Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Ir al canal en Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Chat us! Buy ads: https://telega.io/c/consite
Mostrar más3 605
Suscriptores
-324 horas
-87 días
+630 días
Archivo de publicaciones
👉🏢በአዲስ አበባ ብቻ 141 ሰዎች በሕንፃ ግንባታ ሥራ ላይ በደረሰ አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ተገለጸ
🚧 ከ2015 እስከ 2017 በጀት ዓመት በተሰራ ጥናት መሠረት በሁለት ዓመት ውስጥ ብቻ 141 ሰዎች በሕንጻ የግንባታ ሥራ ላይ በደረሰ አደጋ ሕይወታቸው ማለፉን የአዲስ አበባ ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ለአሐዱ አስታውቋል።
👉 ሕይወታቸውን ያጡ ዜጎች በሁሉም የእድሜ ክልልና ፆታ የሚገኙ መሆናቸውን የገለጹት የባለስልጣን መስሪያቤቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አበበ እሸቱ ናቸው።
▪️በተደረገው ጥናት መሠረት የሞታቸው መንስኤ ተብለው የተለዩት፤ የመጀመሪያው ጥንቃቄ ባልተሞላበት መንገድ የደህንነት ቀበቶ፣ ጫማ እና ኮፍያ የመሳሰሉትን ሳያደርጉ ሲሰሩ የነበሩ ሠራተኞች ከከፍታ ላይ መውደቃቸው ስለመሆኑ ተናግረዋል።
ከዚህ ሌላም በግንባታው ቦታ ላይ በሚያጋጥም የኤሌክትሪክ አደጋ ሲሆን፤ የተላጠ ኤሌክትሪክ በሚይዙበት ወቅት ወይም መብራት ሳያጠፉ በሚሰሩበት ጊዜ የሚከሰት እንደሆነ ተናግረዋል።
▪️በተጨማሪም ከላይ ብሎኬት ወይም ድንጋይ በመውደቁ ከሥር ያለውን ባለሙያ ሔይወት ያጠፋበት ሁኔታ ስለመኖሩ ም/ዋና ዳይሬክተሩ አንስተዋል።
▪️ሕይወታቸውን ካጡ ዜጎች መካከል አብዛኞቹ የሕንፃ ግንባታ ሠራተኞች መሆናቸውን አንስተው፤ አንዳንዶች ግን ህንፃውን ለመጎብኘት ወይም ለመግዛት የሚሄዱ ሰዎች ላይ ጭምር አደጋው መከሰቱን ገልጸዋል።
ም/ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም እነዚህ አደጋዎችም በቀላሉ ጥንቃቄ ቢደረግ ኖሮ መከላከል እና የሞት አደጋን ማስቀረት የሚቻልበት ሁኔታ እንደነበረ አስረድተዋለ።
🏢በመሆኑም የሕንፃ ግንባታ ደህንነትን በተመለከተ በሰፊው እየተሰራ በሚገኝበት በዚህ ወቅት፤ ከበፊቱ የሞት አደጋ እየቀነሰ ስለመምጣቱ ተናግረዋል።
+4
ብርሃን ባንክ ሰንጋተራ ጎማ ተራ አካባቢ ተሰማ አባ ቀናው መንገድ ላይ ለሚያስገነባው የሽግግር ዋና መስሪያ ቤት የአርክቴክቸር ዲዛይን ውድድር Yema Architecture ያቀረበው ዲዛይን አሸናፊ ሆኗል።
በውድድሩ ሁለተኛ Jdaw Consults ሦስተኛ Addis Mebratu አራተኛ Geretta ሲሆን፤ አምስተኛ Biybone consultings ናቸው።አሸናፊው Yema Architecture ባለፈው ማክሰኞ በብርሃን ዋና መሥሪያ ቤት ስምምነት ሊያደርግ ችሏል። Yema Architecture የተቋቋመው እኤአ በመስከረም 2007 ዓ.ም በአዲስአበባ ውስጥ ሲሆን፣ ትኩረት አድርጎ የሚሠራው በአረሰክቴክቸር፣ በኢንጂነሪንግ፣ በኢንቴሪየር ዲዛይን እና በፕሮጀክት ማኔጅመንት ዙሪያ ነው። t.me/infraconmedia
👉 INTERCON Construction Chemicals
● Concrete Admixtures
● Bonding Agents
● Waterproofings
● Wall Putty, Prime Coat
● Concrete Repair Mortar
● Floor hardener, Epoxy
● Grout, Self-level mortar
● Quartz paint, Contextra
● Tile Adhesive & Tile Joint Fillers
● Geotextiles and other construction chemicals and materials
Tel: 0961955555
Address: Signal, around signal mall
#ADVERTISEMENT
🔧📐📐ፀግሽ ፕሌት እና ጄቦልት 📐📐
መማምረቻ ድርጅት⚙🔧🛠
🛠🛠🛠የምንሰጣቸው አገልግሎቶች🛠🛠🛠
1 መገለጫችን የሆነው የሞደፊክ ስራዎች
2 እዲሁም ፕሌት ከ 1ሚሊም እስከ 30 ሚሊም እንቆርጣለን እበሳለን
3 በመቀጠል ጄቦልት 12ሚ እስከ 32ድረስ ጥርስ አውጥተን አጥፈን እናቀርባለን
4 የተለያዩ ቦልቶች በፈለጉት መጥን
📍 አድራሻ መገኛችንቁ1. በእጆት ባለ ስልክ ለናተ ቅርብ ቁ2. በታታሪዎች መገኛ ኮርቻ ተራ ቁ3. አየር ጤና ኪዳን ምህረት ጊቢ ማንኛውም ልሜራ እዛው በዘመናዊ ማሽን እቆርጣለን ቁ4. ሴሚት ፍየል ቤት በቅርባ ባራቱም አቅጣጫ ማሳሰብያ ከጊዜው አንፃር የዋጋ ንረት ካሳሰቦት እኛጋ እሚገርም መፍትሄ አለ በማያስቡት መልክ ስራዎን ይሰራሉ ይደውሉ ስልክ ቁጥር☎️ 📞0912492727 📞0913061530 📞0923764834 መልካም ስራ ለራስ ነው ቸር ይግጠማቹ ፀግሽ ፕሌት እና ጄቦልት!
+3
ማስታወቂያ:-NAYHAf Construction Metal Trading- አቅራቢ🏗 ጥራትና ታማኝነትን የተላበሰ አገልግሎት" ከደንበኞች አብዛኛሆቻችሁ ታውቁታላችሁ
መገኛ አድራሻው ቦታ:-📍- ተክለሃይማኖት በርበሬ በረንዳ
ስልክ ቁጥር:-🔺📞+251- 944454610 🔺📞+251- 952730999 #LTZ 28 #LTZ 38 #LTZ 48 #CHS ከ ባለ 12mm ጀምሮ .... #RHS #I BEAM #U CHANNEL #H BEAM #Mesh Wire #የ ኣጥር ሽቦ #Galvanized Pipe #Angle #Aluminium Sheet #D ብረት#8 ቁጥር #ፌርሞችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ! ስትፈልጉ በቀጥታ ይደውሉ.. .
🏢በግንባታ ሳይቶች የደህንነት ባለሙያ ምደባ ግዴታ ሊሆን ነው!
- በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ለሚፈጠሩ የደህንነት ስጋቶችና አደጋዎች አንዱ መንስኤ በቂ የግንባታ የደህንነት ባለሙያ ባለመኖሩ በመሆኑ፣ ይህንን ችግር ለመቅረፍ በአዲስ አበባ በግንባታ ሳይቶች ላይ የደህንነት ባለሙያ እንዲኖር እንደሚደረግ ተጠቁሟል።
- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ግንባታ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከአጋር አካላት ጋር በመሆን ለ3 ቀናት የሚቆይ የግንባታ ደህንነት ስልጠና መሰጠት ጀምሯል።
- በስልጠና ማስጀመሪያው የተገኙት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ፣ አዲስ አበባን እንደ ስሟ አዲስ፣ ለደህንነት የተመረጠችና ዘመናዊ ከተማ የምናደርጋት የኮንስትራክሽን ዘርፍን ይዘን ነው ብለዋል።
- በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚሰማራ ዜጋ ሁሉ፣ ከአደጋ የፀዳ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የሥራ ቦታ እንዲኖረው ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገልፀዋል።
- በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ለሚፈጠሩ የደህንነት ስጋቶችና አደጋዎች አንዱ መንስኤ በቂ የግንባታ የደህንነት ባለሙያ ባለመኖሩ እንደሆነ ተገልጿል።
- ይህንን ችግር ለመቅረፍ በቀጣይ በአዲስ አበባ በግንባታ ሳይቶች ላይ የደህንነት ባለሙያ እንዲኖር እንደሚደረግ ተጠቁሟል።
- በተያዘው በጀት ዓመት ግንባታ ላይ የሚሠሩ ሁለት ሺህ ዜጎችን ስልጠና ለመስጠት መታቀዱ ተገልጿል።
- ሰልጣኞች በበኩላቸው፣ የሥራ ላይ ደህንነትን ለማስጠበቅ ያለመ ስልጠና መሰጠቱ የሠራተኞችን ደህንነት ከመጠበቁ ባሻገር ከተማዋ ያለመችውን የግንባታ ጥራት ማስጠበቅ ይችላል ብለዋል።
(AMN)
+7
♦️ያዶን ♦️
የኮንስትራክሽን ዕቃ አቅራቢ ድርጅት
▪️◽️◽️▪️◽️◽️▪️
አስተማማኝ ጥራትና ጥንካሬ ያላቸውን የብረታ ብረት ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እና ከአስተማማኝ አቅርቦት ጋር ይዞ መጥቷል፤
🔹 ከምንይዛቸው ብረታ ብረት ምርቶች መካከል፦
▪️◽️ቱቦ ላሬ፦ ክብ ቱቦ፣ RHS, SHS, CHS
በተፈለገው ውፍረት (thickness)
▪️◽️LTZ profiles
28/38/48 (በተፈለገው thickness, size)
▪️◽️ ላሜራ (Sheet Metal)
🔹ኦቨር ሳይዝ (Oversize)
🔹 ሸካራ (Cqeuerd)
🔹 ልሙጥ
🔹 2*1m
🔹 3*1m
በተፈለገው ውፍረት (thickness)
ካልሆነም በትዕዛዝ በተፈለገው ሳይዝ እንቆርጣለን፤
🔹 አንጉላሬ (Angle)
በተፈለገው ውፍረት (thickness)
🔹 ድፍን ብረቶች
ቶንዲኖ እና ኳድሮ (Round Bar and Squire Bars)
🔹 U channel and I section
🔹
ለማንኛውም የብረታ ብረት ምርቶች ይደውሉልን፤ 0916416641 0931246190 የቴሌግራም ግሩፖችንን ይቀላቀሉ t.me/yadonco
🔲🏢 የኮንስትራክሽን ኢንደስትሪውን ቁልፍ ችግር በአጭር ጊዜ ለመፍታት አዎንታዊ ለውጥ ለማምጣት እንዲያስችል ታስቦ በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የተቋቋመው ኢንደስትሪውን ተዋናዮች በውስጡ ያቀፈው የኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢንሼቲቭ ማስጀመርያ መርሀ ግብር ዛሬ ነሀሴ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ ይገኛል።
+5
China porcelain ceramic
80x80cm
60x60cm
60x120 available
0911798889
🚪ለኮንዶሚንየም ዋና በሮች ተዘጋጅቶ ለደንበኞች የቀረበ ለአስቸኳይ በር ፈላጊዎች በቅናሽ ዋጋ:-
👉ቀኝ እና ግራ ተካፋች
✴️በ 1ቀን ውስጥ ወስደው መግጠም ይችላሉ
🔩ከተሟላ Accessory ጋር እንዲሁም ገጠማ በነፃ ::
💵 65,000 birr
አሁኑኑ አዘው አሁኑኑ ይውሰዱ።
+251912288223
በ አካል ማመልከት ለምትፈልጉ መስቀልፍላወር ጋዜቦ አደባባይ ወደ ደምበል ህንፃ ፓርኪንግ ወደሚወስደው መንገድ ቪስኮ ሪል እስቴት 5ኛ ፎቅ ዲኤ ኮንስትራክሽን
በ 0911222467 ይደውሉ
ኦገስት 15 ማመልከቻው ይጠናቀቃል
የ ስራ ቅጥር ማስታወቂያ | Vacancy
ዲኤ ኮንስትራክሽን | DA construction
📞 +251 91 122 2467
ፌሮ ብረት Vs አርማታ
[Reinforcement bar Vs Concrete mix] @consite🏗
- የኮንክሬት መዋቅር (Concrete Skeletons) የተለያዩ የግንባታ ግብአቶችን የሚጠቀሙ ቢሆንም በአብዛኛው የተለመደው የፌሮ ብረት እና የአርማታ ሙሌት ያለው መዋቅር ነው።
ይህ አይነቱ ስትራክቸር «Reinforced Concrete Structure ወይም ባለፌሮብረት የአርማታ ውቅር» ተብሎ ይጠራል።
በመሆኑም እነዚህ ሁለት ዋና ዋና የግንባታ ግብአቶች (ፌሮ ብረት እና አርማታ) ለውቅሩ የየራሳቸው የሆነ አስፈላጊ ጥቅም አላቸው።
ከዚህ አንጻር፦👇- የፌሮ ብረት (Reinforcement bar) በባህርዩ ተለጣጭ አይነት ባህርይ ስላለው በኮንክሬት ውቅሩ ላይ የሚተገበረውን ጫና (load) በቀላሉ እንዳይፈረካከስ በማድረግ እና ባለው ወጥነት የተነሳቭየተወሰነ የመለጠጥ ነጻነትን (Ductile Property) በማበልጸግ የመለጠጥ ጥንካሬን (Tensile Strength) እንዲኖረው ያደርጋል። በዚህ አግባብ የአርማታ ውቅሩ Tension ላይ ልዩ የመቻል አቅም እንዲኖረው የሚያደርግ ግብአት ነው፡ - አርማታ (Concrete Mix) በፌሮ ብረት መዋቅሩ ውስጥ እና ዙሪያ የሚሞላው አርማታ ደግሞ የኮንክሬት መዋቅሩ (Concrete Structure) የመኮማተር አቅም (Compressive Strength) እንዲኖረው የሚያደርግ ነው። በመሆኑም አርማታ በመዋቅሩ ላይ የሚተገበረው ጫና በአንጻራዊ ስፋት ላይ አርፎ ማዕከላዊ የፍሰት ሥርዓትን (Centerline load transfer system) ተከትሎ እንዲፈስ የሚያስችል የመድረቅ ወይም የመኮማተር ሂደትን የሚይዝ ነው። - ማጠቃለያ፦ አርማታ ጠንካራ የማይለጠጥ ጸባይ ስላለው ፌሮ ካልገባበት ጫና ሲበዛበት የመሰበር ወይም የመቀንጠስ አደጋ ይገጥመዋል። ፌሮ ብረትም ብቻውን ቢሆን የመለጠጥ ጸባይ ስላለው አርማታ ባይኖርበት ተጣጥፎ ይተኛል ወይም ጎብጦ ይቀራል እንጂ ራሱን ችሎ ደረቅ መዋቅር የመሆን አቅሙን አያስቀጥልም። በመሆኑም አርማታ ብቻውን ቢሆን ወይም አርማታው በዝቶ ፌሮ ብረት ካነሰ የመለጠጥ አስፈላጊ ባህርዩን ስለሚያጣ «Tensile Failure» ይገጥማል። በተቃራኒው ፌሮ ብቻውን ከሆነ ወይም ፌሮ በዝቶ አርማታ ካነሰ "Compressive Failure" ይከሰታል ማለት ነው።
ለግዙፉ የአውሮፕላን ማረፊያ የፋይናንስ አቅርቦት
***
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቢሾፍቱ አቅራቢያ አቡሴራ አካባቢ አዲስ የሚያስገነባው ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲጠናቀቅ 110 ሚሊዮን ደንበኞችን ማስተናገድ እንደሚያስችል ተመላክቷል።
ለዓለም አቀፍ አየር ማረፊያው ግንባታ የሚያስፈልገው ፋይናንስ ከየት ይገኛል?
ለግዙፉ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ 10 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር እንደሚያስፈልግ ያሳወቀው አየር መንገዱ፤ ፋይናንሱን እንዲያፈላልግ የአፍሪካ ልማት ባንክን መርጧል።
ለዚህም እንዲረዳው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር ዛሬ ስምምነት አድርጓል።
ተቋማታቸውን ወክለውም የአየር መንገዱ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር ለማ ያደቻ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ ፕሬዝዳንት አኪንዉሚ አዴሲና (ዶ/ር) የፊርማ ሥነ ስርዓቱን አከናውነዋል።
የአየር መንገዱ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ እና የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ እንዲሁም የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ በተገኙበት የተደረገው ስምምነት የተለያዩ አሰራሮችን የያዘ ነው።
በስምምነቱ መሰረት አየር መንገዱ ለፕሮጀክቱ ከሚያስፈልገው 10 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ውስጥ የአፍሪካ ልማት ባንክ 80 በመቶውን ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት የማፈላለጉን ኃላፊነት ወስዷል።
ለፕሮጀክቱ ከሚስፈልገው ወጪ 20 በመቶ የሚሆነውን ደግሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚሸፈን ይሆናል ተብሏል።
በሁለት ምዕራፍ የሚገነባው አዲሱ የአቡሴራ የአውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት እጅግ ዘመናዊ ሲሆን፤ በዓመት ከ110 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን በተሻለ ፍጥነት ማስተናገድ እንዲችል ተደርጎ እንደሚገነባም ነው የተገለፀው።
ፕሮጀክቱ በሚያርፍበት ስፍራ ለሚኖሩ 2500 አርሶ አርሶ አደሮችን በዘላቂነት ለማቋቋም በ350 ሚሊየን አሜሪካ ዶላር የመኖሪያ ቤት እና የመስሪያ ቦታ ግንባታ እየተጠናቀቀ መሆኑንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል።
ከአዲስ አበባ በ40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገነባው እጅግ ዘመናዊው የአውሮፕላን ማረፊያ በ3975 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ሲሆን፤ በ2018 ዓ.ም ግንባታው እንደሚጀመር ይጠበቃል።
በላሉ ኢታላ 👈
