ሰዋስው ☘☘☘☘
Ir al canal en Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
Mostrar más1 161
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
1 161
አንድ ሚሊዮን ምዕመን አንድ ዲያቆን መሆን አይችልም
#ዲያቆን #ኤፍሬም የኔሰው ስለ ክብረ ዲቁና አስመልክቶ የሰጠውን ሐሳብ መነሻ በማድረግ ሰሞኑን ብዘዎች ሐሳቡን በመለጠጥ ሲያራግቡትና ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ ሲወስዱት በማየቴ አንድ ነገር ማለት ፈለግሁ
የዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው ሐሳብ አንድ ዲያቆን አንድን ጳጳስ ለማግኘት ወይም ከጳጳሱ ጋር ለመነጋገር የምእመን ፈቃድ ማግኘት ወይም መጠበቅ አይጠበቅበትም ይልቁንም አንድ ዲያቆን ከአንድ ምእመን ለጳጳሱ ቅርበት ስላለው የማንንም ምእመን ፈቃድ ሳይጠይቅ አንድን ጳጳስ ማግኘት ይችላል የሚል ነበር
ነገር ግን ይህ ሐሳብ ደስ ያላሰኛቸው ግለሰቦች ሐሳቡን ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ በመውሰድና ሐሳቡን በመጠምዘዝ መነታረኪያ እና መዘባበቻ ስለአደረጉት አንድ ነገር እንድል ተገደድሁ
ብዙዎች በጽሁፋቸው ዲያቆን ከአንድ ምእመን የሚለየው መቅደስ ውስጥ ገብቶ ተልዕኮ በመፈጸሙ እንጂ አንድ ዲያቆን ከአንድ ምእመን በምንም ነገር እንደማይበልጥ ዲያቆን ማለት ምእመን ማለት እንደሆነ ሲጽፉ አይቻለሁ ተመልክቻለሁ
በዚህ መልኩ የጻፋችሁ ሰዎች ኑና
እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ
አንድ ዲያቆን መቅደስ ውስጥ ገብቶ ተልዕኮ በመፈጸም ከሚሊዮን ምእመን የሚለይ ከሆነ አንድ ዲያቆን ከአንድ ምእመን አንድ የሚሆነው በምን ሂሳብ ነው?
መቶ ሚሊዮን ምእመን ቢኖር እኮ በዲያቆኑ እየተመራ የቤተክርስቲያን ምስጢራትን ይካፈላል እንጂ ዲያቆን በምእመን እየተመራ ምስጢራተ ቤተክርስቲያንን አይፈጽምም
መቶ ሚሊዮን ምእመን ቢኖር መቶ ሚሊዮን ምእመን ከዲያቆኑ እጅ ደመ ወልደ እግዚአብሔርን ይቀበላል እንጂ ዲያቆን ከምእመን እጅ አይቀበልም
ዲያቆን በምእመናን ላይ ይሾማል እንጂ ምእመን ዲያቆናት ላይም አይሾሙም
ለነገሩ ክብረ ግብረ ዲቁና በዚህ ዘመን እንዲሁ እንደ እርዳታ ስንዴ ወይም እንደ ሰንበቴ ጽዋዕ አጥር ጥሶና ኬክ ጎርሶ ለመጣ ሁሉ የሚታደልበት ዘመን ከመሆኑ የተነሣ ለግብረ ዲቁና ያለን ዋጋ በዚህ ደረጃ መውረዱ ብዙም አይገርምም
ምክንያቱም በዚህ ዘመን ስሙን ሰርቀውና ቀምተው በመውሰድ እንበለ ግብር ዲያቆናት የተባሉ እልፍ አእላፋት ስለሆኑ በድፍረት ዲያቆን ማለት ምእመን ነው ምእመን ማለት ዲያቆን ነው እንድንል የልብ ልብ ሰጥቶናልና
በብሉይ ኪዳን አንድ ሰው ካህን የሚሆነው ከ25 ዓመት እስከ ከ 50 ዓመት ነበር ከዚህ በኋላ ሌዋዊ ማለትም የካህናት ተወራጅ ይባል ነበር እንጂ ከዓመት አንዴ መሥዋዕት እንደሚያቀርበው ሊቀ ካህናት እድሜ ልኩን ካህን ሲባል አይኖርም ነበር
ዛሬ ዛሬ ግን አንድ ሰው እንበለ ግብር (ያለ ሞያው ያለ ሥራ ውጤት ሲቀርበት ስሙን ብቻ ሰርቆ ወስዶ እስከ ሰባ ሰማኒያ ዓመት ዲያቆን እየተባለ የሚያረጅበት ስለሆነ ክብረ ዲቁናን በዚህ ደረጃ እንድናየው አድርጎናል
ጌታ ከመቶ ሃያው ቤተሰብ ውስጥ 12ቱን መርጦ ሐዋርያት ከ12ቱ ሐዋርያት ውስጥ አንድ ጴጥሮስን መርጦ ሊቀ ሐዋርያት አድርጎ ሹሟል
ማቴ 10 ዮሐ 21:15
ሐዋርያትም ከስምንት ሽህ ምእመናን መካከል ለክብረ ዲቁና የሚገቡትን አርድእት መርጠው ዲያቆናት ብለው በሕዝቡ ላይ ሹመዋል።
ግብ ሐዋ 6
ቅዱስ ጳውሎስም ለጢሞቴዎስ በጻፈለት መልእክቱ ማንኛውም ምእመን ዲያቆን መሆን እደማይችል ዲያቆናት መሆን የሚችሉት ድንግልናቸውን ጠብቀው የተገኙና በተጨማሪም ክርስቲያናዊ ጠባይ ያላቸው ብቻ መሆናቸውን ግልጥ አድርጎ ጽፎለታል
1 ጢሞ 3
ሠለስቱ ምእትም ይህ ከጌቶቻችን ከሐዋርያት ያገኘነው ሥርዐት ነው በማለት ዲያቆናት የተማሩና ደናግል የሆኑ መሆን እንደሚጠበቅባቸው በፍትሐ ነገሥት ጽፈውልናል
አንዱ ከአንዱ ሥልጣን ያለው ሥልጣን ከሌለው እንደሚበልጥም ጌታ በወንጌል አንትሙሰ ትነብሩ ዲበ ዐሠርቱ መናብርት ወትኴንኑ ዐሠርተ ወክልኤተ ሕዝበ ፳ኤል እናንተስ በአሥራ ሁለቱ የክብር ዙፋን ላይ በክብር ተቀምጣችሁ በዐሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል ላይ ትፈርዳላችሁ በማለት ከሥላሴ በታች ሐዋርያት አጋዕዝተ ሰማይ ወምድር መሆናቸውን ነግሯቸዋል። ማቴ 19:28
ቅዱስ ጳውሎስም ካልእ ክብሩ ለፀሐይ ወካልእ ክብሩ ለወርኅ ወካልዕ ክብሮሙ ለከዋክብት ኮከብ እምኮከብ ይኄይስ ክብሩ
የፀሐይ ክብሩ ሌላ ነው የጨረቃም ክብሩ ሌላ ነው የከዋክብትም ክብራቸው ሌላ ነው ኮከብ ከኮከብ በክብር ይበልጣልና። 1ኛ ቆሮ 15:41 በማለት ፀሐይ ብሎ የመምህራንን ጨረቃ ብሎ የምእመናንን ከዋክብት ብሎ የደቀመዛሙትን ክብር ይናገራል
መጻሕፍት ሁሉ እንዲህ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ እንደ አንድ ልብ አሳቢ ሆነው ከምንጩ ያለውን እውነታ ከነገሩን የእኛ ድርሻ መጻሕፍት የሚነግሩንን ሰምተን በሕገ መጻሕፍት መመራት እንጂ ሕገ መጻሕፍትን ሽረን የራሳችንን ሕግ ልናቆምና ልናጸድቅ አይገባንም
ባጭሩ ዲያቆን ማለት መልአክ ዘበምድር በምድር ያለ መልአክ ማለት ስለሆነ ከመልአክ እኩል ለመሆን ደግሞ መብቃት ማለትም ከስምንቱ የክብር ደረጃ ማለፍ ወይም ሞቶ መነሳት ስለሚጠበቅብን እስጊዜው ድረስ እንደየጸጋችን ብንኖር መልካም ነው እላለሁ
መምህር ወልደ ሰንበት ደሣለኝ
1 161
Repost from ሰዋስው ☘☘☘☘
☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘
ስርዓተ ማሕሌት ዘጥር ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️
ሥርዓተ ነግሥ
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል
@EOTCW
@EOTCW
መልክአሥላሴ
ሰላም ለአዕዳዊክሙ እለ ተኬነዋ ብእሴ፤
ኦ ኄራን አጋዕዝትየ ሥላሴ፤ ድኅረ ጸሐፈ ኦሪት ሊቀ ነቢያት ሙሴ፤ መሐረኒ ሥላሴክሙ መጽሐፈ መምህሩ ቅዳሴ፤ወልደ ነጎድጓድ ዮሐንስ ዘፍሕሮ ውዳሴ
@EOTCW
ዚቅ
ነሥአ ሙሴ ሠለስተ አስማተ ከመ ዘይወስድ አምኃ ለንጉሥ፤ ወሰማዕትኒ ይፀውሩ ሥላሴ።
@EOTCW
ወረብ
ነሥአ ሙሴ ሠለስተ አስማተ/፪/
ከመ ዘይወስድ አምኃ ለንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ዮሐንስኒ ሥላሴ ይፀውር/፪/
@EOTCW
ዓዲ ዚቅ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ በጽምረተ አሐዱ ጸሐፈ ወልደ ነጎድጓድ በክብርት እዱ።
@EOTCW
ዘጣዕሙ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ህይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።
@EOTCW
ዚቅ
ዘመንክር በአርያሙ እግዚአብሔር ስሙ፤ዝንጓጌ መስቀል አመ ተወፈየ ነዋ ወልድኪ ይቤላ ለእሙ ፍቅረ ዮሐንስ ኢያንተገበ ጊዜ ሕማሙ፤ላዕለ ጒንደ መስቀል አመ ውኅዘ ደሙ።
@EOTCW
@EOTCW
ነግሥ
ወልደ ነጎድጓድ ዮሐንስ በራእዩ ዜነወነ ፤ዘከመ ሞዓ ሰይጣነ፤ ሚካኤልሃ ዘይትዓፀፍ ርስነ፤ ይቤ ወንጌላዊ ርኢክዎአነ ፤ታዎሎጎስ (ታዎጎሎስ) ዘረፈቀ እንተ ነድ ሕፅነ።
@EOTCW
ዚቅ
ይቤ ዮሐንስ ለልየ ርኢኩ፤ ወአነ ሰማዕቱ ለሊቀ መላእክት።
@EOTCW
መልክአ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ማግቢያ፦
ባሕረ ጥበባት አበ ልሳናት ፤ንሥር ሠራሪ ልዑለ ስብከት ፨ #ዮሐንስ ወንጌላዊ ረዓዬ ኅቡዓት ፤ ነገሩኒ ቅሱም በጼወ መለኮት
@EOTCW
መልክአ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘተወደሰ ብዙኃ፤ወለሥዕርትከ አቄርብ ፍሬ ከናፍር አምኃ፤ዘተረሰይከ ዮሐንስ ትርሢተ መላእክት ንጽሐ፤ቃል ኃደረ ላዕሌነ ወኮነ መሲሐ፤ ቃለ ዓዋዲ ቃልከ እንዘ ይብል ጸርሐ።
@EOTCW
አመላለስ
ኃደረ ቃል ላዕሌነ/፪/
ወኮነ ወኮነ መሲሐ/፪/
@EOTCW
@EOTCW
ዚቅ
ፈክር ለነ ወልደ ነጎድጓድ፤ ዘረፈቀ ውስተ ሕፅነ ነድ፤ ፈክር ለነ ዘትቤ በወንጌል ፤ውእቱ ቃል ኃደረ ላዕሌነ ፤ወተወልደ እምኔነ።
@EOTCW
ወረብ
ፈክር ለነ ወልደ ነጎድጓድ ዘረፈቀ ውስተ
ሕፅነ ነድ/፪/
ዘትቤ በወንጌል ፈክር ለነ ውእቱ ቃል ኃደረ ላዕሌነ/፪/
@EOTCW
መልክአ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
ሰላም ለእመትከ አረፍተ ቤተ ሕግ ዘሰፈረ፤ ወለእራኅቲከ ዘወርቅ እለ አጽንዓ በትረ ፤ፈለገ ሃይማኖት ዮሐንስ ዘታስተፌሥሕ ሀገረ፤ ማኅተምከ ደኃራዊ አመ ይትፈታሕ ድኅረ ፤ጥቃ ማኅደርከ ሀበኒ ማኅደረ።
@EOTCW
@EOTCW
አመላለስ
ፈለገ ሃይማኖት ዮሐንስ/፪/
ዘታስተፌሥሕ ሀገረ/፬/
@EOTCW
@EOTCW
ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ ምርሐኒ ፍኖተ ወእሑር ቤቶ፤ለአምላከ ዮሐንስ፤ እስመ ኪያሃ አኃሥሥ ዘአፈቀረት ነፍስየ ፤ማኅደረ ስምከ ከመ ተሀበኒ ተምኔትየ፤ ኲሎ አሚረ።
@EOTCW
ወረብ
ምርሐኒ ፍኖተ ወእሑር ቤቶ ለአምላከ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ /፪/
እስመ ኪያሃ አኃሥሥ እስመ ኪያሃ አኃሥሥ ዘአፈቀረት ነፍስ ማኅደረ ስምከ/፪/
@EOTCW
ዓዲ ዚቅ
ይምርሐነ ፍኖቶ ለዘተወልደ እምድንግል፤
ያብዓነ ቤቶ ለዘሰከበ በጎል፤ ህየ ንሰግድ ኲልነ፤ለዘለብሶ ለአዳም፤ወለይእቲ ልብስ ዘንዝኅት በደም።
@EOTCW
@EOTCW
መልክአ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
ሰላም ለሕሊናከ ሀልዮ እከያት ዘኢለመደ፤
ወለአማዑቲከ ሐቅል በዋዕየ ፍቅረ ወልድ ዘነደ፤ ውስተ ኲለሄ ዮሐንስ ከመ ቃልከ አግሀደ፤ ሠለስተ አካላተ ወመለኮተ አሐደ፤ ሰባኬ ሃይማኖት እንበሌከ ኢነኃሥሥ ባዕደ።
@EOTCW
@EOTCW
ዚቅ
ወንጌለ መለኮት ሰበከ ስምዓ ጽድቅ ኮንከ፤ ወበእንተዝ አቡቀለምሲስ ተሰመይከ።
@EOTCW
@EOTCW
ወረብ
ስምዓ ጽድቅ ኮንከ ስምዓ ጽድቅ ኮንከ ወልደነጎድጓድ/፪/
ወበእንተዝ ተሰመይከ ተሰመይከ አቡቀለምሲስ/፪/
@EOTCW
ዓዲ ዚቅ
ሰባኬ ወንጌል መጋቤ ሃይማኖት፤ ቀዋሚሃ ለቤተክርስቲያን ፤ኮከብ ሥርግው ውስተ ሕፅነ ነድ ዘተሐጽነ በንጽሕ፤ ዘኅቡዕ ይኔጽር ምሥጢረ መለኮት፤ ዘመንክረ ይገብር እምኀበ መላእክት፤ ዮሐንስ ድንግል ባሕረ ጥበባት ፤መምህረ ሰላም ለአሕዛብ።
@EOTCW
መልክአ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
በሕማሙ ብዙኅ ለዮሐንስ እኁክሙ፤ወበመንግስትክሙ ዘክቡር ሱታፌክሙ ፤ሐዋርያተ ሕግ ንዑ በበፆታክሙ፤ ሃበ ተጸውዓ ዝክረ ትፍሥሕተ ልብ ስሙ፤ እስመ ዘአሀዱ ክርስቶስ አባላት አንትሙ
ዚቅ
ወዮሐንስ አሐዱ እምሐዋርያት፤ እምቅዱሳን ቀደምት እስመ በዲበ ሠናይቱ ለሰብእ ለሰብእ ተአዛዚ
@EOTCW
ወረብ
ወዮሐንስ አሐዱ እምሐዋርያት/፪/
እምቅዱሳን ቀደምት/፪/
@EOTCW
ምልጣን
ንዑኬ ጉባኤ ማኅበራ ለቤተክርስትያን ከመ ትስምዕዎ ለዮሐንስ ክቡር ወንጌላዊ ፤ዮሐንስ ታዎሎጎስ ዮሐንስ አቡቀለምሲስ ፤ዮሐንስ ዘረፈቀ ውስተ ሕፅኑ ለኢየሱስ።
@EOTCW
አመላለስ፦
ዮሐንስ ዘረፈቀ ውስተ ሕፅኑ/2/
ውስተ ሕፅኑ ለኢየሱስ/4/
@EOTCW
ወረብ
ንዑኬ ጉባኤ ማኅበራ ለቤተክርስቲያን ከመ ትስምዕዎ ለዮሐንስ ወንጌላዊ ክቡር/፪/
ዮሐንስ ታዎሎጎስ ዮሐንስ አቡቀለምሲስ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ/፪/
@EOTCW
እስመ ለዓለም
ሰባኬ ወንጌል ዮሐንስ አርጋኖነ ትንቢት፤ዘይደምፅ ለቤተክርስቲያን ፤ቀርን ነባቢ ዘይጼውዕ መሐይምናነ፤ ኮከብ ዘኤፌሶን ዓምደ ብርሃን ዘፍጥሞ፤መልአክ ዘበምድር ረዓዬ ምሥ
ጢር ፤ምዑዝ ከመ ጽንሐሕወ ከመ ዕጣን ንጹሕ
@EOTCW
አመላለስ
መልአክ ዘበምድር ረዓዬ ምሥጢር/፪/
ምዑዝ ከመ ጽንሐሕ ወከመ ዕጣን ንጹሕ/፪/
@EOTCW
@EOTCW
ወረብ
ሰባኬ ወንጌል ሐዋርያ ትንቢት ለቤተክርስቲያንዘይደምፅ ቀርን ነባቢ ለቤተክርስቲያን/፪/
ዮሐንስ ኮከብ ዘኤፌሶን ዓምደ ብርሃን ዘፍጥሞ መልአክ ዘበምድር ዘበምድር መልአክ/፪/
@EOTCW
ዓዲ እስመ ለዓለም
ሠረገላተ መሠለት ቤተክርስቲያን፤ እንተ
አርባዕቱ ገበዋቲሃ አርባዕቱ ወንጌላውያን፤ዘብእሲ ማቴዎስ ዘአንበሳ ማርቆስ ወዘላህምሉቃስ፤ ዘንሥር ዮሐንስ ዜናዊ፤ ዘልዑለ ይሠርርወይነግር በምሥጢር፤ ህላዌሁ ወሥጋዌሁለወልደ እግዚአብሔር።
https://t.me/Eotcw
#Join & share
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ የዕለቱ እግ.ነግ ዓራራይ ዜማ፦ "ባሕረ ጥበባት አበ ልሳናት ንስር ሠራሪ ልዑለ ስብከት ዮሐንስ ወንጌላዊ ረዓዬ ኅቡዓት ናገሩኒ ቅሱም በጼወ መለኮት"። ትርጉም፦ የጥበባት ባህር የልሳናት አባት በራሪ ንስር ስብከቱ የረዘመ ወንጌላዊ ዮሐንስ ምስጢርን ያየ (የሚያይ) በመለኮት ጨው ነገሩ የጣፈጠ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ ሃሌ ሉያ ፣ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ "ኮከበ ሰመይናከ ፀሓየ ጽድቅ ዘሐፀነከ ውስተ ሕፅኑ ዘአርፈቀከ ኮከበ ሰመይናከ፡፡ በአፉሁ ዘሰዐመከ ወበቅናቱ ዘአቅነተከ ኮከበ ሰመይናከ፡፡ ኅቡአቲሁ ዘአርአየከ ወንጌለ ጸጋሁ ዘአወፈየከ ኮከበ ሰመይናከ። ዮሐንስ መኑ ከማከ አስተምህር ለነ ሰአልናከ"። ትርጉም፦ ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ። ኮከብን ብለን ጠራንኽ፤ የጽድቅ ፀሓይ ያሳደገኽ ባጠገቡ (በጉያውም) ያስቀመጠኽ ኮከብን? ብለን ጠራንኽ፡፡ በአፉ የሳመኽ በመታጠቂውም ያስታጠቀኽ ኮከብን ብለን ጠራንኽ፡፡ የተሰወረውን ምስጢር ያሳየኽ የጸጋውን ወንጌል የሰጠኽ ኮከብን ብለን ጠራንኽ፡፡ ዮሐንስ እንዳንተ ያለ ማን ነው ታማልደን ዘንድ ማለድንኽ። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ጥር ፬ (4) ቀን።
❤ እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ሁል ጊዜ ዐርብ ዐርብ ያከፍሉ ለነበሩት የጌታችንን መከራ እያሰቡ አናታቸውን አቁስለው ሲተላ ትሉን ለወፎች ይመግቡ ለነበሩትና ዋሽራን ለ30 ዓመታት በሹመት ላገለገሉት ለታላቁ አባት ለአቡነ መልከጼዴቅ ዘዋሸራ ለዕረፍታቸው በዓልና ለጸሎት በመቆም ብዛት እግራቸው እስከ ማበጥ ለደረሰ በበትር ሳይመቱ በጥላቸው ብቻ ከይሲውን ለገደሉ ለታላቁ አባት ለአቡነ ናርዶስ ዘደብረ ቢዘን ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ አቡነ መልከጼዴቅ ዘዋሸራ፦ ከአባታቸው ከዘካርያስና ከእናታቸው ስነ ክርስቶስ የተወለዱት አቡነ መልከጼዴቅ ዘዋሸራ ትውልድ አገራቸው ጎጃም ዋሸራ ሲሆን በታላቅ ተጋድሎና በሹመት ያገለገሉትም በዚሁ፡ነው፡፡ ዲቁናንና ቅስናን ከግብፅ ተቀብለው በዋሽራ 30ዓመት በሹመት አገልግለዋል፡፡ ጻድቁ የሚታወቁበት ትልቁ ተጋድሎአቸው በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ሁል ጊዜ ዓርብ ዓርብ ያከፍሉ ነበር። የመድኃኔዓለምን 13ቱን ሕመማተ መስቀሎች በማሰብ አናታቸውን በድንጋይ እያቆሰሉ ቁስሉ ሲተላ ትሉን ለወፎች ይመግቡ ነበር፡፡ በ40ቀን ውስጥ አንዷን ቀን ብቻ ነው ውኃ ይጠጡ የነበረው፡፡ ጻድቁን የቅኔ ተማሪዎች በዋሸራ ይዘክሯቸዋል፡፡ ምንጭ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳን በዓላት።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
1 161
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ወበኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አዕርክቲከ እግዚኦ። ወፈድፋደ ፀንዑ እምቀደምቶሙ። እኌልቆሙ እምኆፃ ይበዝኁ"። መዝ 138፥17-18። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 6፥1-11፣ 1ኛ ዮሐ 1፥1-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 4፥8-24። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 21፥20-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ነው። መልካም የሐዋርያው የቅዱስ ዮሐንስ የስዋሬ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ጥር ፬ (4) ቀን።
❤ እንኳን ለከበረና ለተመሰገነ ለታላቁ ለወንጌላዊው፣ ለአቡቀለምሲስ፣ ለቦኤኔርጌስ፣ ለታኦሎጎስ፣ ለድንግላዊው፣ ለቊጹረ ገጽ፣ለፍቊረ እግዚእ፣ ለሐዋርያው ለቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ለፍልሰቱ (ከሞት ለተሰወረበት) ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበረ ከጊዮርጊስ፣ ከሊቀ ጳጳሳት ከማርቴና፣ ከሰማዕት ታኦድራ፣ ከአባ ሊቃኖስና ቀውስጦስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ንዑኬ ጉባዔ ማኅበራ ለቤተክርስቲያን ከመ ትሰምዕዎ ለዮሐንስ ክቡር ወንጌላዊ ዮሐንስ ቴዎጎሎስ ዮሐንስ አቡቀለምሲስ ዮሐንስ ዘረፈቀ ውስተ ሕፅኑ ለኢየሱስ፡፡ ትርጉም፦ የቤተክርስቲያን ማኅበር አንድነት የምትሆኑ ኑ ትሰሙት ዘንድ ክቡር የሚሆን ዮሐንስ ነባቤ መለኮት ስለመለኮት የተናገረ ዮሐንስ ባለራዕይ ዮሐንስ ከኢየሱስ ከአጠገብ የተቀመጠ። ሊቁ ቅዱሰሰ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ፦ ለዚህም ቅዱስ ወደ እስያ አገር ይሔድ ዘንድ ዕጣው በወጣ ጊዜ እጅግ አዝኖ አለቀስ እነርሱ ክፉዎች ከሀዲዎች ልባቸው የደነደነ መሆናቸውን አውቋልና ግን ጌታችን ኃይልን መጽናናትን አግኝቶ ከደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስ ጋር ወጥቶ ወደ ክፍሉ ሔደ። ወደ ኤፌሶንም ሊሔድ ወዶ በመርከብ ላይ ተሳፈረ መርከቡም ተሰበረ እየአንዳንዱ በመርከብ ስባሪ ሠሌዳ ላይ ተንጠለጠለ ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስንም የባሕሩ ማዕበል ወደአንዲት ደሴት አደረው ቅዱስ ዮሐንስ ግን በባሕሩ ማዕበል መካከል አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ኖረ።
❤ ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስ ወዳለበት ወደ የብስ ባሕሩ ተፋው ስለ መገናኘታቸውም እግዚአብሔርን አመሰገኑት በዚያን ጊዜም ተነሥተው ወደ ኤፌሶን ከተማ ገቡ ግን በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሰብኩ ዘንድ አልተቻላቸውም እነዚያ ያገር ሰዎች እጅግ የከፉ ናቸውና። ስለዚህም ምክንያት ፈጥረው ዮሐንስ ሮምና ለምትባል ሴት የውሽባ ቤት እሳትን የሚያነድ ሆነ ረድኡ አብርኮሮስም አጣቢ ሆነ ያች ሴትም እጅግ ታሠቃያቸው ነበር መጻተኞችም ስለሆኑ ታጐሳቁላቸዋለች ትደበድባቸዋለች ትረግማቸዋለች ባሮቿም እንደሆኑ ጽፈውላታልና ከእርሷ ባሮች አደረገቻቸው በዚህ በታላቅ ጒስቊልና ውስጥ ኖሩ።
❤ ከዚህም በኋላ በአንዲት ዕለት ይታጠብ ዘንድ የአገረ ገዥው ልጅ ገባ በዚያም የውሽባ ቤት ከተሠራ ጀምሮ የሰይጣን ኃይል አለ የመኰንኑም ልጅ አንቆ ገደለው በዚያንም ጊዜ የአገር ሰዎች ለዚያ ለሞተው ሊያለቅሱለት ተሰበሰቡ የከበረ ዮሐንስም እርሳቸው ጋር መጥቶ እንደ ሰው ሁሉ ሊያይ በዚያ ቆመ። ሮምናም በአየችው ጊዜ ረገመችው "አንተ በጌታዬ ልጅ ሞት ደስ ብሎህ ልትዝትብኝ መጣህ" አለችው ቅዱሱ ግን በቅንነት "አይዞሽ አትዘኝ" አላት ይህንንም ብሎ ወደ ሞተው ቀረብ ብሎ በመስቀል ምልክት አማተበበት በፊቱም ላይ እፍ አለበት። በዚያንም ጊዜ ያ የሞተው ድኖ ተነሣ የአገር ሰዎችም ደነገጡ ሮምናም "ወዮልኝ እግዚአብሔር የሚሉት አምላክ አንተ ነህን? አለች። እርሱም "አይደለሁም እኔ አገልጋይ ሐዋርያው ነኝ እንጂ" አላት በእነርሱ ላይ የሠራችውን በደል ሁሉ ይቅር ይሏት ዘንድ መሪር ልቅሶ በማልቀስ ሐዋርያትን ለመነቻቸው እነርሱም አረጋጓት አጽናኗትም።
❤ ከአገሩም ሰዎች ብዙዎቹ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው በፊታቸውም ብዙዎች የሆኑ ድንቆች ተአምራትን አደረገ ይህንንም አይተው የአገሩ ሰዎች ሁሉም በጌታችን አመኑ። ከጣዖታቱ አገልጋዮች በቀር እነርሱም ሰይጣን በእርሱ ላይ ስለሚያነሣቸው ሊገድሉት ይሹ ነበር ነገር ግን ምርጦቹን እግዚአብሔር ጠበቃቸው። የከበረ ዮሐንስም ሁሉንም እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ እስከመለሳቸው ድረስ ታላቅ ድካምና ጭንቅ የሆነ መከራ ደረሰበት። የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ልቡናቸው ደንዳናነት ጣዖታትን ስለመውደዳቸውም ስለ እነርሱ መስክሮአል። እርሱም ቅዱስ ዮሐንስ በታላቅ ድካም ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው። ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶሳትን፣ ቀሳውስትን፣ ዲያቆናትን ሾመላቸው። ከዚህም በኋኋ ከእስያ በዙርያዋ ወዳሉ አገሮች ሁሉ ወጥቶ አስተማረ እግዚአብሔርንም ወደማወቅ መለሰላቸው።
❤ ይህም የከበረ የተመሰገነ ቅዱስ ዮሐንስ በዚህ ዓለም ዘጠና ዓመት ኖረ እጅግም ሸመገለ ግን እንደ ባልጀሮቹ ሐዋርያት በሰይፍ ሞትን አልቀመሰም። ስለ ድንግልናውና ስለ ንጽሕናው ይህ ሆነ ሁሉም በክብር ይስተካከሉ ዘንድ እርሱም ወንጌልን ቀለምሲስ የሚባለውን ራእይ ሦስት መልክታትን የጻፈ ነው። ራት ሲበሉ በጌታ ኢየሱስ አጠገብ የተቀመጠውና "የሚያሲዝህ አቤቱ ማነው?" ያለው ይህ እርሱ ነው። ጌታችንም በተሰቀለ ጊዜ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር በመስቀሉ አጠገብ የቆመ እናቱንም "እነሆ ልጅሽ ያላት" እርሱን ደቀ መዝሙሩንም "እነኋት እናትህ" ያለው ነው።
❤ ቅዱስ ጴጥሮስም እርሱን ሲከተለው በአየው ጊዜ ስርሱ ጌታ ኢየሱስን "አቤቱ ይህስ እንዴት ነው?" ብሎ የተናገረ ጌታ ኢየሱስም "እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ከወደድኩ አንተ ምን አለህ አንተ ግን ተከተለኝ ያለለት" ይህ ነው።
❤ የተመሰገነ ቅዱስ ዮሐንስም ከዚህ ዓለም የሚወጣበት ሰዓት እንደ ቀረበ በአወቀ ጊዜ ሕዝቡን ጠራቸው ጸሎትንም ጸለየና ኅብስቱን ባርኮ ቆረሰ ይህም የጌታችን ሥጋውንና ደሙን ሰጣቸው በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አዘዛቸው ባረካቸው አጽናናቸውም።
❤ ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስን ከወንድሞችም ሌሎች ሁለቱን መቆፈሪያ ይዘው ይከተሉት ዘንድ አዘዘ። ከኤፊሶንም ከተማ ወጭ ወጣ ጒድጓድ እንዲቆፍሩም አዘዘ ከውስጥዋም ወርዶ ቆመ ልብሱንም አስወገደ ከአንድ የበፍታ ቀሚስ በቀር አላስቀረም። እጆቹንም አንሥቶ ጸለየና ወደ ከተማ ይመለሱ ዘንድ አሰናበታቸው በክርስቶስም ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ለሕዝቡ ይነግሩአቸው ዘንድ አዘዛቸው በጎ ሥራዎችንም ይሠሩ ዘንድ ጌታችን ለሁሉም እንደ ሥራው ይከፍለው ዘንድ አለውና።
❤ ሁለተኛም እንዲህ አላቸው "እኔ ከሁላችሁም ደም ንጹሕ ነኝ ከእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ ሳልነግራችሁ የተውኩት ምንም ምን የለምና እናንተም ከእንዲህ ከቶ ፊቶን አታዩኝም"። ይህንንም በተናገረ ጊዜ አለቀሱ እጆቹንና እግሮቹን ስመው በጒድጓዱ ውስጥ ትተውት ወደ መንደር ተመለሱና የሆነውን ሁሉ ለሰዎች ነገሩዋቸው ሁሉም ደንግጠው መጡ ግን ልብስና ጨማ እንጂ መቃብሩን አላገኙም እጅግም አደነቁ ደቀ መዝሙሩ ዮሐንስን በዚህ በጎ ዕረፍት ያሳረፈው እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ አባት በሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 4 ስንክሳር።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ"። ወእስከ አፅናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ18፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 4፥17-ፍ.ም።
1 161
50 የአቋቋም መምህራን በዛሬው ዕለት ተመረቁ!
በጎንደር ደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያም አብነት ምስክር ጉባኤ ቤት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ የአቋቋም ደቀ መዛሙርት በዛሬው ዕለት ተመርቀዋል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ምእመናን እና ምእመናት ተገኝተዋል።
ጥር 3 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ ጎንደር)
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለአባ ለሊባኖስ ዘበዐፅሙ ዱያን ይፌውስ፤ ዘበጠ ኰኵሐ በበትሩ ወአውሐዘ ማየ በጸሎቱ"። ትርጉም፦ በዐጥንቱ ሕሙማንን የሚፈውስ ሰላምታ የተገባው ሊባኖስ፤ በበትሩ ዐለቱን መትቶ በጸሎቱ ውሃን አመነጨ። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ የዕለቱ እግ.ነግ ዓራራይ ዜማ፦ "በእንተ ጽድቅ ወሕይወት ርእሶ ዘአንደየ እምሐውዘ ዓለም ዘጐየ በኀበ እግዚኡ ተዓሥየ ዐቢየ ብፁዕ ሊባኖስ ኃይለ ጸሎቱ አርአየ ዘቢጦ ኰኵሐ ወአውኃዘ ማየ"። ትርጉም፦ ስለ እውነት (ጽድቅ) እና ሕይወት ራሱን ድሃ ያደረገ ከዓለም ተድላ ደስታ የሸሸ በጌታው ዘንድ ተስተካከለ ንዑድ ክቡር የሆነ አባ ሊባኖስ የልመናውን (የጸሎቱን) ኃይል አሳየ አለቱን መትቶ ውኃን አፈለቀ። ሊቅ ቅዱስ ያሬድ።
+ + +
❤ "ሰላም ለ፲ወ፼ወ፵፻ ሕፃናት እለ ኢያርስሑ አልባሲሆሙ እለ አቅደሙ ተቤዝዎ እምግብጽ እለ ኢነበበ አፉሆሙ ቃለ ሐሰት እለ ያሐልይዋ ለይእቲ ማሕሌት እለ ቃሎሙ ከመ ቃለ መሰናቁት"። ትርጉም፦ ልብሶቻቸውን ያላሳደፋ፤ ከግብጽ አስቀድመው የተዋጁ፤ አፋቸው የሐሰት ቃልን ያልተናገረ፤ ያችን ማሕሌት የሚዘምሯት፤ ቃሎቻቸውም እንደ መሰንቆዎች ለኾኑ ለዐሥራ አራት እልፍ አራት ሺህ ሕፃናት ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ "ሰላም ለሕፃናት ዘቀተሎሙ ኄሮድስ። እንዘ ይመስሎ ምስለ እሉ ከመ ይትረከብ ክርስቶስ። ልበ አበዊሆሙ ነድ ወዘእሞሙ ከርሥ። ጊዜ አስተርአየ በመልዕልተ ገጸ ለየብስ። ሐሊበ አጥባት ምስለ ደም ሕውስ"። ትርጉም፦ ክርስቶስ ከእርሱ ጋር የሚገኝ መስሎት ሄሮድስ ለገደላቸው ሕፃናት ሰላምታ፤ ይገባል፤ ከደመ ጋር የተቀላቀለ የጡቶች ወተት በምድር ፊት ላይ በታየ ጊዜ የአባቶቻቸው ልቡ ነደደ፤ የእናቶቻቸው ኾድም። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 3።
https://t.me/Eotcw
