es
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

Ir al canal en Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

Mostrar más
1 161
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
photo content
+1

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለእምራይስ ድንግል ዘሞአቶ ለብርያል ዘሠናይ ገድል ወከለላ እምሰማይ አክሊል"። ትርጉም፦ ሰይጣንን በመልካም ገድል ድል የነሣችውና ከሰማይ የወረደ አክሊል የጋረዳት ለድንግል እምራይስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ "ሰላም ለእምራይስ ዘኀደገት ቀሱታ። ዘትቀድሕ ቦቱ ማየ ቀዳሜ ሕይወታ። ውስተ ዐውደ ስምዕ ትሑር ምስለ ሰማዕታት ሙቅሕታ። ሐየለት እምልሒቃን ወተለዓለት በሥርዓታ። እንዘ ዐሠርቱ ወክልኤቱ ክረምታ"። ትርጉም፦ ከሰማዕታት ጋር ታስራ ወደ ምስክርነት አደባባይ ትኼድ ዘንድ የሕይወቷ መዠመሪያ (ከሕይወት ዘመኗ አስቀድሞ) የሚኾን ውሃን የምትቀዳበትን ማድጋን የተወች ለኾነች ለእምራይስ ሰላምታ ይገባል፤ ዕድሜዋ ዐሥራ ኹለት ሲኾን ከታላላቆች በረታች፤ በሕጓም ከፍ ከፍ አለች። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር14። https://t.me/Eotcw

photo content
+2

ካላሳየኸኝ እኔ ወደ ዱር እሄዳለሁ፣ አራዊትም ይበሉኛል" ብላ ላከችበት፡፡ ቅዱስ አርከሌድስም እናቱ ካላየችው እንደማትተወው እርሱም ለእግዚአብሔር የገባውን ቃልኪዳን ማፍረስ እንደማይቻለው ባወቀ ጊዜ ነፍሱን እንዲወስዳት ወደ ጌታችን ለመነ፡፡ ከዚህም በኋላ የበሩን ጠባቂ "እናቴን ወደእኔ ትገባ ዘንድ ፍቀድላት" አለው፡፡ እናቱም ወደ ውስጥ በገባች ጊዜ ልጇን ቅዱስ አርከሌድስን ሙቶ አገኘችውና በታላቅ ድምፅ በመጮህ አለቀሰች፡፡ የእርሷንም ነፍስ ይወስድ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነች፡፡ ጌታችንም ልመናዋን ተቀብሎ ነፍሷን ወሰደ፡፡ ❤ እናትና ልጅም በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ካረፉ በኋላ የሁለቱን ሥጋቸውን ለይተው ሊቀብሯቸው ሲሉ የቅዱስ አርከሌደስ በድን በሰው አንደበት መናገር ጀመረ፡፡ "የእናቴን ሥጋ ከሥጋዬ አትለዩ በሕይወቷ ሳለች ታየኝ ዘንድ ልቧን ደስ አላሰኘሁምና" የሚል ቃል ከአርከሌድስ በድን ወጣ፡፡ ይህንንም ቃል በሰሙ ጊዜ እጅግ አድንቀው እግዚአብሔርን ካመሰገኑት በኋላ ሁለቱንም ድ መቃብር ውስጥ ቀበሯቸው፡፡ ጌታችንም ለበሽተኞች ታላቅ ፈውስን ከሥጋ ገለጠ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አርከሌድስ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 14 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ፍኖተ ጽድቅከ አብደርኩ። ወኵነኔከሰ ኢረሳዕኩ። ተለውኩ ስምዐከ እግዚኦ ኢታስተኀፍረኒ"። መዝ 118፥30። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥28-32። + + + ❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን"። መዝ 83፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 2፥1-3፣ 1ኛ ዮሐ 5፥1-13፣ የሐዋ ሥራ 10፥34-39። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 2፥1-14። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ አረጋዊ የልደትና የአቡነ አካለ ክርስቶስ የመታሰቢያ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፲፬ (14) ቀን። ❤ እንኳን ጠምህዋ ከሚባል አገር ሰዎች ለሆነች በ12 ዓመቷ በከሀዲው ንጉሥ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን ፍልፍልያኖስ በሚባል መኰንን እጅ በጊንጦች እፋኝቶችንና እባቦችን ሰብስበው በዳውላ ውስጥ ጨምረው በዚህ ሰማዕትነት ለተቀበለች ለቅድስት ምህራኤል ለዕረፍት በዓል፣ ለታላቋ ሰማዕት ለከበረች ለቅድስት እምራይስ ለዕረፍቷ በዓልና በገድል ለተጠመደ የሴት ፊት ሳያይ ለኖረ ለከበረ አባት ለአባ አርከሌድስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡ፦ ከከበረ ሕፃን ከቅዱስ ቂርቆስ ማኅበር ከሆኑ አራት ሽህ ሠላሳ አራት ጭፍሮች በሰማዕትነት ከዐረፉና ከቅዱስ ዱማቴዎስ ወንድም ከከበረ ከቅዱሴ መክሲሞስ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ የዚህ ሳምንት መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፫ "ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ እንዘ ይገብረ ተአምረ ወመንክር በውስተ አሕዛብ፤ ሖ አዝ፣ አርአዮሙ ስብሐቲሁ አምኑ ቦቱ አርዳኢሁ፤ ሖ አዝ፣ ወይቤሎሙ ቅድሑ ማየ ወምልእዎን ለመሳብክት እስከ አፉሆን፤ ሖ አዝ፣ ጥዒሞ አንከረ ሊቀ ምርፋቅ በረከተ ዘአምላከ ገብረ፤ ሖ አዝ፣ ቤዛነ ተስፋነ ወልደ አምላክ ወለማይኒ ረሰዮ ወይነ"። ትርጉም፦ ኢየሱስ ክርስቶስ በደስታ ወደ ሠርግ ቤት ሔደ በብዙ ሕዝብ መካከል ድንቅ ተአምርን ሊሠራ ሔደ ደቀ መዛሙርቱም ክብሩን ተአምራቱን አይተወሸ አመኑበት። ውሃም ቀድታችሁ ጋኖቹን እስከ አፋቸው ሙሏቸው። የጠጅ አሳላፊው አምላክ ከሠራው በረከት ቀምሶ አደነቀ። ቤዛች ተስፋችን የእግዚአብሔር ልጅ ውሃው ወይን አደረገ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። + + + ❤ ቅድስት እምራይስ፦ ይቺም ብፅዕት በክርስቶስ ሃይማኖት ለጸኑ ለከበሩ አባቶች ልጅ ናት ፈሪሀ እግዚአብሔርንም እየተማረች አደገች። በአንዲትም ዕለት ውኃ ልትቀዳ ወደ ወንዝ ስትወርድ ስለ ክርስቶስ የታሠሩ እሥረኞችን አየች እነርሱም ጳጳሳት ቀሳውስትና ዲያቆናት ናቸው ከእርሳቸውም ጋር ስሟን ይጽፍ ዘንድ መዝጋቢውን ለመነችው መዘገባትም ወደ ከሀዲውም መኰንን ወደ ቊልቁልያኖስ አቀረባት። እርሱም ለጣዖት ትሰግድ ዘንድ ብዙ ነገር ሸነገላት እምቢ ባለችም ጊዜ ቸብቸቦዋን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ከተባባሪዎቿም ጋር ምስክርነቷን ፈጸመች። ለእግዚአብሔርም ምስጋና የሰማዕታት በረከቷም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ ቅድስት ምህራኤል፦ የዚችም ቅድስት ወላጆቿ እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ክርስቲያኖች ናቸው የአባቷም ስሙ ዮሐንስ የሚባል ቄስ ነው እናቷም ኢላርያ የምትባል ደግ ናት። ነገር ግን ልጅ ስለሌላቸው ስለዚህ እያዘኑ ወደ እግዚአብሔር ይለምኑ ነበር ከብዙ ዘመንም በኋላ ይህችን የከበረች የተቀደሰች ልጅ ተሰጠቻቸው ስሟንም ምህራኤል ብለው ጠርዋት። ዐሥራ ሁለት ዓመትም በሆናት ጊዜ በላይዋ በአደረ መንፈስ ቅዱስ ስጦታ ድንቆች ተአምራቶችን መሥራት ጀመረች። ❤ ከዚህም በኋላ ከሀዲ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ በተነሣ ጊዜ ወደ ባሕር ዳርቻ ወጣች መርከብም አግኝታ በላዩ ተሳፈረች ለሰማዕትነት ከሚሔዱት ጋር በመሔድ ወደ እንጽና ከተማ በደረሰች ጊዜ ስሙ ፍልፍልያስ በሚባል መኰንን ፊት ቆመች በአያትም ጊዜ ስለታናሽነቷ ራርቶላት ሊተዋት ወደደ። ሊተዋትም እንደወደደ ዐውቃ እርሱንና የረከሱ አማልክቶቹን በድፍረት ረገመች። ስለዚህም መኰንኑ ተቆጥቶ ጽኑዕ የሆነ ሥቃይን አሠቃያት ከቀናች ሃይማኖቷ ሸንግሎ ይመልሳት ዘንድ በተሳነው ጊዜ ጊንጦችን፣ እፉኝቶችንና እባቦችን ሰብስበው በዳውላ ውስጥ እንዲጨምሩአቸው እርሷንም ከእርሳቸው ጋር በዳውላ ውስጥ እንዲጨምሩት አጥማጆችን አዘዛቸው እነርሱም እንዲሁ አደረጉ። ❤ ያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጸላትና ከጌታችን ዘንድ የተሰጣትን ቃል ኪዳን አስረከባት ከዚህም በኋላ ነፍሷን አሳረፈች የምስክርነት አክሊልንም ተቀበለች ከዳውላውም ውስጥ አውጥተው በዚያች ቦታ ቀበሩዋት። ከዚህም በኋላ አባቷና እናቷ በሰሙ ጊዜ ሥጋዋ ወዳለበት ከብዙ ሕዝብ ጋር መጡ ከዚያም ሥጋዋን አፈለሱና ወሰዱአት በታላቅ ክብርም ገንዘው በአማረች ሣጥን ውስጥ አኖሩዋት በሥውር ቦታም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠሩላት ከእርሷም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ምህራኤል በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ አርኬሌድስ፦ ይህም ቅዱስ ከሮሜ አገር ከታላላቆች ወገን ነው የአባቱም ስም ዮሐንስ የእናቱም ስም ሰንደሊቃ ነው ሁለቱም ዕውነተኞች የሆኑ በእግዚአብሔር ሕግ ያለ ነቀፋ የጸኑ ናቸው። ቅዱስ አርከሌድስም ዕድሜው ዐሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ አባቱ ሞተ እናቱም ሚስት ልታጋባው አሰበች እርሱ ግን ይህን አልወደደም። አባቱ በሕይወት ሳለ ንጉሡ የሾመው ነበርና እናቱ አሁንም ወደ ንጉሡ ሄዶ የአባቱን ሹመት ይቀበል ዘንድ አርከሌድስን መከረችው፡፡ ለንጉሡ የሚሰጥ እጅ መንሻንና አገልጋዮችን አድርጋ ብዙ ገንዘብ አስይዛ ላከችው፡፡ እርሱም በመርከብም ተጭኖ ሲሄድ ታላቅ ንፋስ ተነሣና ማዕበሉ አየለባቸው፡፡ መርከቡም ተሰበረ፡፡ ❤ ቅዱስ አርከሌድም አንዲት የመርከብ ስባሪ ሠሌዳ ላይ ተንጠልጥሎ ወደ የብስ ደረሰ፡፡ ከባህሩ ሲወጣ ማዕበል የተፋው አንድ በድን አገኘና ተቀምጦ ስለ በድኑ አለቀሰ፡፡ የዓለምን ኃላፊነትና እርሱም ከሞተ በኋላ አፈርነቱን አሰበ፣ ነፍሱንም ገሠጻት፡፡ ወደ ቀና መንገድ ይመራውም ዘንድ ወደ ጌታችን ለመነ፡፡ ረጅም መንገድ ተጓዘና ሶርያ ውስጥ በቅዱስ ሮማኖስ ስም ወደተሠራች አንድ ተራራማ ገዳም ደረሰ፡፡ ከገንዘቡም ከእርሱ ጋር የቀረውን ሁለት መቶ የወርቅ ዲናር ለአበ ምኔቱ ሰጠው፡፡ እንዲያመነኩሰውም ጠየቀው፡፡ መጀመሪያውኑ አርኬሌድስ ከመምጣቱ በፊት ለአበምኔቱ መንፈስ ቅዱስ የመምጣቱን ነገር አስረድቶት ነበርና እርሱ በደረሰ ጊዜ ደስ አለው፡፡ መነኰሳቱም ሁሉ ከጸለዩለት በኋላ አመነኰሰው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ የከበረ አርከሌድስ ጽኑ ተጋድሎ መጋደል ጀመረ፡፡ ሲጸልይ ይውላል ሲጸልይ ያድራል፤ ሁልጊዜ በየሰባቱ ቀን የሚጾም ሆነ፡፡ እግዚአብሔርም ሀብተ ፈውስን ሰጥቶት ብዙ ሕመምተኞችን ፈወሳቸው፡፡ ከዚህም በኋላ የሴቶችን ፊት ከቶ እንዳያይ ከጌታችን ጋር ቃል ገባ፡፡ እናቱም ለ12 ዓመት ያህል የልጇን ወሬ ምንም ስላልሰማች በእርሱ የሆነውን አላወቀችም ነበርና የሞተም ስለመሰላት እጅግ አዘነች፡፡ የእንግዶችና የመጻተኞች መቀበያ የሚሆን ቤት ሠርታ የመንገደኞች ማደርያ አደረገችው፡፡ ❤ በአንዲት ዕለት ያሳደረቻቸው እንግዶች የቅዱስ አርከሌድስን ዜና ሲናገሩ ሰማቻቸው፡፡ እንግዶቹም ስለ ቅድስናው፣ ስለ ተጋድሎው የሚያሳያቸውን ምልክቶችና ተአምራቶቹን፣ የመልኩንም ደም ግባት ሲነጋገሩ ሰምታ ልጇ እንደሆነ ዐወቀች፡፡ መንገደኞቹንም ስለ ሥራው ጠየቀቻቸውና ሥራውን ሁሉ ነገሯት፡፡ ልጇ በሕይወት እንዳለና ሕያው እንደሆነ ተረዳች፡፡ በዚያን ጊዜ ተነሥታ ወደ ከበረ ሮማኖስ ገዳም ሄደች፡፡ ወደ ልጇዋ ወደ ቅዱስ አርከሌድስ "እነሆ ፊትህን አይ ዘንድ ወድጄ እኔ እናትህ መጥቻለሁ" ብላ መልእክት ላከች፡፡ ልጇ ቅዱስ አርከሌድም "ከቶ የሴቶችን ፊት እንዳላይ ከክብር ባለቤት ከባለቤት ከጌታዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ቃል ገብቻለሁና ቃልኪዳኔን ማፍረስ አይቻለኝም" ብሎ መልሶ ወደእርሷ ላከ፡፡ እናቱም "ፊትህን

photo content
+3

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፲፬ (14) ቀን። ❤ እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ለአቡነ አካለ ክርስቶስ ዘቤጌምድር ለበዓላቸው መታሰቢያ በዓል፣ ከዘጠኙ ቅዱሳን አንዱ ለሆኑት ለዘሚካኤል በሚሰሩት ስራቸው አረጋዊ ለተባሉት ለታላቁ አባት ለአቡነ አረጋዊ ለልደታቸውና ደብረ ደሞ ለወጡበት ቀን ዓመታዊ መታሰቢያ በዓልና ለቊስጥንጥንያ ንጉሥ ለቴዎዶስዮስ ልጅ ለሙሽራወ ለቅዱስ ለገብረ ክርስቶስ ለበዓሉ መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። + + + ❤ "ሰላም ለአባ አረጋዊ ምንኵስናሁ ዘፈጸመ፤ በፍኖተ ጽድቅ ዘቆመ። ሰላም ለገብረ ክርስቶስ ብእሴ እግዚአብሔር ለነፍሱ ዘኮነ ኬንያ ዘአብዕዎ መላእክት ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ እንዘ ይብሉ ሃሌ ሉያ"። ትርጉም፦ በእውነት ጐዳና የቆሞ ኾኖ ምንኩስናውን ፍጹም ላደረገ ለአባ አረጋዊ ሰላምታ ይገባል። ሃሌ ሉያ እያሉ ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት መላእክት ያስገቡት ለነፍሱም ጠቢብ የእግዚአብሔር ሰው ለኾነ ለገብረ ክርስቶስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ አቡነ አካለ ክርስቶስ ዘቤጌምድር፦ ከአባታቸው ከገላውዴዎስ ከእናታቸው ወለተ አዳም ጌታችን በተወለደበት ዕለት ታኅሣሥ 29 ቀን ተወለዱ። በተወለዱም ጊዜ ሙት አስነሥተዋል። የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ሲሆኑ በ21 ዓመታቸው ነው በሐይቅ እስጢፍኖስ ገዳም የመነኰሱት። ዘገብርኤል የተባለ በስሙ አሳሳች የሆነ ጣዖት አምላኪ ለጣዖት አልሰግድም ቢሉ ወስዶ በእጅጉ አሠቃቷቸዋል። በ6 ችንካሮች ቸንክሮ ሲያሠቃያቸው ጌታችን ተገልጦላቸው እንደ ጊዮርጊስ ጽና ብሎ ተስፋውን ሰጥቷቸዋል። ❤ ጻድቁ አገራቸው ጋይንት ሲሆን በዚሁ አካባቢ ምዕራፈ ቅዱሳን በተባለው ቦታ አንድ የወይራ ዛፍ ተደግፈው ሳይንቀሳቀሱ 40 ዓመት ቆመው የጸለዩበት ወይራ ዛፍ ዛሬም በገዳሙ ተከብራ ትኖራለች። ቤተ መቅደሱ ሳይታጠን የቀረ እንደሆነ ወይም ዲያቆኑ መብራት ሳያጠፋ የሄደ እንደሆነ የጻድቁ መቋሚያቸው እንደ ሰው አፍ አውጥታ ታቃጭላለች። ያበደ ሰው በመቋሚያዋ 7 ጊዜ ቢተሻሽባት ይድናል። በአካባቢው ብዙ መርዛማ እባቦች ቢኖሩም የአቡነ አካለ ክርስቶስን ስም ከተጠራባቸው ምንም ጉዳት አያደርሱም። በሌላም ቦታ ሆኖ እባብ የነደፈው ሰው እምነታቸውን ከተቀባ ጸበላቸውን ከጠጣ ፈጥኖ ይድናል። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

photo content

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለ፯ቱ ደቂቅ እለ ኀብኦሙ እግዚአብሔር ውስተ በኣት ወወሀቦሙ ንዋመ ጥዑመ እስከ ፫፻፸ወ፪ ዓመት፤ እለ አስማቲሆሙ አርከሌዶስ ዲኦሚዶስ አውጋንዮስ፣ ድሜጥሮስ፣ በርናጥዮስ፣ ከእስጢፋኖስ፣ ኪራኮስ ሰማዕታት እለ ክርስቶስ"። ትርጉም፦ እግዚአብሔር በዋሻ ውስጥ የሰወረራቸው፤ እስከ 372ዓመት ድረስ ጥዑም እንቅልፍን የሰጣቸው በክርስቶስ ሰማዕት ለኾኑ ስማቸው አርከሊዶስ ዲኦሚዶስ አውጋንዮስ፣ ድሜጥሮስ፣ በርናጥዮስ፣ ከእስጢፋኖስ፣ ኪራኮስ ለኾነ ለሰባቱ ሕፃናት ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። https://t.me/Eotcw

photo content

የሚያገለግሉት ሴቶች መነኰሳይያት በንጽሕና በቅድስና የሚኖሩበት ታላቅ ገዳም ነው፡፡ ዛሬ ላይ በኤርትራ ያለውም የቅድስት ዴሚያና ገዳም እንዲሁ ሴቶች ደናግል መነኰሳይያት ብቻ የሚኖሩበት ቤተ ደናገል ገዳም ነው፡፡ ከሰማዕቷ ከቅድስት ዴሚያና እንዲሁም ከአርባው ደናግል ሰማዕታት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከታቸው ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!፡፡ (ምንጭ፦ የሰማዕቷን ታሪክ እኅታችን መምህርት ዘውዴ እንደጻፈችው።) ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ ቅዱስ ማርቆስም ሐምሌ ስምንት ቀን ሰማዕትነት ከመቀበሉ በፊት አስቀድሞ ጌታችንን ስለ ስሙ መስክሮ በሰማዕትነት እንዲሞት ስለፈቀደለት እጅግ አድርጎ ያመሰግነው ነበር፡፡ ዲዮቅልጥያኖስም ታማኝ ሹመኛው ነበርና ቅዱስ ማርቆስን ካስገደለው በኋላ መጸጸትና መናደድ ጀመረ፣ ቅዱስ ማርቆስም በመጀመሪያ እሽ ብሎት ወደ ጣዖት አምለኮው ከገባለት በኋላ እንደገና በክርስቶስ ወደማመን ተመልሶ እስከሞት ድረስ ለመታመን የቻለው በልጁ በቅድስት ዴሚያና ምክንያት እንደሆነ አጣርቶ ደረሰበት፡፡ እርሷም አባቷን አስተምራ አሳምና ለሰማዕትነት እንዳበቃችው ሲሰማ ዲዮቅልጥያኖስ የት እንዳለች ከጠየቀ በኋላ በአስቸኳይ ይዘው እሽ ካለች እንዲያከብሯት፣ ነገር ግን ለጣዖታቱ ካልተገዛች አሰቃይተው እንዲገድሏት በማዘዝ አንዱን መኰንን ከመቶ ጭፍሮች ጋር ላከው፡፡ የተላከው መኰንንም ጭፍሮቹን አስከትሎ ሔዶ ቅድስት ዴሚያናን አገኛትና በንጉሡ ትእዛዝ መሠረት ለጣዖታት እንድትሰግድ ሲጠይቃት እርሷም "ሰማይንና ምድርን፣ ውቅያኖስንና በውስጡ ያሉትን ሁሉ ከፈጠረ ከአንድ እግዚአብሔር ከአብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ በቀር ሌላ አምላክ የለም…" በማለት በእምነቷ ጸናች፡፡ ሐሳቧንም እንድትለውጥ የዲዮቅልጥያኖስ መኰንን ብዙ ጊዜ ሲያባብላት እርሷም እስከመጨረሻው በእምነቷ ስለጸናች መኰንኑ እጅግ ተበሳጭቶ ከዓሥር በላይ የተለያዩ መከራዎችን አደረሰባት፡፡ ❤ በመጀመሪያ በድንጋይ መጭመቂያ መሣሪያ ጨምቀው አሰቃዩዋት፣ ደሟም በምድር ላይ እንደውኃ ፈሰሰ፣ ነገር ግን ቅድስት ዴሚያና እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ለገዳዮቿ ምሕረትን ትለምን ነበር፡፡ ጭፍሮቹም በእሥር ቤት ጥለዋቸው ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦላት ሰውነቷን በመዳደድ ከቊስሏ ፈወሳትና ምንም እንዳልነካት ሆነች፡፡ በቀጣዩ ቀንም ሞታ እንደሆን ለማየት መኰንኑ ሲመጣ እንደቀድሞው ደኅና ሆና አገኛት፣ ይህንንም አይተው በቅድስት ዴሚያና አምላክ ያመኑትን በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ገድላቸውና የሰማዕትነት ክብርን ተቀዳጁ፡፡ ❤ ዳግመኛም መኰንኑ የቅድስት ዴሚያናን ሰውነት በተሳለ ብረት እንዲፈቀፍቁት አዘዘና ሥጋዋን ፋቋት፣ በዚኽም ሳያበቁ እንደገና በፈቀፈቋት ሰውነቷና በቊስሏ ላይ የሚያቃጥል አሲድና ኮምጣጤ ጨምረው አሰቃዩአት፤ እርሷ ግን በዚህ ሁሉ ትደሰትና ታመሰግን ነበር፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ለኹለተኛ ጊዜ በእሥር ቤት ውስጥ ሳለች ተገልጦላት ፈወሳት፡፡ ይኽንንም ተኣምር ያዩ በርካታ ሰዎች በቅድስት ዴሚያና አምላክ አመኑ፡፡ መኰንኑም እንደገና በታላላቅ የብረት መዶሻ እንዲመቷት አዘዘና ከመሬት ላይ ወድቃ መነሣት እስከማትችል ድረስ በኀይል በብረት መዶሻ ቀጠቀጧት፡፡ ዳግመኛም መኰንኑ በዚህ አልበቃ ብሎት በቲአትር መመልከቻ አደባባይ ላይ አውጥቶ በላይዋ ላይ ቅባት ካፈሰሱባት በኋላ በእሳት አቃጠሏት፣ እሳቱም ወደላይ እስኪወጣ ድረስ ዕንጨት በመጨመር ቢቃጥሏትም ቅድስት ዴሚያና ግን ልዑል እግዚብሔርን ታመሰግን ነበር፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ለሦስተኛ ጊዜ መጥቶ ከዚህ መከራ አዳናት፡፡ ይኽንንም ታላቅ ተአምር ያዩ ሁሉ በጌታችን አምነው ስለ ስሙ መስክረው በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ❤ ዳግመኛም መኰንኑ "…ይሄ ሁሉ ሕዝብ በአንቺ ምክንያት ሲሞት አንቺ ግን ፊትሽ በደስታ ያበራል" እያለ ሲዘልፋት እርሷ ግን "…ለክርስቶስ መሥዋዕት አድርጌ ያቀረብኳቸው ናቸው" አለችው፡፡ በዚኽም ጊዜ የራሷን ቆዳ በስለታማ ብረት እንዲላጩትና የፈላ ዘይትና አሲድ እንዲጨምሩበት ጭፍሮቹን አዘዛቸው፣ እንደታዘዘውም አደረጉባትና አሰቃዩአት፡፡ ዳግመኛም ዐይኖቿን እንዲያወጡት አደረገ፤ የመላ ሰውነቷንም ቆዳ እንዲገፉት አደረገና የፈላ ዘይት እንዲጨምሩበት አዘዘ፡፡ ቅድስት ዴሚያናም በዚህ ሁሉ መከራ ውስጥ እያለች የእግዚአብሔርን ምስጋና አላቋረጠችም ነበር፡፡ ❤ በዚህም ጊዜ ጌታችን በሕዝቡ ሁሉ ፊት ከመከራውና ከሕማሙ ሁሉ ፈወሳት፡፡ ለአራተኛም ጊዜ ይህን ተኣምር የተመለከቱ ሁሉ በጌታችን አምነው በሰማዕትነት ዐርፈው የክብር አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ መኰንኑም ለአምስተኛ ጊዜ በእሥር ቤት ውስጥ አሠራት፡፡ በማግስቱም እየተሽከረከረ ከሚዞር ብረት ጋር አጣብቀው እንዲቸነክሯትና በዚያም አካሏ እስከሚበታተን ድረስ እንዲያሰቃዩአት አዘዘ፤ በትእዛዙም መሠረት ከሰውነቷ ጋር የታሰረውን ስለት ያለው የብረት ማጣበቂያ ጎተቱትና አጥብቀው ሲቸነክሯት ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለየች፡፡ ❤ መኰንኑም ከተኣምራቷ የተነሣ ከሞት ልትነሣ ትችላለች ብሎ ሥጋዋን እንዲበሉት ለዱር አራዊት ሰጠው፡፡ ነገር ግን ወዲያው ከሰማይ ታላቅ የነጎድጓድ ድምፅ ተሰማ፣ በዚያ የነበሩ ሰዎችም ተፍገምግመው ወደቁ፣ እንደሞቱም ሆኑ፡፡ ወዲያውም የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሠራዊተ መላእክት ታጅቦ ክብርት እመቤታችን በቀኙ ሆና በታላቅ ግርማ ወረደና የቅድስት ዴሚያና አካሏ ወደተበላበት ተመለከተና "የተባረክሽ ልጄ ዴሚያና ሆይ! ተነሺ" በማለት ሲያዝ ወዲያው በአራዊት ተቆራርጦ የተበላው አካሏ ተሰበሰበ፣ ዴሚያናም ከእንቅልፏ እንደምትነሣ ፈጥና ተነሣችና ከሞት ካስነሣት አምላኳ እግር ሥር ወድቃ ሰገደችለት፡፡ ጌታችንም ሦስት አክሊላትን ካቀዳጃትና ቃልኪዳን ከገባላት በኋላ በዚያ ቦታ ላይ በስሟ ቤተ ክርስቲያን እንደሚሠራ ነግሯት በክብር ዐረገ፡፡ ❤ ከዚኽም በኋላ ቅድስት ዴሚያና ፈጥና ወደ መኰንኑ ዘንድ ሔዳ "ጌታዬ መድኀኒቴ ከሞት አስነሣኝ…" ብላ መሰከረች፡፡ ስትሞት ያዩዋትም ሁሉ አሁን ላይ ድጋሚ ቆማ ስትመሰክር ሲያዩዋት እጅግ ተገርመው በአምላኳ በክርስቶስ አምነው መስክረው እነርሱም በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ መኰንኑም የሽንፈትና የሐፍረት ስሜት ስለተሰማው ጭፍሮቹን ሰብስቦ የቅድስት ዴሚያናን አንገት በሰይፍ ቆርጠው ወደ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ በቶሎ እንዲመለሱ ተማከሩ፡፡ ከዚኽም በኋላ ቅድስት ዴሚያና እና አርባው ደናግል እንዲሁም በክርስቶስ ያመኑት ሁሉ እንዲገደሉ ደብዳቤ ጻፈ፡፡ በዚኽም መሠረት ሁሉንም ይዘው ከከተማው አውጥተው በሰይፍ ሰየፏቸው፡፡ በቅድስት ዴሚያና አምላክ ያመኑ 400 ሰዎችም በሰማዕትነት ዐርፈው ለክብር በቁ፡፡ የቅድስት ዴሚያናም ዕረፍቷ ጥር 13 ቀን ተፈጸመው፡፡ ❤ የንግሥት ዕሌኒ ልጅ ደገኛው ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሲነግሥ አብያተ ክርስቲያናትን አስከፍቶ ክርስቲያኖችን ከእሥር አስለቅቆ የተሰደዱትንም መልሶ አከበራቸው፡፡ ንግሥት ዕሌኒም ስለ ቅድስት ዴሚያና ተጋድሎና ስለተቀበለችው መከራ ስትሰማ ከእርሷ በረከትን ታገኝ ዘንድ የሰማዕታቱ ቅዱስ ሥጋቸው ወዳለበት ቦታ ሔደች፡፡ የሰማዕታቱም ሥጋቸው ምንም ሳይሆን በክብር ተቀምጦ አገኘችና የሁሉንም በተለይም የቅድስት ዴሚያናንም ቅዱስ ሥጋዋን በክብረ ልብስ ጠቅልላ በልዩ መቃብር ውስጥ አስቀመጠችውና ታላቅ ቤተ ክርስቲያን አሠራችላቸው፤ ግንቦት 12 ቀንም ቅዳሴ ቤታቸው ተከበረ፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ድንቅ ድንቅ ተኣምራት ተገልጠው ታዩ፡፡ ❤ ለቅድስት ዴሚያና ወላጅ አባቷ ቅዱስ ማርቆስ መጀመሪያ ላይ ባሠራላት ቤተ መንግሥት በኋላም እርሷ ወደ ገዳምነት የቀየረችው ቤት ዛሬ ላይ ግብፅ ውስጥ የሰማዕታቱ ቅዱስ ዐፅማቸው ያረፈበት ታላቅ ገዳም ሆኗል፡፡ ገዳሙ "የቅድስት ዴሚያና የሴቶች አንድነት ገዳም" የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን የእርሷን ፈለግ የተከተሉ ክርስቶስን በድንግልና

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፲፫ (13) ቀን። ❤ እንኳን ለታላቋ ሰማዕት ቅድስት ዴ (ድ)ሚያናና ከእርሷ ጋር አብረው ሰማዕትነት ለተቀበሉ ለአርባው ደናግል ለዕረፍቸው መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። + + + ❤ ሰማዕቷ ቅድስት ዴ (ድ)ሚያና፦ ይኽችም ቅድስት ዴሚያና በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጨረሻ የተወለድችና በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ክርስቲያኖችን በአስከፊና በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገድል በነበረው በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን የነበረች በእርሱም እጅ በጭካኔ ዐሥር ጊዜ እጅግ አሠቃቂ የሆኑ መከራዎችን በመቀበል በመጨረሻም ከተከታዮቿ ከ40 ደናግል ሰማዕታት ጋር አንገቷን የተሰየፈች ታላቅ ሰማዕት ናት፡፡ ❤ ኤርትራ ውስጥ ወደሚገኘው ቅድስት ዴሚያና የሴቶች ገዳም (ቤተ ደናግል) ስንሔድ መጀመሪያ ላይ ያጋጠመንና ያስገረመን ነገር መነኰሳይያቱ በጣም ወጣት ሆነው ብዛት ያላቸው መሆኑ ነው፡፡ ገዳሙ ቤተ ደናግል ነው፣ ማለትም ድንግል የሆኑ ሴቶች ብቻ የሚኖሩበት ገዳም ነው፡፡ እንግዳን ለመቀበል የነበራቸው ጉጉትና ፍቅር፣ ትሕትናቸው፣ ትጋታቸው ሁሉ እውነትም ሰማዕቷን ድንግል ዴሚያናንና አርባውን ደናግል ሰማዕታት አስመስሏቸዋል፡፡ገዳሙ ያለበት ቦታ ከተማው ላይ ከእንዳ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ብዙም ሳይርቅ ነው፣ ከአጠገቡም የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ይገኛል፡፡ ❤ ገዳሙ አሁን ያለበት ቦታ በመጀመሪያ የግለሰብ ቤት እንደነበር የነገሩን መነኰሳይያቱ ናቸው፡፡ ሰማዕቷ ቅድስት ዴሚያና በቦታው ላይ ትኖር ለነበረችው አንዲት ሕዝባዊት እናት ተገልጣላት ቦታው ወደፊት ቤተ ደናግል እንደሚሆን ስለነገረቻት ያችም እናት ቤቷን ለሰማዕቷ ቤተ ክርስቲያን እንዲሆን ሰጠች፡፡ ዳግመኛም ቅድስት ዴሚያና ለአንዲት ድንግላዊት ተገልጣላት ወደ ግብጽ ሔዳ መንኵሳ እንድትመጣና ገዳሙን ገድማ ለደናግል መነኰሳይያቱ እመ ምኔት እንድትሆን ነገረቻት፡፡ በዚኽ መሠረት ነው ገዳሙ ተስፋፍቶ ቤተ ደናግል ለመሆን የበቃው፡፡ ስያሜውም በትግርኛ "ገዳም ደብረ ደናግል ሰማዕት ቅድስት ድምያና ምስ 40 ደቃ" ተባለ፡፡ ❤ የሰማዕቷ የቅድስት ዴሚያና አባቷ ማርቆስ የከሃዲው ንጉሥ የዲዮቅልጥያኖስ ሹመኛ ሆኖ በግብፅ ሁለት ግዛቶችን ያስተዳድር የነበረ ቢሆንም እርሱና ቤተሰቡ ግን ክርስቲያኖች ነበሩ፡፡ እናቷ ገና በልጅነቷ ስለሞተች አባቷ ቅድስት ዴሚያናን ከልጅነቷ ጀምራ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንድታውቅ ሃይማኖት እንድትማር አድርጎ በንጽሕና አሳደጋት፡፡ እርሷም ከልጅነቷ ጀምራ መጽሐፍ ቅዱስንና የቅዱሳንን ሕይወት እያነበበች አደገች፡፡ ❤ ቅድስት ዴሚያናም 15 ዓመት በሆናት ጊዜ በከተማው የታወቀ አንድ ሰው ሊያገባት ፈለገ፣ አባቷም ይህንን ሲያማክራት እርሷ ግን "…እኔ የክርስቶስ ሰማያዊ ሙሽራ ለመሆን ራሴን ለክርስቶስ ሰጥቻለሁ" በማለት ጋብቻውን በጽኑ ተቃወመች፡፡ ከዚኽም በኋላ ከከተማ ውጭ ባለው በረሓ ውስጥ በሰሜናዊ አቅጣጫ የምትኖርበትን ቤት ይሠራላት ዘንድ አባቷን ጠይቃ ሲሠራላት ቤቱን የጸሎት ቤት አደረገችው፡፡ በኋላም ቅድስት ዴሚያና ያንን አባቷ ያሠራላትን ቤተ መንግሥት የመሰለ ቤቷን ወደ ገዳምነት ቀየረችውና ከደናግል ጓደኞቿ ጋር በአንድነት መኖር ጀመረች፡፡ እርሷም ለደናግል ጓደኞቿ ጌታችንን ስለማመን ታስተምራቸውና ታበረታቸው ነበር፡፡ እነርሱም በጾም በጸሎት፣ ቅዱሳት መጻሕፍን በማንበብ፣ የዳዊት መዝሙርን በመዘመር፣ የእጅ ሥራንም በመሥራት እየተጉ መንፈሳዊ ሕይወታቸው ሌሎቹን ደናግል እየማረከ ስለመጣ ቊጥራቸው 40 እስኪሆኑ ድረስ ተሰባሰቡ፡፡ ❤ ከዚኽም በኋላ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ በ284 ዓ.ም ከነገሠ በኋላ ክርስቲያኖችን ሁሉ ከያሉበት እያስፈለገ ይገድል አብያተ ክርስቲያናትንም ያጠፋ ጀመር፡፡ ዲዮቅልጥያኖስ ከነገሠና ከካደ በኋላ ወርቅ አቅልጦ 35 የወንድና 35 የሴት ጣዖታትን አሠርቶ ሰው በሚመላለስበት አደባባይ ላይ በማቆም ሁሉም ለጣዖታቱ እንዲሰግድ አዋጅ አስነገረ፡፡ በዘመኑም ለጣዖታቱ ያልሰገዱትንና ክርስቶስን በማመን የጸኑትን ሁሉ በዓለም ላይ ያሉ ከ470 ሺህ በላይ ክርስቲያኖችን በግፍ በሰማዕትነት አስገደለ፡፡ ቅድስት ዴሚያናም ከ40 ቅዱሳት ደናግል ጋር በምናኔ ላይ ሳለች ነው ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ በሰይጣን ታግዞ ወደ ንግሥናው ሥልጣን የመጣው፡፡ ዲዮቅልጥያኖስም በእርሱ ሹመት በግብጽ ሁለት ግዛቶችን ያስተዳድር የነበረውን የቅድስት ዴሚያናን አባት ማርቆስን ወደ አንጾኪያ አስጠርቶ አመጣውና ለጣዖታቱ እንዲሰግድ አዘዘው፡፡ ❤ ማርቆስም በመጀመሪያ ለጣዖታት ስገድ የሚለውን የዲዮቅልጥያኖስን ትእዛዝ ተቃውሞ የነበረ ቢሆንም በኋላ ግን በሰይጣን ፈተና በንጉሡም ሽንገላና ስጦታ ተታሎ ለጣዖታቱ ሰገደ፡፡ በመጀመሪያ ጠንካራ ክርስቲያን ስለነበር አሁን ላይ ክርስቶስን ክዶ ለጣዖታት መስገዱ በሀገሩ ሁሉ ተሰማ፤ ልጁ ቅድስት ዴሚያናም ይኽን በሰማች ጊዜ እጅግ አዝና ስለ አባቷ ነፍስ መጥፋት እያነባች ወደ እግዚአብሔር ጸሎትንና ልመናን አበዛች፡፡ ቅዱስ ቂርቆስ ስለ እናቱ ኢየሉጣ እንደጸለየ እርሷም ደወል ደውላ ለደናግል እኅቶቿ ነገረቻቸውና አብረው ስለ አባቷ ጸለዩ፡፡ ❤ እርሷም ወደ አባቷ ዘንድ ፈጥና ሔዳ "…ከፈጣሪህ ከኢየሱስ ክርስቶስ ተለይተህ በመንፈሳዊ ጌጥ ከምትኖርበት ሕይወት ወጥተህ ከምሰማ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተህ ነፍስህ ወደ ገነት ስትገባ መስማትን እሻለሁ" እያለች ገሠጸችው፣ መከረችው፡፡ ዳግመኛም "…ስለ ክርስቶስ መስክረህ ሰማዕት ሆነህ ብትሞት ከክርስቶስ ጋር ትኖራለህ፣ ነገር ግን ለጣዖት እየሰገድክ ከኖርክ ግን ከዲያብሎስ ጋር ትኖራለህ፤ በዚህ ሥራህ ከቀጠልክም አንተ አባቴ አይደለህም እኔም ልጅህ አይደለሁም" አለችው፡፡ አባቷ ማርቆስም ይህንና ሌላውንም የበዛውን የምክሯን ቃል ከእርሷ በሰማ ጊዜ ልቡ ተነክቶ ተጸጽቶ ዳግመኛ በክርስቶስ ስም መስክሮ ለመሞት የተዘጋጀ ሆኖ ወደ ንጉሡ ዘንድ ሔደ፡፡ ቅድስት ዴሚያናም የእርሷንና የአርባውን ደናግል ጸሎታቸውን ሰምቶ የአባቷን ነፍስ ስላዳነላት ጌታችንን አመሰገነችው፡፡ ዳግመኛም እንዲጠብቀው ስለ አባቷ ጸለየች፡፡ ❤ አባቷ ማርቆስ ወደ አንጾኪያ ሔዶ በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ፊት ቆሞ ፊቱን በመስቀል ምልክት ካማተበ በኋላ ድምፁን ከፍ አድርጎ ለንጉሡ እንዲህ አለው፡- "እኔ ኃጢአትን ሠርቻለሁ፣ እርሱ ስለ እኔ የሞተውንና ደሙን ያፈሰሰውን እውነተኛውን ንጉሤን ጌታዬንና መድኀኒቴን ኢየሱስ ክርስቶስን አሳዝኜዋለሁ፤ ዛሬ እኔ ከዚህ የመጣሁት ስለ እርሱ በግልጽ በአንተ ፊት መስክሬ ስለ ስሙ ለመሞትና ደሜን ለማፍሰስ ተዘጋጅቼ ነው፡፡ በተሳሳተ መንገድ ጌታዬን በመካድ ከአፌ የወጣውን ነገር ሁሉ እቃወማለሁ፣ ሰዎች የሠሯቸውን ጣዖታትን እቃወማለሁ፣ እነርሱም ከዲያብሎስ ናቸው…" አለው፡፡ ዲዮቅልጥያኖስም ከማርቆስ ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ደንግጦ ሐሳቡን ያስቀየረውን ነገር መመርመር ጀመረ፡፡ ማርቆስንም መልሶ ለማሳመን ብዙ ሞከረ ነገር ግን ማርቆስ የጌታችንን አምላክነት መመስከርና ጣዖታትን መቃወሙን ቀጠለ፤ ንጉሡም መኳንንቱን ሰብስቦ "ማርቆስ ከሮም ግዛቶች ውስጥ ካሉት ከታላላቆቹ አስተዳዳሪዎች ውስጥ አንዱ ስለሆነ እርሱን ልንተወው አይገባም፣ በሕይወትም መኖር የለበትም" ብሎ ከሰዎቹ ጋር ከተማከረ በኋላ የማርቆስን አንገት በሰይፍ አስቆረጠውና ለሰማዕትነት ክብር አበቃው፡፡

በአዋጅ ነጋሪ ቃልም ይሰበሰባሉ፡፡ ይህቺ ሀገር ትልቅ ናትና እስከ ዓርብም ያስተምራቸዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ሰይጣን ቀና፡፡ አባ ሐዊም እንደልማዱ በዕለተ ዓርብ ወደ ሰማይ በሄደ ጊዜ ያ ሰይጣን በመቀመጫው ተቀምጦ በእርሱ በሐዊ ተመስሎ በቀዳሚት ሰንበት ቀንም ተገልጦ "ፈጣሪያችን የሚወዳትን ነገር እነግራችሁ ዘንድ ሁላችሁም ተሰብሰቡ" አለ፡፡ ሁላቸውም ተሰበሰቡ፡፡ "አባት ሆይ! ያለ ልማድህ ዛሬ ለምን መጣህና ጠራኸን?" አሉት፡፡ ያ ጠላት ዲያብሎስም "ጌታዬ ለሕዝቦቼ የዚያችን በቤትህ አንፃር ያለችውን እንጨት ቅጠል በጥርሳቸው ይጨምሩ ዘንድ፣ በአፋቸውም ያጤሱ ዘንድ ዛሬ ካልነገርሃቸው ወዳጄ አይደለህም አለኝ" አላቸው፡፡ ይህችንም እንጨት ባያት ጊዜ እንዲህ አደረገ፣ ሔዋንን በእንጨት እንዳሳታት አሳታቸው፡፡ ዛሬ እንደሚያደርጉትም የጥንባሆ ዕቃን አደረጉ፡፡ ቅጠሏንም አምጥተው ቀጥቅጠው በእሳት አጢሰው ትንሹም ትልቁም፣ የከበረውም የጎሰቆለውም ሁላቸውም ጠጡ፡፡ ❤ ሐዊም በሰማይ ሳለ በጸጋ አውቆ አዘነ፣ ነገር ግን ስለ ሰንበታት ክብር ብሎ አደረ፡፡ ሰኞ በነግህም ሐዊ መጣ፣ ሰይጣንም እንደ ጢስ በኖ ጠፋ፡፡ እርሱም ሰዎቹን ሰብስቦ "ይህን ማን አስተማራችሁ?" አላቸው፡፡ "አንተ ነህ" አሉት፡፡ "ሰይጣን ነው እንጂ እኔ አይደለሁም፣ ከዛሬ ጀምሮ ተው" አላቸው፡፡ "ትናንት ጠጡ፣ ዛሬ ተው" ይለናል ብለው እምቢ አሉት፡፡ እርሱም አወገዛቸው፡፡ "በእርሻው የዘራት፣ በአፉም የጠጣት፣ በእጁም የያዛት የተረገመ ይሁን" አላቸው፡፡ ጋኔኑም በቅሉ ውስጥ ሆኖ ይነጋገራል፣ በውጭ ያሉትንም አጋንንት ይጠራቸዋል፡፡ በዚህን ሰዓት የተውም አሉ፣ እምቢም ያሉ አሉ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያቺ እንጨት ተረገመች፡፡ ሰውም በጠጣት ጊዜ የአምስት ቀፎ ሙሉ ንቦችን የሚያህሉ አጋንንት ይመጣሉ፡፡ በሁለቱ ዓይኖቹ ውስጥ፣ በሁለቱ አፍንጫዎቹም፣ በሁለቱ ጆሮዎቹም፣ በአፉም፣ በታች በሰገራ መውጫም በእነዚህ ሁሉ እንደ ቀፎ ንብ ይገባሉ፣ ይወጣሉ፡፡ ትምክህትን፣ ትዕቢትን፣ መግደልን፣ ሥርቆትንም፣ ክፉውንም ሁሉ ይመሉታል፡፡ ወሶበ ይሰትያ ብእሲ ይመጽኡ አጋንንት ዘየአክሉ መጠነ ፭ቱ ቀፈዋት ዘመልኡ አንህብት ወይበውኡ ውስቴቱ፡፡ በ፪ አዕይንቲሁ፣ ወበ፪ አዕናፊሁ፣ ወበ፪ አዕዛኒሁ ወበመንፈሱ ዘታህት በአፉሁ በዝንቱ ኵሉ ከመ ንህብ ዘቀፎ ይበውኡ ወይወጽኡ፡፡ ወይመልእዎ ትምክህተ፣ ወትዕቢተ፣ ቀትለ፣ ወሠሪቀ ወኵሎ ዕከያተ እንዲል መጽሐፍ፡፡ ❤ አባታችን ዘርዓ ቡሩክም ይህን ሰምቶ እጆቹን በትከሻው አመሳቅሎ አለቀሰ፣ በሥዕሉም አለ፣ በዚያን ጊዜ ወደ ዓለም ወጣ፡፡ ይህችን የተረገመች እንጨት እንዲህ ብሎ አወገዛት፡- "በአፉ የጠጣት፣ በእጁም የያዛት፣ የዘራት፣ የሸጣት፣ የገዛትም የጥምቀት ልጅ አይደለም፤ በሥጋው አይጠቀምም፣ ነፍሱም ወደ ሲዖል ትወርዳለች፡፡ ልጄ የሆነ ግን መድኃኔዓለምንና ኪዳነ ምሕረትን ያክብር፡፡ ጥንባሆንም አይጠጣ› አለ፡፡ የዚህ ጻዲቅ በረከቱ ያልታዘዝንውን ከመብላት ይጠብቀን አሜን" በማለት ተአምረ መድኃኔዓለም ወገድለ መባዓ ጽዮን ነገረ ጥንባሆን በሰፊው ዘግቦታል፡፡ በሌላም በኩል ትንባሆን በተመለከተ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የሰጣቸው ቃልኪዳን በራሳቸው በዘርዐ ቡሩክ ገድል ላይ የተጻፈውን ወደፊት እናያለን፡፡ እንዲሁም ይህችን የተረገመች ዕፅ የሚጠቀሙባት ሁሉ የሰይጣን ማደሪያዎች እንደሚሆኑና ክፉውንም ሁሉ እንደሚያሠሩት በሌላም ቦታ በአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ገድል ላይ በሰፊው ተጽፏል፡፡ ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ሳይጠመቁ ለሚሞቱ አሕዛብም ጭምር ትልቅ ቃልኪዳን የተሰጣቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ይኸውም በቅዱስ ገድላቸው ላይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል- "በሥራው ሁሉ ፍጹም የሆነና ገድሉ ያማረ ቅዱስ አባታችንን በአድማስ ራስ ቆሞ ምሥራቁንና ምዕራቡን፣ ሰሜኑንና ደቡቡን እንዲባርክ በአፉ እስትንፋስም የምሕረት እስትንፋስን እፍ እንዲል እስትንፋሱንም ከአድማስ እስከ አድማስ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደርስ ዘንድ እግዚአብሔር አዘዘው፡፡ በእግዚአብሔር በቅዱስ ስሙ ያልተጠመቁ አሕዛብ በእስትንፋሱ ምክንያትና የምሕረት እስትንፋስን እፍ እንዲል እስትንፋሱንም ከአድማስ እስከ አድማስ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደርስ ዘንድ እግዚአብሔር አዘዘው፡፡ በእግዚአብሔር በቅዱስ ስሙ ያልተጠመቁ አሕዛብ በእስትንፋሱ ምክንያት ልጅነት አግኝተው እንዲከብሩ በቃል ኪዳኑ ተማፅነው ሳይጠመቁ በሚሞቱበት ጊዜ "ይህ ከእኔ የተቀበልከው ቃልኪዳን ከጎኔና ከሰውነቴ እንደፈሰሰው ደሜ ይሁንላቸው" በማለት ለዓለም መድኃኒት አድርጎ ቃልኪዳን ሰጠው፡፡ ❤ ዳግመኛም በቅዱስ አባታችን ዘርዐ ቡሩክ ስም ከእግዚአብሔር ምሕረትን ለምነው በሚሞቱበት ጊዜ በውኃና በመንፈስ ቅዱስ እንደተጠመቁ ይሁንላቸው ብሎ ነገረው፡፡ በከበረና በገናና ስሙ የተጠመቁ ሕዝቡም በኃጢአታቸው በወደቁ ጊዜ በሥራቸውም በረከሱ ጊዜ በጻድቁ ጸሎት ቢማጸኑ በቃልኪዳኑ ቢያምኑ ይህ እስትንፋሱ የኃጢአት ማስተሠርያ ይሁናቸው ብሎታል፡፡ ጻድቁ አባታችንም የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በሰማ ጊዜ ከዚያ በፊት ለሌሎች ያልተሰጠ ቃልኪዳን ተቀብሎ በአድማስ ላይ ቆመ፡፡ በዚያም ቆሞ መንፈሳዊ እስትንፋሱን በምድር ላይ እፍ አለ፡፡ ያም የሕይወት እስትንፋስ በአራቱ ማዕዘን ደርሶ በኃጢአታቸው መከራ የተቀበሉ ለበደላቸውም የተገዙ ሰዎች በፈጣሪያቸው ስም እንዲከብሩ ዓለሙን ሁሉ ባረከ" ይላል ቅዱስ ገድላቸው፡፡ ይህም የሚያሳያየው መድኃኔዓለም ክርስቶስ የሰውን ልጆች ምን ያህል እንደወደዳቸውና በትንሽ ምክንያት የመዳንን መንገድ ያዘጋጀላቸው መሆኑን ነው፡፡ ❤ ሌላው አቡነ ዘርዐ ቡሩክ እሳቸው በባረኳት ምድርና በልጆቻቸው ላይ ችግርና ርኀብ እንደማይደርስባቸው ቃልኪዳን የተሰጣቸው ድንቅ አባት ናቸው፡፡ ይኸውም በቅርቡ እንኳን በ1977ቱ የርሃብ ዘመን በግልጽ ስለታየ ታሪክ ይመሰክረዋል፡፡ በዚህ ወቅት ከወሎና ከሌሎችም ቦታዎች በርሃብ ተሰዶ ጎጃም ለመጣው የሀገራችን ሕዝብ የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ በረከት ከበቂ በላይ ነበር፡፡ ❤ ጻድቁ በጎጃም ባሕር ዳር አካባቢ ሁለት ቤተ ክርስቲያን አላቸው፡፡ የዓባይ ምንጭ መነሻ የሆነው ፈለገ ግዮን ግሽ ዓባይ ከባሕር ዳር ከተማ 174 ኪ.ሜ የሚርቅ ሲሆን ከባሕር ዳር ቲሊሊ፣ ከቲሊሊ ሠከላ በመሳፈር በቦታው ላይ ለብዙ ዘመን ቆመው በመጸለይ ታላቅ ቃልኪዳን የተቀበሉበትን እጅግ ተአምረኛና ፈዋሽ የሆነውን ጸበላቸውን ማግኘት ይቻላል፡፡ ቦታው መጽሐፋቸውን ለዓባይ ወንዝ አደራ የሰጡበት ነው፡፡ ❤ ሌላኛው ቤተ ክርስቲያናቸው ከባሕር ዳር የሁለት ሰዓት የመኪና መንገድ ርቀት ላይ በምትገኘውና አዴት በምትባለው ቦታ የሚገኘው ነው፡፡ የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ መካነ መቃብራቸውና ከሰማይ የወረደላቸው መስቀል እዚህ ይገኛሉ፡፡ ቦታውን የረገጠ ሁሉ ከመካነ መቃብራቸው ላይ እምነት ይወስዳል፣ በመስቀሉም ይባረካል፡፡ ነገር ግን ጻድቁ በቃል ኪዳናቸው መሠረት በዚህ መስቀላቸው የተባረከ ሁሉ ዲቁናን፣ ክህነትን መቀበል ስለሚችል ሴቶች አይባረኩበትም፡፡ መካነ መቃብራቸው ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ከመቅደሱ ውጭ የሚገኝ ሲሆን ከመቃነ መቃብራቸው ላይ ያለው አፈር ሁልጊዜ እየፈላ መጠኑ ይጨምራል፡፡ ይህን የእምነቱን አፈር ቢዝቁት አያልቅም፣ ባዶ እንኳን ቢደረግ በተአምራት ሞልቶ ይገኛል፡፡ ለብዙ ሕመምተኞች ፍጹም ፈውስ የሆነው ይህ እምነት አጠቃላይ ሁኔታው ለዕይታ አመቺ ስለሆነ ይህንን ማንኛውም ሰው ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ማየትና እምነቱን ወስደው መጠቀም ይችላሉ፡፡ ❤ ጻድቁ አባታችን በ482 ዓመታቸው በዚህች ዕለት ጥር 13 ቀን በታላቅ ክብር ያረፉበት በዓላቸው በድምቀት ይከበራል፡፡ በዕረፍታቸው ዕለት ከቤተ ክርስቲያኑ አደባባይ ላይ አትሮንስ ወጥቶ ገድላቸው ይነበባል፡፡ ገድላቸው ሲነበብም ከአትሮንሱ ሥር ሰባት ጠርሙሶችና አንድ ማሰሮ ይቀመጥና በጠርሙሶቹ ውስጥ አንድ አንድ ስኒ ውኃ ይደረግባቸዋል፡፡ የአባታችን ቅዱስ ገድላቸው ሲነበብ ውኃው ይፈላል፣ ገድሉ ተነቦ እንዳለቀ ጠርሙሶቹና ማሰሮው በተአምራት ተሞልተው ይገኛሉ፡፡ ❤ ጌታችን ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ትንባሆን ስለሚጠጡ ሰዎች ታላቅ ምሥጢርን እንደነገራቸው በቅዱስ ገድላቸው ላይ ተጽፏል፡፡ ቅዱስ አባታችን በየቀኑ ለሰባት ሰዓት ያህል በሲኦል ውስጥ ቆመው በመጸለይ ብዙ ነፍሳትን ከእሳት ያወጡ ነበር፡፡ አንድ ቀን ብዙ ነፍሳትን ካወጡ በኋላ አንዲት ነፍስ ግን ከሲኦል ግደግዳ ጋር እንደ ሰም ተጣብቃ እምቢ አለቻቸው፡፡ አባታችንም ያቺን ነፍስ አወጣለሁ ሲሉ ቆመው ይጸልዩበት የነበረው የሲኦል እሳት አሁን ያችን ነፍስ አወጣላሁ ባሉ ሰዓት ግን አቃጠላቸው፡፡ እሳቸውም ያችን ነፍስ እዚያው ሲኦል ጥለው በመውጣት ጌታችንን "የዚያች ነፍስ ኃጢአቷ ምንድን ነው?" አሉት፡፡ የዚህን ጊዜ ነው ጌታችን ትንባሆን ስለሚጠጡ ሰዎች ታላቅ ምሥጢርን የነገራቸው፡፡ ይኸውም አባ ሐዊ የሚባሉ ጻድቅ ያስተላለፉትን ውግዘትና ግዝት የጸና እንደሆነ ነው ጌታችን ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የነገራቸው፡፡ ❤ ዝርዝር ታሪኩም በድርሳነ መድኃዓለም ላይ እንዲህ ተጽፎ ይገኛል፡- ትንባሆ የሚጠጡ ሰዎች ለምን ለማቆም እንደሚቸገሩና መጨረሻቸውም ምን እንደሆነ፡- "ይቅርታውና ምሕረቱ ከሁላችን የጥምቀት ልጆች ጋር ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኔዓለም ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡- አባታችን ዘርዓ ቡሩክ መድኃኔዓለምን እንደወደደውና በየወሩ በሃያ ሰባት ቀን በዓሉን እንደሚያከብር በአሥራ ስድስት ቀንም ኪዳነ ምሕረትን እንደሚያከብር እነሆ እንነግራችኋለን፡፡ ባለሟልነትን ባገኘ ጊዜና መድኃኔዓለም የእሳት ፈረስንና የመስቀል ምልክት ያለበት የወርቅ በትርን በሰጠው ጊዜ "ወደ ሲዖል ሂድና መሸከም የምትችለውን ያህል ነፍሳትን አውጣ› አለው፡፡ ሄዶም ወደ ሲዖል ገባ፣ ነፍስ በነፍስ ላይ እንደ ንብ እየተጨናነቁ በሰውነቱ ላይ ታዘሉ፡፡ ነፍሳትንም ይዞ ሲወጣ አንድ ኃጢአተኛ ‹ዘርዓ ቡሩክ ብቻዬን ቀረሁ፣ አውጣኝ" አለው፡፡ ዘርዓ ቡሩክም ወደ እርሱ ተመልሶ ሳበው፡፡ ሰም ከፈትል ጋራ እንደሚጣበቅ ከሲዖል ጥልቅ ጋራ ተጣብቆ እምቢ አለው፡፡ የእሳቱ ነበልባልም ዘርዓ ቡሩክን አቃጠለው፣ እርሱም ተወው፡፡ ክብር ይግባውና እነዚያን ነፍሳት ይዞ ወደ ጌታው ወደ መድኃኔዓለም ሄደ፡፡ ❤ ሄዶም "ጌታዬ ሆይ! አንዲት ነፍስ ስሜን እየጠራች ቀርታለች ማርልኝ" አለው፡፡ መድኃኔዓለምም "ዘርዓ ቡሩክ ሆይ! በእኔ ዘንድ ባለሟልነትን ብታገኝ ትንባሆ የሚጠጣውን ማርልኝ ትለኛለህን?" አለው፡፡ እርሱም "ጌታዬ ሆይ! ይህቺ እንጨት በምን ትከፋለች?፣ ከሁሉ ኃጢአትስ በምን ትበልጣለች?" አለው፡፡ ወይቤሎ መድኅን ኢሰማዕከኑ ግብራ ለዛቲ ዕፅ ዘከመ ዘርዓ ሰይጣን ውስተ ገራህተ ዓለም፡፡ መድኃኔዓለምም "የዚህችን እንጨት ሥራ በዓለም እርሻ ሰይጣን እንደዘራት አልሰማህምን?" አለው፡፡ እነሆም እንነግራችኋለን፣ ስሙ ሐዊ የሚባል የፈጣሪውንም ሕግ የሚጠብቅ አንድ መምህር ነበረ፡፡ በዓርብ ቀንም ወደ ሰማይ ይሔዳል፤ በቀዳሚት ሰንበትና በእሑድ ከፈጣሪው ጋር ይነጋገራል፡፡ በሰኞ ቀንም ወደ ቦታው ይመለሳል፡፡ ለሀገር ሰዎችም በጉባኤ ይነግራቸዋል፣

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፲፫ (13) ቀን። ❤ እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ሲዖል ውስጥ ገብተው ይጸልዩ ለነበሩት ለታላቁ አባት ለአቡነ ዘርዐ ብሩክ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። + + + ❤ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ፦ ከመወለዳቸው አስቀድሞ ትንቢት ተነግሮላቸው ነበር፡፡ አባታቸው ደመ ክርስቶስ ዐይነ ሥውር የነበረ ሲሆን አቡነ ዘርዐ ቡሩክ በተወለዱ ጊዜ ግን የአባታቸውን ዐይን አብርተውለታል፡፡ አባታችን ዘርዐ ቡሩክ ገና በሰባት ዓመታቸው ነው ረቡዕና ዓርብ መጾም የጀመሩት፡፡ በዚሁ በሰባት ዓመታቸውም ‹‹ይህን ዓለም ክፋቱን እንዳላይ ዐይኖቼን አሳውርልኝ›› በማለት ዐይናቸውን እንዲያጠፋላቸው አምላካቸውን ለምነው እንደፈቃዳቸው ዐይነ ሥውር ሆነዋል፡፡ ነገር ግን ከሰባት ዓመት በኋላ በ12 ዓመታቸው ጌታችን "ለዓለም የምታበራ ብርሃን አደርግሃለሁና ዐይንህም ይብራ" በማለት ዐይነ ብርሃናቸውን መልሶላቸው እንዲያዩ አድርጓቸዋል፡፡ በዚህም ዕድሜያቸው (በ12 ዓመታቸው) ሰባቱንም አጽዋማት ይጾሙ ነበር፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ጌታችን የቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢር ሁሉ ገለጠላቸው፡፡ መጻሕፍተ ብሉያትን፣ መጻሕፍተ ሐዲሳትን፣ መጻሕፍተ ሊቃውንትን፣ መጻሕፍተ መነኮሳትን፣ አዋልድ መጻሕፍትን ሁሉ ገልጦላቸዋል፡፡ ከሟርት መጻሕፍት በቀር ያስቀረባቸው ነገር አልነበረም፤ የቅዱስ ያሬድንም ዜማ እንዲሁ ገለጠላቸው፡፡ ❤ ጻድቁ ከሁሉ ቅዱሳን በበለጠ ሁኔታ ዐሥራ ሁለት ክንፍ የተሰጣቸው ሲሆን በ12 ክንፎቻቸውም የሰማይን ደጆች ሁሉ ገሃነመ እሳትንም አልፈው በመሄድ ቀጥታ በሥሉስ ቅዱስ ዙፋን ፊት ይቆሙ እንደነበር ቅዱስ ገድላቸው ይናገራል፡፡ እጅግ በሚደንቅና ከአእምሮ በላይ በሆነ ሁኔታ አባታችን ለሰባት ቀናት በየቀኑ ለሰባት ሰዓት ያህል በሲኦል ውስጥ ቆመው ይጸልዩ ነበር፡፡ ብዙዎቹ ቅዱሳን በምልጃቸው ነፍሳትን ከሲኦል ሲያወጡ ነው የምናውቀው እንጂ እንደ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ በሲኦል ውስጥ ገብቶ ጸሎት የጸለየ ጻድቅ እስካሁን እኔ አላጋጠመኝም፡፡ ❤ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ እንደ አባታችን ተክለሃይማኖት ለጸሎት በመቆም ብዛት አንድ እግራቸው እስኪሰበር ድረስ በብዙ መከራ ተጋድለዋል፡፡ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር መንበሩን ያጥኑ ዘንድ ከፈጣሪአቸው ታዘው አጥነዋል፡፡ ጌታችን ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ፍጥረታትን ከመፍጠር በቀር ያልሰጣቸው ሥልጣን የለም፡፡ "እግዚአብሔር ብፁዕና ቅዱስ ለሚሆን አባታችን ዘርዐ ቡሩክ "እኔ ከሥልጣኔ ሥልጣንን፣ ከክብሬም ክብርን፣ ከጥበቤም ጥበብን፣ ከተአምራቴም ተአምራትን፣ ከስጦታዬም ስጦታን፣ ከትዕግስቴም ትዕግስትን፣ ከፍቅሬም ፍቅርን፣ ከትሕትናዬም ትሕትናን፣ ከባለሟልነቴም ባለሟልነትን ሰጥቼሃለሁና ሁሉ ከሥልጣንህ በታች ሆኖ ይታዘዝልህ" የሚል እጅግ ድንቅ ቃልኪዳን ነው የሰጣቸው፡፡ ልዩ ልዩ ሀብታትን ሁሉ ሰጣቸው፡፡ "ለሥላሴ ከሚገባ ከስግደትና በቃልና በሥልጣን ፍጥረታትን ለመፍጠር በቀር ምንም ያልሰጠሁህ የለም" ብሎ ጌታችን በማይታበል ቃሉ እንደነገራቸውና ቃል እንደገባላቸው በቅዱስ ገድላቸው ላይ ተጽፏል፡፡ (የአባታችን ገድላቸው ከመጥፋቱ የተነሣ በአሁኑ ሰዓት አንዳንድ ነጋዴዎች አንዱን ፍሬ ከ3 ሺህ ብር በላይ እየሸጡት ነበር፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ ቲሊሊ የሚገኘው ገዳማቸው በድጋሚ አሳትሞታል፡፡ ❤ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ በወቅቱ በነበረው ገዥ ፊት በሐሰት ተከሰው ለ5 ዓመታት ያህል በእስርና በእንግልት ሲኖሩ በእነዚህ ጊዜያት ሁሉ ምግብ የሚባል አይቀምሱም ነበርና ከእስር ሲፈቱ አምስት ዓመት ሙሉ ሲሰጣቸው ያጠራቅሙት የነበረው ምግብ ትኩስ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ያሳሰራቸውንም ንጉሥ ገና ሕፃን ሳለ እናቱ ልታስባርከው ወደ አባታችን ዘንድ ወስዳው ነበር፡፡ አቡነ ዘርዐ ቡሩክም ሕፃኑን ከባረኩት በኋላ ለእናቱ "ይህ ልጅሽ ወደፊት ይነግሣል በንግሥናው ዘመንም እኔን ያስርና ያንገላታኛል" ብለው ይህ እንደሚሆን አስቀድመው ትንቢት ተናግረው ነበር፡፡ እንዳሉትም ልጁ አድጎ ሲነግሥ ጭፍሮቹ "ንጉሥ ሆይ አንተን የማይወድ ለቃልህም የማይታዘዝ አንድ መነኩሴ አለ" በማለት ምንም እንኳን ንጉሡ ባያውቃቸውም በሐሰት ነገር ስለከሰሱለት በግዞት እንዲኖሩና እንዲታሰሩ አድርጓቸዋል፡፡ ጻድቁ በግዞት ሲወሰዱ "እነዚህን መጻሕፍቶቼን ለሰዎች አደራ ብሰጣቸው ይክዱኛል፣ ቤተ ክርስቲያን ባስቀምጣቸው ይጠፉብኛል" በማለት ሰባት መጽሐፎቻቸውን ለግዮን (ለዓባይ) ወንዝ አደራ የሰጡ ሲሆን ከ5 ዓመት በኋላ ከእስር ተፈተው ሲመለሱ በወንዙ አጠገብ እንደደረሱ ጸሎት ካደረጉ በኋላ "ግዮን ሆይ በእግዚአብሔር ፊት በአደራ የሰጠሁሽን መጽሐፎቼን ግሺ (ትፊ)" ብለው እጃቸውን ወደ ወንዙ ሰደው መጽሐፎቻቸው ሳይረጥቡና ሳይበሰብሱ ከወንዙ ውስጥ አውጥተዋቸል፡፡ እንዲያውም አቧራውን ከመጻሕፍቶቻቸው ላይ እፍ ብለው አራግፈውታል፡፡ ❤ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተጠቀሰው የጠለቀው ምሳር እየተንሳፈፈ ወደ ኤልሳዕ እንደመጣ ሁሉ አሁንም እንዲሁ የቅዱስ አባታችን መጽሐፎች አብሯቸው ከነበረውና ዘሩባቤል ከሚባለው ደቀ መዝሙራቸው ጋር ወዳሉበት ተንሳፈው ሊመጡ ችለዋል፡፡ መጽሐፎቻቸውንም አብሯቸው ለነበረው ደቀ መዝሙራቸው ካሳዩት በኋላ እንዲይዛቸው ሰጥተውታል፡፡ ❤ የግዮን ወንዝ "ግሺ ዓባይ" ወይም "ዓባይ" እየተባለ መጠራት የጀመረው አቡነ ዘርዐ ቡሩክ "ግዮን ሆይ በእግዚአብሔር ፊት በአደራ የሰጠሁሽን መጽሐፎቼን ግሺ (ትፊ)" ብለው እጃቸውን ወደ ወንዙ ሰደው መጽሐፎቻቸው ሳይረጥቡና ሳይበሰብሱ ከወንዙ ውስጥ ካወጡበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ አባታችን በቦታው ላይ 30 ዓመት ሙሉ ቆመው ጸልየው ቦታውን የባረኩት ሲሆን ጌታችንም በቦታው ላይ ትልቅ ቃልኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ "ብፁዕ አባታችን ለግዮን ወንዝ መጽሐፎቹን በአደራ ሰጥተው በኋላም ከደቀ መዝሙራቸው ከዘሩባቤል ጋር መጽሐፎቹን ከግዮን ምንጭ ውስጥ ከተቀበለ በኋላ "በግዮን ውኃ ውስጥ ሳይረጥቡ በደረቅ መጽሐፎቼን የጠበቀ እግዚአብሔር ይመስገን" ብሎ ፈጣሪውን አመሰገነ፡፡ "ያንጊዜም በውስጥሽ ታላቅ ድኅነት ይደረግብሽ፣ ሕመምተኞች ሁሉ ይዳኑብሽ፣ መካኖች ይውለዱብሽ" ብሎ ግዮንን በቃሉ መረቃት፣ በእጁም ባረካት፡፡ ብፁዕ አባታችንም በዚህች ቦታ ላይ ፈውስ፣ ረድኤት፣ በረከት ይደረግብሽ ብሎ ብዙ ዘመን ቆሞ ጸለየ፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ "ይህ በረከት፣ ረድኤት፣ ሀብት፣ ፈውስ እንደወደድህ እስከዘለዓለሙ በዚህ ቦታ ይሁንልህ" አለው" ተብሎ ነው በቅዱስ ገድላቸው ላይ የተጻፈው፡፡ ❤ ጻድቁ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ሌላው የሚታወቁበት "ብሄሞትና ሌዋታን" የተባሉ እጅግ ግዙፍ የሆኑ ሁለት ዘንዶዎችን ጥርሳቸውን ቆጥረው ምላሳቸው ሲጣበቅ የዓለም ፍጻሜ እንደሚሆን አስቀድመው ያወቁ ድንቅ ነቢይ የሆኑ አባት በመሆናቸው ነው፡፡ እነዚህም እጅግ ግዙፍ የሆኑ ሁለት እንስሳት ሴትና ወንድ ሆነው ምድርን እንደመቀነት ከበው የያዙ ናቸው፡፡ ዝርዝር ታሪካቸው በመጽሐፈ አክሲማሮስ (ሥነ ፍጥረትን በሚያስረዳው መጽሐፍ) ላይ በስፋት ተጠቅሰዋል፡፡

photo content

photo content