለልተኛ አካል መሆኑም ተመላክቷል፡፡ በመጨረሻም ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ከአካዳሚክ ሰራተኞቹ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
2 822
7
በኢፐሰዩ በትምህርት ሚኒስቴር የጸደቁትን የትምህርት ፕሮግራሞች እና የመምህራን ምዘና ረቂቅ ሰነድ ለመምህራን እና ለአካዳሚክ አመራሮች ቀረበ፡፡+4
በኢፐሰዩ በትምህርት ሚኒስቴር የጸደቁትን የትምህርት ፕሮግራሞች እና የመምህራን ምዘና ረቂቅ ሰነድ ለመምህራን እና ለአካዳሚክ አመራሮች ቀረበ፡፡
2 275
8
ውድ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ቤተሰቦች የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን (EBC) ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ፣የዩኒቨርሲቲያችንን የለውጥ ጉዞ የሚቃኝ ዶክመንተሪ  እንድትከታተሉ የፕሮግራም ጥቆማ መስጠታችን ይታወቃል፡፡ ዶክመንታሪውን በቀጥታ መከታታል ያልቻላችሁ፣ https://youtu.be/b6V2Wk-DRj8?si=qgeVQNnV6Zg11TnB በዚህ ማስፈንጠሪያ (ሊንክ) በመግባት ማየት የምትችሉ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ
7 213
9
ውድ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ እንኳን ለተማሪዎች ምረቃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን፣ ዛሬ ምሽት ከ3፡ 00 ሰዓት ዜና በኋላ በኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን (EBC) የዩኒቨርሲቲያችንን የለውጥ ጉዞ የሚቃኝ ዶክመንተሪ ስለሚቀርብ እንድትከታተሉ የፕሮግራም ጥቆማ ለመስጠት እንወዳለን፡፡ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ
6 708
10
ኢፐሰዩ በልዩ ልዩ የትምህርት መርሀ-ግብር ያሰለጠናቸውን 1817 ተማሪዎች በድምቀት አስመረቀ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በልዩ ልዩ የትምህርት መርሀ-ግብር ያሰለጠናቸውን 1,817 ተማሪዎቹን በዛሬው ዕለት በአድዋ ድል መታሰቢያ ፓን አፍሪካን አዳራሽ በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመረቀ። ከተመራቂዎቹ መካከልም 4 የፒኤች ዲ ተመራቂዎች ሲሆኑ 454ቱ ደግሞ ሴት ተመራቂዎች ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም 151 የዩኒቨርሲቲውን የፋሲሊቲና መስተንግዶ ሰራተኞችም ዩኒቨርሲቲው ከሆቴልና ቱሪዝም ኢንስቲትዩት ጋር ባደረገው ስምምነት በደረጃ ሁለት ሰርቲፊኬት አስመርቋል። በምረቃ በዓሉ ላይ የኢፌዴሪ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ይህ የምረቃ ዕለት ተመራቂዎች የደረሱበት ደረጃ የግል ስኬት ብቻ ሳይሆን ዜጎችን በታማኝነት ለማገልገልና ለኢትዮጵያ የተሻለ ወደፊት ለመገንባት ቃል ኪዳን የሚገቡበት ታሪካዊ ቀን መሆኑን ገልጸዋል። አያይዘውም በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ እጅግ ትልቅ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም በቁርጠኝነት መተግበር መጀመሯን ጠቅሰው የዚህ ሪፎርም ሀገራዊ ራዕዩ ሰው ተኮር፣ በብቃት ላይ የተመሰረተ፣ ግልጽ ተጠያቂነትን የሚያሰፍን፣ ዲጂታል፣ ፈጠራን የሚያበረታታና ውጤት ተኮር የሆነ የላቀ አገልግሎት ለዜጎች ማቅረብ እንደሆነ አብራርተዋል። ይህንን በሰባት ዓምዶች የተከፈለውን ስትራቴጂካዊ ሪፎርም የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በበላይነት እያስተባበረው እንደሚገኝና ዋና ዓላማውም የመንግስት ተቋማትን ማዘመንና ለእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚሰጠውን የአገልግሎት ጥራት ማላቅ እንደሆነ ገልጸዋል። በዚህ ታላቅ ሀገራዊ ለውጥ ውስጥ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እሴትን፣ ዕውቀትንና በጎ አስተሳሰብን ሰንቀው የሲቪል ሰርቪሱን የሚቀላቀሉ ብቁ ሰራተኞችን በላቀ ደረጃ በማዘጋጀት ረገድ የላቀና ስትራቴጂካዊ ሚና እንደሚጫወት የሚጠበቅ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ክቡር ኮሚሽነሩ አክለውም የአሁኑን ዘመን የአገልግሎት ተግዳሮቶች በተለመደው አሮጌ መንገድና አቀራረብ ብቻ መፍታት እንደማይቻል አስገንዝበው፣ ለዚህም ወቅቱን ያገናዘበ፣ በማስረጃና በመረጃ ላይ የተመሰረተ መፍትሄ እንዲሁም ቀጣይነት ያለው ትምህርት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው የሚካሄዱ ጥናቶች የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦችን፣ ተቋማዊና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያዎችን እንዲሁም አጠቃላይ የመንግስት ዘመናዊነትን የሚመለከቱ አጀንዳዎች ላይ ማተኮር እንዳለባቸው አሳስበዋል። መንግስት ዩኒቨርሲቲው ለዘመናዊ ቢሮክራሲና አመራር ልማት የልቀት ማዕከል እንዲሆን የሚጠብቅ ሲሆን፣ ይህም በአካዳሚ ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን በተግባርና በአገልግሎት ዘርፍ ዕውቀት ባላቸው ተመራማሪዎችና አሰልጣኞች ሊደገፍ እንደሚገባ ተጠቁሟል። ከዚህም በላይ የመምህራን ጥራት ከተመራቂዎች ጥራትና ከሀገሪቱ የመንግስት አገልግሎት አስተዳደር ጥራት ጋር ቀጥተኛ ትስስር እንዳለው በማንሳት፣ በአካዳሚው ብቃትና ምርምር ላይ ቀጣይነት ያለው የመንግስት ኢንቨስትመንት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። ተመራቂዎችም ወደ ስራው ዓለም ሲሰማሩ ጥራት ያለውና አምራች ዜጋ መሆን እንዲችሉ ፣በተሰማሩበት ቦታ ሁሉ ሁሌም በታማኝነት ማገልገል፣ በብቃት መስራትና በብቃት መምራት፣ ፈጠራንና ፍጥነትን በስራ ላይ መለማመድ፣ ቀጣይነት ያለው ትምህርትን የህይወት አካል ማድረግ፣ በምታደርጉት ተግባር ሁሉ "ዜጎችን ማዕከል ማድረግ" የሚሉትን መርሆዎች ሁልጊዜ እንዲያስታውሱ አደራ ብለዋል፡፡ በመጨረሻም የተቀበሉት ዲግሪ የተማሩትን ትምህርት ብቻ የሚያሳይ ሳይሆን ለሀገር የሚበረከት ታላቅ ቃልኪዳን ጭምር መሆኑን አብራርተዋል። "ሀገራችን ዛሬ የምትፈልገው ችግርን የሚያብራራ ብቻ ሳይሆን ችግርን በተግባር የሚፈታ፣ ለውጥን ተቀብሎና ተግብሮ ሰርቶ የሚያሳይ፣ እንዲሁም በስነ-ምግባር አመራር የዜጎችን እምነት የሚያገኝ ባለሙያና መሪ ነው" ያሉት ኮሚሽነሩ "የእውነተኛ ስኬት መለኪያ የያዛችሁት ማዕረግ ወይም ዲግሪ ሳይሆን፣ ያሻሻላችሁት የዜጎች ህይወት መሆኑን ዘወትር በልባችሁና በአዕምሯችሁ ሊታተም ይገባል" በማለት ተመራቂዎች ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ሲወጡ በራስ መተማመን፣ በትህትና እና በቁርጠኝነት ታላላቅ ህልሞችን እንዲያልሙ፣ በትጋት እንዲሰሩና በታማኝነት በማገልገል ዕውቀታቸውን ወደ ጥበብ እንዲለውጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ ፐበሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ባደረጉት ንግግር ተመራቂ ተማሪዎች ለዚህ ስኬት በመብቃታቸው "እንኳን ደስ አላችሁ" ብለዋል። አክለውም ዩኒቨርሲቲው የፌደራል ሥርዓቱን መመሥረት ተከትሎ በወቅቱ የነበረውን ክፍተት የመሙላት ተልዕኮን አንግቦ የተቋቋመ መሆኑን አስታውሰው፣ ባለፉት ሦስት አሥርት ዓመታትም በፐብሊክ ሴክተሩ የአቅም ግንባታ ጉዞ ላይ ደማቅ አሻራ ማሳረፉን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲውን ለመለወጥ በተጠናው ሀገራዊ ጥናት መሠረት በርካታ ተቋማዊ፣ አካዳሚያዊና አስተዳደራዊ ሪፎርሞች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ዩኒቨርሲቲውን ወደ ተግባር ሳይንስ (Applied Science) ዩኒቨርሲቲነት ለመቀየር የ25 የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች ተቀርጸው ለትምህርት ሚኒስቴር ቀርበዋል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ1,500 በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን በቀጥታ ተቀብሎ ማስተማር መጀመሩንም አስታውሰዋል ። አያይዘውም በምርምርና በስልጠና ዘርፍ ዩኒቨርሲቲው በርካታ መደበኛና የሪፎርም ስራዎችን በመስራት ላይ መሆኑን ገልጸው፣ በገቢ ማመንጨት ሂደትም ዩኒቨርሲቲው በጥናት በተለየው መሰረት አዲስ ኢንተርፕራይዝ ማቋቋሙንም ገልጸዋል። በሌላ በኩልም በዩኒቨርሲቲው ለበርካታ ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩ የፋሲሊቲና መስተንግዶ ሰራተኞች በደረጃ ሁለት ሰርተፊኬት መመረቃቸውን አስመልክቶ "እነዚህ ተመራቂዎች ለተቋማቸውም ለሀገራቸውም በጣም ትልቅ አስተዋፅኦ የሚያደርጉና ለረጅም ጊዜ በዚያው ደረጃቸው የቆዩ እናቶች ናቸው። ስለዚህ፣ ህንፃ ከማደስ ባለፈ፣ የተለመደውን ዲግሪም ከመስጠት ባለፈ፣ ለእነኚህ ሰራተኞች ከፍ እንዲሉ ማሰልጠን አስፈላጊ በመሆኑ፣ በኢትዮጵያ ሆቴልና ቱሪዝም ኢንስቲትዩት እንዲሰለጥኑ አድርገናቸዋል" ብለዋል። በተለያየ የመስተንግዶ፣ በምግብ ዝግጅትና በመሳሰሉት ዘርፎች ለአራት ወራት ሰልጥነው፣ ምዘናም ተመዝነው፣ ደረጃ ሁለትን (Level 2) አሟልተው ዛሬ ለምረቃ መብቃታቸውን የገለጹጽ ዶ/ር ንጉስ "ለሀገራቸው የለፉ እናቶች ናቸው። ሰው መተካት ትልቅ ነገር ነው፤ በጎና መልካም ነገር ማድረግ ደግሞ የላቀ ተግባር ነው ስለዚህ፣ ልናመሰግናቸውም ልናከብራቸውም ይገባል። የአንድ ሰው ትልቅነት የሚለካው ብዙ ነገሮች ቢኖሩትም፣ ለሀገሩ ባለው አስተዋፅኦና አበርክቶ ላይ መሆን ይኖርበታል። በአቅማቸውና በልካቸው ለሀገራቸው እያገለገሉም ይገኛሉ" ብለዋል። ይህ ስልጠና በዓይነቱ ልዩ የሆነና በሀገሪቱ ታሪክም ፋና ወጊ ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል መሆኑ በመድረኩ የተገለጸ ሲሆን፣ ስልጠናውን ከወሰዱት መካከል 93 በመቶ የሆኑት ለደረጃው የተዘጋጀውን መመዘኛ አልፈው ሊመረቁ መቻላቸው ተጠቅሷል። በመጨረሻም በትምህርታቸው ብልጫ ላስመዘገቡ ተማሪዎች የሜዳሊያና የዋንጫ ሽልማት ከዕለቱ የክብር እንግዳ እጅ ተቀብለዋል፡፡
6 128
11
ኢፐሰዩ በልዩ ልዩ የትምህርት መርሀ-ግብር ያሰለጠናቸውን 1817 ተማሪዎች በድምቀት አስመረቀ
ኢፐሰዩ በልዩ ልዩ የትምህርት መርሀ-ግብር ያሰለጠናቸውን 1817 ተማሪዎች በድምቀት አስመረቀ
3 968
12
+9
Sin texto...
5 823
13
Sin texto...
5 405
14
የእንኳን ደስ አላችሁ   ለተከበራችሁ የኢትዮጵ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲው  ማህበረሰብ፣ ውድ ወላጆች እና ተመራቂዎች፤ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ-ግብሮች ትምህርታቸውን በስኬት ያጠናቀቁ የ2018 ዓ.ም ተማሪዎቹን የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም (ፓን አፍሪካ አዳራሽ) በታላቅ ድምቀት ያከናውናል። ዓመታትን በትጋት እና በፅናት አሳልፋችሁ ለዚህ ታላቅ ቀን የበቃችሁ የዘንድሮው ዓመት ተመራቂዎች በሙሉ፤ እንኳን ለዚህ ለስኬት ቀን አበቃችሁ! ሁላችሁም የነገ አገር ተረካቢዎች፤ በእውቀታችሁ አገርን የምታገለግሉበት፣ በሙያችሁ የምታበሩበት ስኬታማ ዘመን እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን! እንኳን ደስ አላችሁ! የኢትዮጵ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲው  ህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ
8 456
15
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሪፎርም ጉዳዮች ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አካሄደ በተቋማዊ የሪፎርም ሂደት ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣+1
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሪፎርም ጉዳዮች ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አካሄደ በተቋማዊ የሪፎርም ሂደት ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ከሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ስትራቴጂካዊ ውይይት አካሂዷል። በትምህርት ሚኒስትሩ ሰብሳቢነት በተመራው በዚህ ወሳኝ መድረክ ላይ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።ውይይቱም በዋናነት ትኩረት ያደረገው የአካዳሚክ ስታፍና አመራር ምዘና መመሪያ ላይ ነበር፡፡ በውይይቱ ወቅት መመሪያው መያዝ ስለሚገባው ይዘት እና መደረግ ስላለባቸው ማሻሻያዎች ሰፊ ምክክር ተደርጓል። በማጠቃለያውም ክቡር የትምህርት ሚኒስትሩ የቀረቡት ጠቃሚ ግብዓቶች ተካተው ሰነዱ በቀጣይ የሚጸድቅበትን ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ ካስቀመጡ በኋላ ውይይቱ ተጠናቋል።
5 496
16
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እና የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ስምምነት ተፈራረሙ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አዘጋጅነት ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም የሚጀምረዉን ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ተሳታፊዎችን ለማስተናገድ የሚያስችል ስምምነት በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ እና በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ መካከል ተፈረመ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 ሲቋቋም በኢትዮጵያ በሚገኙ የተለያዩ የፖለቲካ እና የሃሳብ መሪዎች እንዲሁም የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሃሳብ ልዩነት እና አለመግባባት የሚታይ በመሆኑ፤ ይህንን ልዩነት እና አለመግባባት ለመፍታት ሰፋፊ ሀገራዊ የህዝብ ምክክሮችን አካታች በሆነ መንገድ በማካሄድ ሀገራዊ መግባባት መፍጠር አስፈላጊ መሆኑ ታመኖበት ነዉ፡፡ ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ አንዲደረግ ተወስኗል፡፡ በዚህም መሰረት በኮሚሽኑ አዘጋጅነት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በሚካሄደው ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ተሳታፊዎችን ለማስተናገድ ከተመረጠው የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡ በፊርማ ሥነ-ስርዓቱ ላይም የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) አንደገለጹት ዉሎዉን በአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ሰንተር የሚያደርገዉ ጉባኤ ላይ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል የተዉጣጡ 3000 በላይ ተሳታፊዎች እንደሚታደሙ እና ከነዚህ ተሳታፊዎች ዉስጥ 1800 የሚሆኑት በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ አንደሚቆዩ ስምምነት ላይ መደረሱን ተናግረዋል፡የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ በበኩላቸዉ የዚህን ታሪካዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች ተቀብሎ ማስተናገድ ሀገራዊ ኃላፊነት መሆኑን ጭምር በማንሳት ተሳታፊዎች በቆይታቸዉ ጊዜ ጥሩ እና የተሻለ አገልግሎት እንደሚያገኙ ሙሉ እምነት እንዳላቸውም ገልጸዋል፡፡
4 165
17
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እና የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ስምምነት ተፈራረሙ+2
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እና የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ስምምነት ተፈራረሙ
3 949
18
የኢፐሰዩ አመራሮችና ሰራተኞች በሳይንስ ሙዚየም የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አውደ-ርዕይን ጎበኙ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በዶ/ር ንጉሥ ታደሰ የተመራ እና ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ መምህራንንና የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ ቡድን፣ በሳይንስ ሙዚየም “ዲጂታል ለልህቀት” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አውደ-ርዕይ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጎበኙ። ከጉብኝቱ በኋላ በሳይንስ ሙዚየሙ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በዶ/ር ታረቀኝ ዴአ በተመራው እና የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ አምዶችን ትኩረቱ ያደረገ የፓናል ውይይት ላይ በርካታ አበይት ርዕሰ-ጉዳዮች የተነሱ ሲሆን፣ በተለይም የመንግሥት ሠራተኞችን ክህሎትና ብቃት ማረጋገጥ የሚያስችል የብቃት ምዘና ሥርዓት መዘርጋት፣ ይበልጥ ውጤታማና ቀልጣፋ አሠራርን ለመፍጠር የሚያግዝ የመንግሥት አደረጃጀት አስተዳደር፣ እንዲሁም የሲቪል ሰርቪሱን ተቋማዊ ነጻነትና ገለልተኝነት ማረጋገጥ ስለሚቻልበት ሁኔታ በሰፊው ተዳስሰዋል። በተጨማሪም ሁሉንም ዜጋ አካታች ያደረገ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር የሚያስችሉ የብዝሃነትና አካታችነት ጉዳዮች፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያልመው የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ግንባታ፣ እና በተግባር ላይ የተመሠረቱ አሠራሮችን በመከተል ዋና ዋና የአገልግሎት መስጫ ዘርፎችን ለይቶ ማውጣትን የሚመለከተው የገቢር ነበብ አሰራርና የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያተኮሩ፣ ፍሬያማ ውይይት ተደርጎባቸዋል። የዚህ መሰሉ የዲጂታል አሠራርና የፓናል ውይይት መድረክ በሀገሪቱ የሲቪል ሰርቪስ ሥርዓት ውስጥ የሚታዩ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ክፍተቶችን ለመሙላትና ተቋማዊ ልህቀትን ለማምጣት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው የተገለጸ ሲሆን፤ የጉብኝቱም ዋነኛ ዓላማ ተቋማቱ በዲጂታል የሲቪል ሰርቪስ ዘርፍ ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግና የወደፊት የልህቀት ጉዟቸውን ለማጠናከር ያለመ ነው። በተጨማሪም ይህ መርሐ-ግብር የዩኒቨርሲቲው መምህራንና የሥራ ኃላፊዎች በሀገሪቱ የሪፎርም እና የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ላይ ያላቸውን ሚና ይበልጥ ለማሳደግ ተነሳሽነትን የፈጠረ እንደነበር ከውይይቱ ሂደት ለማወቅ ተችሏል፡፡
4 759
19
የኢፐሰዩ አመራሮችና ሰራተኞች በሳይንስ ሙዚየም የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አውደ-ርዕይን ጎበኙ+3
የኢፐሰዩ አመራሮችና ሰራተኞች በሳይንስ ሙዚየም የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አውደ-ርዕይን ጎበኙ
5 501
20
ኢፐሰዩ የፋሲሊቲና መሰረተ-ልማቶች  ጥገና እና ዕድሳት  ላይ ውይይት ተካሄደ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) የፋሲሊቲዎችንና መሰረተ-ልማቶችን ለማዘመን እንዲሁም ነባር ሕንጻዎችን ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ መልሶ ለመጠገን የሚያስችሉ የዲዛይንና ToR ግምገማ የምክክር መድረክ አካሄደ። በውይይት መድረኩ ላይም የዩኒቨርሲቲው አመራሮች ፣ የከተማ ልማትና ምህንድስና ኮሌጅ መሀንዲሶች፣ የፕሮጀክት ጽ/ቤት ባለሙያዎች፣ የስልጠና ባለሙያዎች፣ ስራ አስፈጻዎችና የሚመለከታቸው የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡ በውይይቱ መክፈቻ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ባደረጉት ንግግር፣ በ2018 በበጀት ዓመት በእድሳት ደረጃ የሕንጻ ማሻሻያ ሥራዎች እና ከነባር ግንባታዎች ማለትም የG+7 የስልጠና ማዕከል፣ የG+10 የመማሪያ ክፍሎች እና የወሊሶ ካምፓስ ግንባታዎች ተጠናክረው እየተሠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት ተጀምረው በመካሄድ ላይ ያሉ የሪኖቬሽን ሥራዎች አብዛኛዎቹ በዘንድሮው ዓመት የሚጠናቀቁ ሲሆን፣ አንዳንዶቹ ደግሞ በ 2019 በጀት ዓመት  እንደሚጠናቀቁ ጠቁመዋል። የዕለቱ የምክክር መድረክ በዋናነት በሁለት አጀንዳዎች ላይ ያተኮረ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ንጉስ፤ የመጀመሪያው ToR ተዘጋጅቶላቸው እና  ለአማካሪ ድርጅት ከተሰጡ በኋላ የመነሻ ዲዛይን የተሰራላቸው የማሰልጠና ክፍሎች፣ የሰልጣኞች መኖሪያዎች፣ የስልጠና ክፍሎች እና የመሰብሰቢያ አዳራሾችን የመማሪያ ክፍሎች ስማርት ለማድረግና የሕዳሴ አዳራሽ እንዲሁም የመመገቢያ አዳራሹን መልሶ ለመጠገን፣ የተሰራለቸውን ዲዛይኑ መገምገምና ጉድለቶችን መለየት እንዲሁም ሁለተኛው ደግሞ ገና ዲዛይን ያልተደረገላቸውን መልሶ ለመጠገን የሚያስችሉ የToR ሰነዶች ዝግጅት  ግብዓት መሰብሰብ እንደሆነ ጠቅሰዋል። እነዚህ የሪኖቬሽን ሥራዎች በሙሉ ከመንግስት ይሁንታና  ፈቃድ ያገኙ መሆናቸውም ገልጸዋል። "የስልጠና ክፍሎችን፣ የተማሪዎች ዶርሚተሮችንና አጠቃላይ ግቢውን አድሶ ማሻሻልና ዘመናዊ ማድረግ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት ነው" ያሉት ዶ/ር ንጉስ፣ መድረኩ በዋናነት የስልጠናና የመማሪያ ክፍሎችን እና ፋሲሊቲዎችን ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ እንዴት ስማርት ማድረግ እንደሚቻል የባለቤትነት ስሜት በተላበሰ መልኩ ግብዓት የሚሰበሰብበት መሆኑን አስገንዝበዋል። በመቀጠልም በአማካሪ ድርጅቱ ኦ ቦን ቮያጅ የተዘጋጀው የመነሻ ዲዛይን  ለታዳሚዎቹ የቀረበ ሲሆን፣ አማካሪው በዩኒቨርሲቲው ግቢ የሚገኙ 19 ሕንጻዎችን በጥልቀት በመገምገም መታረም የሚገባቸውን ጉድለቶች አሳይቷል። ድርጅቱ የመልሶ ጥገናና የሪኖቬሽን አስፈላጊነት ደረጃቸውን ከፍተኛ፣ መካከለኛ እና ዝቅተኛ በማለት የመደበ ሲሆን፤ በዚህም መሠረት የድህረ-ምረቃ ሕንጻ፣ የተማሪዎች ማደሪያዎች፣ የሰልጣኞች ማደሪያና የስልጠና ክፍሎች፣ እንዲሁም የአባይ የመሰብሰቢያ አዳራሽን ጨምሮ ሌሎች ህንታችንም በከፍተኛ ደረጃ አስቸኳይ እድሳት የሚያስፈልጋቸው መሆኑን በዝርዝር አቅርቧል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው መሰረተ ልማቶቹን ለማዘመንና ዲጂታላይዝ ለማድረግ የጀመረውን ጥረት አድንቀው፣ በቀጣይ ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት ያግዛሉ ያሏቸውን ስትራቴጂካዊ የሆኑ አስተያየቶችና ግብዓቶችን አበርክተዋል። በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ለተነሱት መሠረታዊ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከአማካሪው ድርጅት ተወካይና  ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። ዶ/ር ንጉስ ታደሰ በሰጡት ማጠቃለያም  የተከናወኑትን ተግባራት በአካባቢ ውበትና አረንጓዴ ልማት (ላንድስኬፕና ግሪነሪ) እንዲሁም በህንጻዎች ጥገናና ዕድሳት ዘርፍ በሁለት ከፍሎ መመልከት እንደሚገባ ጠቁመዋል። ሁሉንም የልማት ሥራዎች በአንድ ጊዜ ማከናወን የማይቻል በመሆኑ፣ በ2019 በጀት ዓመት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ሕንጻዎች ደረጃ በደረጃ በመለየት በእድሳት ሥራቸው ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሠራ አስገንዝበዋል። አክለውም፣ ነባር ሕንጻዎችን መልሶ የመጠገን ዓላማ ከተቋሙ  ራዕይና ተልዕኮ ጋር የተጣጣመ መሆኑንና ለወደፊት ዕድገትም የሚመጥን ዘላቂ አቅም መፍጠርንም ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የዕድሳት ሂደቱም የሕንጻዎቹን ውጫዊ ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ በውስጣቸው ሊኖሩ የሚገቡ የቴክኖሎጂ ግብዓቶችንና ፋሲሊቲዎችን በጥንቃቄ በማሟላት፣ ሙሉ በሙሉ ደረጃቸውን የጠበቁና የተሟላ አገልግሎት የሚሰጡ አድርጎ መገንባት አስፈላጊ በመሆኑ እዚህም ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
5 641