es
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Ir al canal en Telegram

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service

Mostrar más
3 587
Suscriptores
-224 horas
+27 días
+3030 días
Archivo de publicaciones
የግንባታ ስራ ተቆራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 <<ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 28 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply &nbsp
የግንባታ ስራ ተቆራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 <<ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 28 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply   ----------- ጨረታ | bid ----------- ዩኒቲ ኮንስትራክሽን ስራ ኦፊሻሎች

Bill of Quantities Civil Engineering Civil Engineering.xls7.07 KB

የግንባታ ስራ ተቆራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 &lt;&lt;ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 28 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply &nbsp
የግንባታ ስራ ተቆራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 <<ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 28 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply   ----------- ጨረታ | bid ----------- ዩኒቲ ኮንስትራክሽን ስራ ኦፊሻሎች

የግንባታ ጨረታ ማስታወቂያ የገዋኔ ግብርና /ቴ.ሙያ ስልጠና ኮሌጅ የተለያዩ የግንባታ ስራዎች መስፈርቱን የሚያሟሉ ተቋራጮችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል። ተጫራቾች ለሥራው ህጋዊ ፈቃድ ኖሯቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ከሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ፣ የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ያላቸው የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸው፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምስክር ወረቀት ያላቸው ከመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን የተመዘገቡ ምስክር ወረቀት ያላቸው፣ የ2015 ዓ.ም ንግድ ፈቃድ ያሳደሱ ተቋራጮች መሆን ይጠበቅባቸዋል።ተጫራቾች ዋናውንና ኮፒ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል። ከላይ በተጠቀሰው በግልጽ ጨረታ ለመሳተፍ ሎት 1 DORMIIARY BLOCKS ግንባታ ስራ ተቋራጭ ደረጃ GC-4 ወይም BC-4 እና ከዚያ በላይ መሆን ይኖርባቸል። በሎት 2 CAFTERIA AND MEETING-HAI BLOCKS ግንባታ ስራ ተቋራጭ ደረጃ GC-5 ወይም BC-5 እና ከዚያ በላይ መሆን ይኖርባቸል:: በሎት 3 REMAINING WORKS FOR POULTRY FARMING BLOCKS ተቋራጭ ደረጃ GC-7  ወይም BC-7 እና ከዚያ በላይ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ 3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከኮሌጁ ግዥና ሽያጭ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ድረስ በመምጣት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 21 (ሃያ አንድ) ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 1,000 (አንድ ሺ ብር) በመክፈል መውሰድ ይኖርባቸዋል። 4. ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነድ አንድ ኦሪጅናል እና አንድ ኮፒ ፋይናንሽያል ሰነድ አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ በድምሩ አራት ሰነድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። በተጨማሪም በሰም የታሽገውን 4 ፖስታ የፋይናንሽያል ሰነድ ሁለቱን ፖስታ በአንድ ፖስታ በማሽግ እና ቴከኒካል ሰነድ ሁለቱንም ፖስታ በአንድ ፖስታ በማሸግ ሁለቱን ፖስታና የCPO ፖስታውን በአንድ እናት ፖስታ በማሽግ የድርጅቱን ማህተም እና የሚወዳደሩበትን የስራ አይነት ስም በመጻፍ በሰም ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል። ሰነዱን ከላይ በተጠቀሰው ቢሮ በኮሌጁ ግዥና ሽያጭ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ በሚገኘው የጨረታ ሳጥን በ22ተኛ (ሃያ ሁለተኛው) ቀን እስከ ጠዋት 4፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ የጨረታ ሰነዱን ቴክኒካል ሰነድ /technical proposal/ / እና ፋይናንሻል ሰነድ /financial proposal / ማስገባት ይኖርባቸዋል። 5. በዚሁ ቀን ጠዋት 4፡30 ሰዓት ላይ የቅድመ ብቃት/technical proposal በኮሌጁ ግዥና ሽያጭ ንብረት አስተዳደር ዳይሬከቶሬት ቢሮ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (BID BOND or BID SECURITY) ለሎት 1 እና ሎት 2  (200,000 ብር) ሎት 3 (20,000 ብር) በባንክ የተረጋገጠ (CPO) (ገዋኔ ግብርና ቴ/ሙያ ስልጠና ኮሌጅ ስም ማስያዝ ይኖርባቸዋል። 7. ኮሌጁ ባወጣው የግንባታ ጨረታዎች ከአንድ ሎት በላይ መሳተፍ አይቻልም። በተጨማሪም ተጫራቾች ሞልተው ያስገቡትን ሰነድ በሁሉም ገፆች ላይ ማህተም እና ፊርማ አለማድረግ፣ የሥራ ዝርዝር ዋጋ (Rate) ላይ የማይነበብ እና ያልተፈረመበት ስርዝ ድልዝ ካለ 1 ዋጋ (Rate) ያልተሞላለት የስራ ዝርዝር እንዲሁም የስራ ዝርዝር ዋጋ (Rate) ላይ ፍሉድ መጠቀም ከተወዳዳሪነት ያሰርዛል። 8. የበለጠ ማብራሪያ ካስፈለገ በኮሌጁ ግዥና ሽያጭ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ በአካል በመቅረብ መረዳት ይቻላል። 9. ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ማሳሰቢያ- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜ፣ እሁድ ወይም የበአል ቀን ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን ላይ የሚከፈት ይሆናል። የገዋኔ ግብርና ቴ/ሙ/ት/ሰ ኮሌጁ (ገዋኔ አፋር)                                                                                                                       

INVITATION FOR TENDERING IFB No. ECWCT/NCB/PG-89/2015 1. The Ethiopian Construction Works Corporation (ECWC) hereby invites registered eligible bidders for supply of ALUMINUM & PVC MATERIALS 2. Interested Potential Bidders are required to present renewed relevant Trade License for the Ethiopian fiscal year, VAT Registration Certificate, Tax Clearance Certificate and Online Supplier list Registration Certificate together with their offer. 3. Bidding document should be prepared in English language. 4. Interested Potential Bidders obtain a complete set of bidding document from the office of Procurement Department against payment of none refundable fee of Birr 300.00 upon presentation of Trade License renewed for the fiscal year. 5. This invitation of bid is open to all interested potential bidders regardless of their nationality and the bid evaluation and award shall be determined in accordance with the provision indicated in bidding document. 6.  The deadline for bid Submission shall be on February 17, 2023, at 02:30 P.M. 7. Bid must be accompanied with a Bid Security of an amount of Birr Birr 300,000.00 ETB (Three hundred thousand) in the form of certified cheque (CPO) or Bank guarantee. Bid Bond in the form of insurance bond or in any other form shall not be accepted. 8. Bids must be delivered or deposited in the Tender Box situated at the office of the Procurement Department on February 17, 2023, at 03:00 P.M. in Ethiopian Construction Works Corporation Procurement Department conference room, in the presence of bidders and/or their representatives who choose to attend. 10. The Ethiopian Construction Works Corporation reserves its rights to reject any or all bids. 11. Bidders may get further information at the following address: Ethiopian Construction Works Corporation Address: - Gurd shola behind Athletics Federation Building In front of Andinet International school Telephone No.011 8 72 29 58/ 0118 72 30 86/011 896 29 91

የግንባታ ጨረታ ማስታወቂያ የደ/ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ የግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ቡድን     ደ/ብርሃን ከ/አስ/ምኒሊክ አረንጓዴ ልማት ፓርክ ግንባታ ስራ በፓኬጅ ቁጥር D/Birhan/cw 09/2021/22 በከተማ ከተመደበ በጀት ደረጃ 1 ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ (GC) ወይም በህንፃ ስራ ተቋራጭ (BC)     ደ/ብ/ከ/አስ/G+7 የቢሮ ግንባታ ስራ በፓኬጅ ቁጥር D/Birhan/cw-10/2022/23 በከተማ ከተመደበ በጀት ደረጃ 2 እና በላይ የሆኑ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ (GC) ወይም በህንፃ ስራ ተቋራጭ (BC) ያላቸውን ተወዳዳሪዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል። ስለዚህ በዘርፉ ፈቃድ ያላቸው እና የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎች በጨረታ መሳተፍ ይችላሉ።     2015 በጀት ዓመት የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው     የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር/Tin Number/ ያላቸው     የግዥ መጠኑ ከብር 200,000/ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆኑ የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል     ተጫራቾች የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፡፡     ተጫራቾች ከአማራ ክልል ውጪ የንግድ ስራ ፍቃድ ያላቸው ከሆነ የፌዴራል የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።     ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከተራ ቁጥር 1-5 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ከዋናው ጋር የተገናዘበ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻው ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::     ተጫራቾች የመጫረቻ ዋጋቸውን መ/ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ ሞልተው ማቅረብ አለባቸው።     የግንባታ ስራውን ዝርዝር መግለጫ /Specification/ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ።     በጨረታው ሰነድ ላይ ስርዝ ድልዝ ካለ ከውድድር ውጪ ይሆናል፡፡     ተጫራቾች ከአንድ ሎት በላይ መጫረት አይፈቀድም ::     ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ከግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ቡድን 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 10 ድረስ በመምጣት ለእያንዳንዱ ጨረታ የማይመለስ ብር 1000 /አንድ ሺህ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ገዝተው መጫረት ይችላሉ።     ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት 500,000/አምስት መቶ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና/ጋራንት/ በስማቸው ለደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማት ቤቶችና ኮንስትራክሽን አገልግሎት ጽ/ቤት በሚል አድራሻ ለብቻው በፖስታ በማሸግ ማቅረብ አለባቸው፡፡     ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን ቴክኒካልና ፋይናንሽያል በማለት ለየብቻው በማድረግ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በደ/ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 8 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስታወቂያው በጋዜጣ በግልፅ ጨረታ ከወጣበት እለት ጀምሮ በ30 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡     ጨረታው በጋዜጣ ግልፅ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ31ኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በደ/ብ/ከ/አስ/ከ/መ/ል/መምሪያ ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 8 በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ እለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡ ዕለቱ ቅዳሜ ፣ እሁድ ወይም የህዝብ በዓላት ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቾች በራሳቸው ምክንያት ባይገኙ የጨረታው ፖስታ ተሟልቶ ከተገኘ እንዲከፈት በማድረግ ውድድሩ ይካሄዳል፡፡     አሸናፊው ተጫራች ውጤት ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ከ5 የስራ ቀን በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀን ውስጥ የሚፈለግበትን ማስረጃዎች በማቅረብ ውለታ መፈፀም ይኖርበታል፡፡     በጨረታው አሸናፊ የሆነ የውል ማስከበሪያ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ /10%/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ/ሲ.ፒ.ኦ./CPO/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርበታል፡፡     መ/ቤቱ 20 በመቶ ጨምሮ ወይም ቀንሶ መዋዋል ይችላል፡፡     መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ወይም አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት አለው።     በማስታወቂያው ያልተገለፁ ነገሮች ቢኖሩም በግዥ መመሪያው መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡     ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት በስልክ ቁጥር፡-011 681 2717/28 57 ላይ በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡ የደ/ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ የግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ቡድን

የግንባታ ጨረታ ማስታወቂያ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 የበጀት ዓመት ከመንግስት በተመደበለት በጀት G+0 Students Cafe Building @ Burie Campus በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ ከዚህ በታች የተገለጹትን ማለትም፡ በዘመኑ እና በዘርፉ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ እና የግብር ከፋይነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ። ለስራ የሚያስፈልገውን የሰው ሀይል ማቴሪያልና ማሽነሪዎችን ሙሉ በሙሉ በራሱ አቅርቦት መስራት የሚችል እና በደረጃ BC-4 GC-5 እና ከዚያ በላይ የግንባታ ስራ ፈቃድ ያላቸው ሁሉ መወዳደር ይችላሉ። ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ሞልተው ሲመልሱ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000.00 /አንድ መቶ ሺህ ብር ብር/ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ስም አሰርተው ማቅረብ ሲኖርባቸው ፤ በጥቃቅን የተደራጁ ከአዳራጃቸው የመንግስት መ/ቤት የዋስትና ደብዳቤ በደብረ ማርቆስ ዪኒቨርሲቲ ስም በማሰራት ማቅረብ አለባቸው፡ ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች ሁሉ የጨረታ ዶክመንቱን ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ህንፃ ቁጥር 27 ቢሮ ቁጥር 10 ወይንም አዲስ አበባ 4 ኪሎ ከቅድስት ማሪያም ቤ/ክርስቲያን ወረድ ብሎ ሮሚና ካፌ ላይ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 7 ከሚገኘው ቢሮአችን ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 ተከታታይ ቀናት የማይመለስ ብር 200.00/ሁለት መቶ ብር / በመክፈል መግዛት ይችላሉ። የጨረታውን ዶክመንት አስተማማኝ በሆነ ማጣበቂያ በታሸገ ፖስታ በማድረግና በፖስታ ላይ የአሰሪ መስሪያ ቤቱንና የድርጅቱን መሉ ስምና አድራሻ በመጻፍ ፊርማና ማህተም በማድረግ ማቅረብ አለባቸው። የጨረታውን ፋይናሽያል ኦሪጅናል ዶክመንቶች ፣ ቴክኒካል ሰነዶችን እንዲሁም የጨረታ ማስከበሪያውን ለየብቻ አስተማማኝ በሆነ ማጣበቂያ በታሸገ ፖስታ በማድረግ በተጠቃለለ አንድ ፖስታ በማሸግ ማቅረብ ሲኖርባቸው ፤ ፋይናሽያል ዶክመንቶች ከኦሪጅናሉ በተጨማሪ አንድ ኮፒ ማቅረብ አለባቸው። አሸናፊው ድርጅት አሸናፊነቱ በተገለፀለት ከ7 ተከታታይ የስራ ቀናት በኋላ በግንባር ቀርቦ አሸናፊ የሆነበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በማስያዝ በ8 ቀን ውስጥ ውል መያዝ የሚችል ሆን አለበት ተወዳዳሪዎች የጨረታ ሰነዱን በአግባቡ በመሙላትና በማሸግ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከተከታታይ 21 ቀናት በኋላ  በ22ኛው ቀን ከጥዋቱ 3:59 ድረስ ደብረ-ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ህንፃ ቁጥር 27 ቢሮ ቁጥር 10 ድረስ በመቅረብ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ሲኖርባቸው ጨረታው በዚሁ ዕለት  ከጠዋቱ 3፡59  ሰዓት ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4፡30 ይከፈታል። ነገር ግን በካላንደር የተዘጋ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል። በጨረታው መክፈቻ ዕለት ተጫራቾች መገኘት ካልቻሉ መስፈርቱን እስካሟሉ ድረስ በጨረታው ላይ ተጫራቾችን ፖስታ ጨምሮ በዕለቱ ይከፈታል። የበለጠ መረጃ ለማግኘት  በስልክ ቁጥር 058 771 6691 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ። ዩኒቨርሲቲው ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

በድጋሚ የወጣ የግንባታ የጨረታ ማስታወቂያ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከመንግስት በተመደበለት በጀት የዋናው ካምፓስ የዉሃ መስመር ዝርጋታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል። ስለሆነም ሥራውን ለሥራት የሚፈልጉ ተጫራቾች፡ -      በዘመኑ የታደሰ ንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታከስ እና የቲን ምዝገባ የምስክር ወረቀት ከሚመለከተው     የመንግስት አካል ማቅረብ የሚችሉ፣     ለሥራ የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል፣ ማቴሪያልና ማሽነሪዎችን ሙሉ በሙሉ በራሱ አቅርቦ መሥራት የሚችል እና በደረጃ WC-1/GC1 እና ከዚያ በላይ የግንባታ ሥራ ፈቃድ ያላቸው ሁሉ መወዳደር ይችላሉ፣ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ዋጋ ሞልተው ሲመልሱ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 500,000.00/አምስት መቶ ሽህ/ ብር በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ስም አሠርተው ማቅረብ ሲኖርባቸው በጥቃቅን የተደራጁ ከአደራጃቸው የመንግስት መ/ቤት የዋስትና ደብዳቤ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከም በማሠራት ማቅረብ አለባቸው።     አሸናፊው ተጫራች አሸናፊነቱ በተገለፀለት ከ7/ሰባት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት በኃላ በግንባር ቀርቦ አሸናፊ የሆነበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በማስያዝ በI ቀናት ውስጥ ውል መያዝ የሚችል ሆን አለበት።     ከላይ የተዘረዘሩትን ስፈርቶች የሚያሟሉ ሥራ ተቋራጮች ሁሉ የጨረታዶhመንቱንደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ህንፃ ቁጥር 27 ቢሮ ቁጥር 10 እና አዲስ አበባ አራት ኪሎ ከቅድስት ማርያም ቤተhርስቲያን ወረድ ብሎ ሮሚና ካፌ ህንፃ ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 07 ድረስ በመቅረብ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 30 ቀናት የማይመለስ ብር 200.00/ሁለት  መቶ/ በመክፈል ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።     ተወዳዳሪ ተቋራጮች የጨረታ ሰነዱን በአግባቡ በመሙላትና በማሸግ በ31ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡59 ድረስ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ህንፃ ቁጥር 27 ቢሮ ቁጥር 10 ድረስ በመቅረብ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።     . ጨረታው በ31ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ህንፃ ቁጥር 27 በግዥ ቡድን ቢሮ ቁጥር 10 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቾች በጨረታው ላይ መገኘት ካልቻሉ መስፈርቱን እስካሟሉ ድረስ በጨረታው ላይ ያልተገኙ ተጫራቾች ፖስታን ጨምሮ ጨረታው በእለቱ ይከፈታል።     የጨረታውን ፋይናንሽያል ኦርጅናል ዶከመንቶች እንዲሁም የጨረታ ማስከበሪያውን ለየብቻ አስተማማኝ በሆነ ማጣበቂያ በታሽı ፖስታ በማድረግና በእያንዳንዱ ፖስታ ላይ የመ/ቤቱን ሙሉ ስምና አድራሻ በመፃፍ ማህተም በማድረግ በተጠቃለለ አንድ ፖስታ በማሸግ ማቅረብ ሲኖርባቸው ፋይናንሽያል ዶhመንቶች ከኦርጅናሉ በተጨማሪ አንድ ኮፒ ማቅረብ አለባቸው።     ዩኒቨርሲቲው ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ማሣሰቢያ፡- የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም በበዓል ቀናት ከሆነ ጨረታው በቀጣዩ የሥራ ቀን ተዘግቶ የሚከፈት ይሆናል። ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር : 058-771-6691 ደብረማርቆስ መጠየቅ ይቻላል። የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የግንባታ ጨረታ ማስታወቂያ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ጽ/ቤት በበጀት አመቱ ከሚያሰራቸው ፕሮጀክቶች መካከል 1. የዝቅተኛ ማህበረሰብ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ ደረጃ 5 /ህንጻ ስራ ተቋራጭ ደረጃ 4 እና በላይ የሆኑ በዚህ ኘሮጀክት ላይ መሳተፍ ለምትፈልጉ፡-  የታደሰ የንግድ የስራ ፈቃድ ያላቸው፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው። ከላይ የተጠቀሰውን ፕሮጀክት ለማሰራት አስፈላጊውን ሁሉ የሰው ሃይል፣ የማቴሪያል እንዲሁም የመሳሪያ አቅርቦቶችን የሚያሳይ በስማቸው የታሸገ የፋይናንሽያል እና የቴክኒካል የመወዳደሪያ ሃሳቦችን ማቅረብ አለባቸው።  የጨረታ ሰነድ መግዛት የሚፈልጉ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራቾች በኮንስትራክሽን መምሪያው የግዥና ፋይናንስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 13 ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ። ማንኛውም ተጫራች የተጫራቹንና የኘሮጀክቱን ስም በግልፅ ተቀባይነት ያለው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልመሰረተ የባንክ ዋስትና ጨረታ ዝርዝር መረጃ ሰንጠረዥ የተጫራቾች መመሪያ ተ.መ 21.1 ላይ የተጠቀሰውን የገንዘብ መጠን ማስያዝ ይኖርበታል። ተጫራቾች መመሪያ በማንበብ ሙሉ ፈቃደኛ እንዲሆኑ ይመከራሉ።  የዝቅተኛ ማህበረሰብ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ኘሮጀክት በ90 /ዘጠና/ ካላንደር ቀኖች የሚጠናቀቅ ይሆናል። ሁሉም የቅድመ ማጣሪያ /ቴክኒካል/ እና ጨረታ ዋጋ /ፋይናንሻል/ ሰነዶች በተለያዩ ኢንቨሎፓች ማህተም በማድረግ መታሸግ ይኖራባቸዋል። (አንድ ኦርጅናል አንድ ኮፒ) ጨረታው ሁለት የግምገማ ሂደቶች ይኖሩታል። የመጀመሪያው ሂደት ደረጃ የቴክኒካል ሰነዶች ግምገማ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ቴክኒካል ግምገማውን ካለፉት ተጫራቾች ውስጥ ዝቅተኛ የጨረታ ዋጋ ያቀረበውን ተጫራች መም ረጥ ይሆናል።  የታሸጉ የቅድመ ማጣሪያና የጨረታ ዋጋ ሰነዶች የሚቀርቡት ለኮንስትራክሽን መምሪያው የግዥና ፋይናንስ የስራ ሂደት ሆኖ ጨረታው በአየር ላይ ከዋለበት ከ2፡30 ጀምሮ እስከ 21ኛ ቀን 8፡00 ታሽጎ የሚዘጋ ሲሆን ጨረታው በይፋ የሚከፈተው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ21ኛው ቀን 9፡00 ላይ በግዥና ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 13 ውስጥ ይሆናል። ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ከስራ ቀናት ውጭ ከሆነ ወደ ሚቀጥለው የስራ ቀን ይዘዋወራል።  ተጫራቾች ማንኛውንም ተጨማሪ መረጃ ከባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ጽ/ቤት ፓ.ሳ.ቁ 49 ቴሌ 0583204138 ፋክስ 058-222-16-26 ማግኘት ይችላሉ። በባህር ዳር ከተማ ውስጥ በባለፈው አመት ውስጥ ፕሮጀክት ጀምሮ ያቋረጠ ወይም በተሰጠው ውል መሰረት ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች ያሉት ተጫራች በዚህ ጨረታ ላይ መሳተፍ አይችሉም። ማንኛውም ተጫራች ከስራ ዝርዝሩ ውስጥ ወይም ከዚህ በላይ የስራ አይነቶች ላይ የነጠላ ዋጋ ሳይሞላ ቢቀር ያለ ክፍያ ስራውን እንዲሰራው ይገደዳል። ማንኛውም ተጫራች ጨረታውን ከማስገባቱ በፊት የሳይት ጉብኝት ማድረግ ይጠበቅበታል። ስለዚህም አሰሪ መስሪያ ቤቱ ከሳይቱ ሁኔታ ጋር የተያያዙ ቅሬታዎችን አይቀበልም። ማንኛውም ተጫራች ከቴክኒካል ሰነዱ ዉስጥ ከጠቅላላ ዉሉ 15 በመቶ ያህሉን ለስራ እድል ፈጠራ ለማዋል መስማማቱን የሚገልፅ ህጋዊ ማረጋገጫ ደብዳቤ አብሮ ማያያዝ አለባቸው። ካልሆነ ግን በጥቃቅን አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለተደራጁ ወጣቶች የስራ እድል አማራጮችን ለማስፋትና ለማበረታታት የተዘጋጀ መመሪያ ቁጥር 52/2014 ዓ.ም. መሰረት ተጫራቾች ዉድቅ የሚደረግ ይሆናል። የባ/ዳር ከተማ አስተዳደር የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ጽ/ቤት

የግንባታ ጨረታ ማስታወቂያ በአብክመ በምስ/ጎጃም ዞን የሞጣ አየር ማረፊያ 2ኛ/ደ/ት/ቤት የተቋረጠ G+1 ባለ2 ብሎክ 20 የመማሪያ ክፍሎችን GC እና BC ደረጃ 6 እና ከዚያ በላይ ፈቃድ ያላቸው ተቋራጮችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፡- . በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡  ተጫራቾች የግንባታ ፈቃድ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ። የግዥው መጠን ከብር 50,000 /ሀምሳ ሺህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስከር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፡፡ . ተጫራቾች ከተራ ቁጥር 1-3 ድረስ የተዘረዘሩትን የሚመለከታቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡ . የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡  ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በማይመለስ 1,000 /አንድ ሺህ ብር/ ከፍለው አየ/ማረ/2ኛ/ደ/ት/ቤት የግዥ ቢሮ ቁጥር 5 መውሰድ ይችላሉ፡፡  ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ G+1 ባለ 2 ብሎክ 20 የመማሪያ ክፍሎችን በብር 340,000 /ሶስት መቶ አርባ ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡ በጥሬ ገንዘብ የሚያሲዙ ተጫራቾች በመስሪያ ቤቱ የገቢ መሰብሰቢያ ደረሰኝ በማስቆረጥና ደረሰኙን ኮፒ በማድረግ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡ ተጫራቾች የጨረታ ሀሳባቸውን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በማድረግ ስምና አድራሻ በመፃፍ ፊርማና ማህተም በማድረግ እንዲሁም ፖስታው ላይ የሚወዳደሩበትን ግንባታ ዓይነት በመፃፍ ከሞጣ አየ/ማረ/2ኛ/ደ/ት/ቤት የግዥ ቢሮ ቁጥር 5 ለጨረታ ከተዘጋጀው የጨረታ ሳጥኑ ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡  ተጫራቾች ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 30 ቀናት ሁኖ በ31ኛው ቀን እስከ ጠዋቱ 4፡00 ድረስ የመጫረቻ ሰነዳቸውን ከተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡፡ ጨረታው በ31ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ 4፡20 ላይ ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው/ በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 5 ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ይከፈታል፡፡  የጨረታ መክፈቻ ቀኑ ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የህዝብ በዓል ቀን ከሆነ በቀጣይ የስራ ቀን በተመሳሳይ የስራ ሰዓት ይከፈታል፡፡  ስለጨረታ ዝርዝር ሁኔታው ለመጠየቅ ከፈለጉ በአካል በመምጣት ወይም በስ/ቁጥር 0586611933 ወይም በሞባይል ቁጥር /0975498231/ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡ . በተጨማሪ በአብክመ የግዥ መመሪያ ቁጥር 1/2003 እና በተሻሻለው የግዥ መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡  መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ሞጣ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት የሞጣ አየር ማረፊያ 2ኛ/ደ/ት/ቤት

የ ኮንስትራክሽን ውሎችን ለሌላ መልቀቅ(Assignment) ምን ማለት ነው? . 📌ውሎችን ለሌላ መልቀቅ (Assignment) ዋናው ተቋራጭ የግንባታ ውሉን ስራ በሙሉ እንዲፈጽምለት ለአንድ ሶስተኛ ወገን ለሆነ ሲያስተላልፍ ነው፡፡ (የፍ/ህ/ቁ 3201(1)) *ይሄውም ከንኡስ ተቋራጭነት ጋር ሁኔታው አንድ አይነት ሲሆን በዋናነት ልዩነቱ ዋናው ተቋራጭ ለሌላ ተቋራጭ(ለንኡስ ተቋራጩ) የሚያሰራው ሙሉውን የግንባታ ስራ ነው፡፡ *በዚህ ውል ውስጥ ሁለቱም ተዋዋይ ወገኖች ተቋራጮች ናቸው፡፡ **ለምሳሌ "ሀ" የተባለ ተቋራጭ "ለ" ከተባለ አሰሪ ጋር የኮንስትራክሽን ውል ገባ እንበል፡፡የግንባታ ስራው ደግሞ ትምህርት ቤት ቢሆን እና ሁለት ብሎክ መማሪያ ህንጻ እና አንድ ሽንት ቤት ግንባታ ቢሆን እንበል፡፡ እንግዲህ ዋናው ተቋራጭ "ሀ" ከግንባታ ስራው ውስጥ አንዱን ብሎክ መማሪያ ክፍል "ሐ" ለተባለ ተቋራጭ በውል ሰጥቶ ቢያስገነባው በ "ሀ" እና "ሐ" መካከል የሚደረገው ውል የንኡስ ተቋራጭነት ውል ይባላል ማለት ነው፡፡ *በሌላ በኩል ምናልባት ዋናው ተቋራጭ "ሀ" ሁሉንም ግንባታ ማለትም ሁለት ብሎክ መማሪያ ህንጻ እና አንድ ሽንት ቤት "መ" ለተባለ ተቋራጭ በውል ሰጥቶ ቢያስገነባው በዋናው ተቋራጭ "ሀ" እና "መ" በተባለው ተቋራጭ መካከል የተደረገው ውል በንኡስ ተቋራጭነት ሳይሆን ውሎችን ለሌላ መልቀቅ(Assignment) በሚለው የህግ ክፍል የሚጠቃለል ይሆናል ማለት ነወ፡፡ . 📌ጀኔራል ኮንዲሽኖች ንኡስ ተቋራጭነትን በምን ሁኔታ ያስቀምጡታል? ፒፒኤ 2011 ስለ ንኡስ ተቋራጭነት አስመልክቶ በክሎስ 14 ላይ አስቀምጧል፡፡ *በዚህም የንኡስ ተቋራጭነት ውሉ በጽሁፍ መሆን እንዳለበት እና ይሄውም የቫሊዲቲ መስፈርት ስለመሆኑ ይገልጻል፡፡ *ንኡስ ተቋራጮች በዋናው የኮንስትራክሽን ውል ላይ ያልታወቁ( Non nominated) የሆኑ እንደሆነ ዋናው ተቋራጭ ሌሎች ንኡስ ተቋራጮችን የግንባታ ስራ ለማሰራት የአሰሪውን የጽሁፍ ፈቃድ ማግኘት ይኖርበታል በሚል ያስቀምጣል፡፡ *የንኡስ ተቋራጭነት ውሉም ከዋናው ውል ጋር የተጣጣመ እና በዋናው ውል ጭምር የሚገዛ እንደሚሆን ክሎስ 14.3 ላይ ተቀምጧል፡፡ *ዋናው ተቋራጭ የአሰሪው መስሪያ ቤት ሳይፈቅድለት የንኡስ ተቋራጭነት ውል የገባ እንደሆነ አሰሪው ፎርማል ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልገው ውልን ማቋረጥ እንደሚችል ክሎስ 14.8 ያስቀምጣል፡፡ *ሌላው ንኡስ ተቋራጩ የግንባታ ስራ ለማከናወን ብቃት የሚያንሰው እንደሆነ አሰሪው መስሪያ ቤት ወይም መሀንዲሱ ዋናውን ተቋራጭ ሌላ ብቃት ያለው ንኡስ ተቋራጭ እንዲያመጣ ወይም ስራውን በራሱ እንዲያከናውን ሊጠይቀው እንደሚችል ክሎስ 14.9 ይገልጻል፡፡ ፊዲክ ሬድ ቡክ 1999-በዚህ ጀኔራል ኮንዲሽን ክሎስ 4.4 ላይ ዋናው ተቋራጭ ሙሉውን የግንባታ ስራ ለንኡስ ተቋራጭ መስጠት እንደማይችል ተቀምጧል፡፡ *እንዲሁም በስፔሻል ኮንዲሽን ላይ በሌላ ሁኔታ ካልተቀመጠ በስተቀር ንኡስ ተቋራጩ በዋናው የኮንስትራክሽን ውል ላይ ስሙ የተጠቀሰ በሆነ ጊዜ በንኡስ ተቋራጭነት ለማሰራት የመሀንዲሱን ፈቃድ መጠየቅ አይጠበቅበትም፡፡ *ሆኖም የታሰበው ንኡስ ተቋራጭ አዲስ እና በዋናው ውል ስሙ ያልተጠቀሰ የሆነ እንደሆነ በቅድሚያ የመሀንዲሱን ፈቃድ ማግኘት አስፈላጊ ይሆናል፡፡ *ዋናው ተቋራጭ ለመሀንዲሱ በተለይ ንኡስ ተቋራጩ የሚሰራውን የግንባታ ስራ መጀመሪያ ቀን/ኮመንስመንት ዴት/ ተብሎ የታሰበውን ጊዜ ከ28 ቀን ባላነሰ ጊዜ ማስታወቅ ሲኖርበት ንኡስ ተቋራጩ በትክክል በሳይት ላይ ስራ የጀመረበትንም ቀን ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡ Nominated subcontractors በሚመለከት በክሎስ 5.1 ላይ ትርጉም ተሰጥቶታል፡፡ *በዚህም መሰረት ኖምኔትድ ሰብ ኮንትራክተር የሚባለው በዋናው የኮንስትራክሽን ውል ላይ ኖምኔትድ ሰብ ኮንትራክተር መሆኑ የተገለጸ እንደሆነ ወይም ኢንጅኒየሩ ለተቋራጩ ንኡስ ተቋራጭ መርጦለት እንዲያሰራው ያዘዘው የሆነ እንደሆነ ነው፡፡ . ለኖምኔትድ ሰብ ኮንትራክተሩ ክፍያ የሚፈጸምለት በንኡስ ተቋራጭነት ውሉ አግባብ በመሀንዲሱ በሚሰጥ የክፍያ ሰርተፍኬት መሰረት ሲሆን ክፍያውን የሚፈጽመውም ዋናው ተቋራጭ ስለመሆኑ ክሎስ 5.3 ላይ ተቀምጧል፡፡ ✍በ ጉባዔ አሰፋ

ግንባታ ጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር OO9/2015 በደቡብ ክልል በስልጤ ዞን የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ፋ/ኢ/ጽ/ቤት ለቂልጦ ጎሞሮ ማ/ቤት ለአነስተኛ ድልድይ ግንባታ ብቁ ተጫራቾችን በጨረታ አወዳድሮ ማስገንባት ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታው ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ይህ ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ስለግንባታው የሚገልጽ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 150 (አንድ መቶ ሃምሳ) በመከፈል ዘወትር በስራ ሰዓት በምስ/አዘ/በር/ወረዳ ፋ/ኢ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 16 ድረስ በመምጣት ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት የጨረታ ሰነድ መግዛት ትችላላችሁ። በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች GC/BC-6 እና ከዚያ በላይ የሆኑ ተጫራቾች በዘርፉ ያላቸው የታደሰ የንግድ ፍቃድ፣ የምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፣ ከግብርቨ ሰሰብሳቢ መ/ ቤት/ቤት የተሰጠ ወቅታዊ የግብር ክፍያ ማረጋገጫ፣ የቫት ምዝባ ሰርተፊኬት፣ በአቅራቢዎች ስም ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸው የሚገልጽ ማስረጃና ሌሎች ሰነዶችን ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው። ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 15,000 (አስራ አምስት ሺህ)ብር በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ወይም በCPO በምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ፋ/ኢ/ጽ/ቤት ስም አሰርተው ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ በታሸገ ፖስታ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል የጨረታ ሰነድ ማስገባት አለባቸው፡፡ ዘግይቶ የሚቀርብ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረውም። ተጫራቾች የቴክኒካል እና ፋይናንሻል የመረቻ ሰነዶችን ለእያንዳዳቸው አንድ ኦሪጅናል እና ሁለት ኮፒ የጨረታ ሰነድ ለየብቻ በታሸገ ፖስታ ህጋዊ ማህተም በማድረግ ማቅረብ አለባቸው። ጨረታው ለተከታታይ 15 የስራ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በ15ኛው ቀን በ8:00  ፡ሰዓት ታሽጎ በዚያው ቀን 8:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ይከፈታል። ዕለቱ ቅዳሜ ወይም እሁድ ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን ከላይ የተጠቀሰው ሰዓት ታሽጎ በተባለው ሰዓት ይይከፈታል። የግንባታው ቦታ ጉራቾ ወንዝ ላይ ሲሆን ሳይት ጉብኝት ግዴታ ነው። በተጫራቾች ተሞልተው የሚቀርቡ ፋይናንሻል ዋጋዎች እና የግንባታ ስራው ቴክኒካል የማወዳደሪያ ሀሳብ ደጋፊ ሰነዶች በግልጽና በጥራት የሚታዩና ስርዝ ወይም ድልዝ ያልሆኑ መሆን አለባቸው። መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ወረዳው ከአዲስ አበባ ርቀቱ 221 ኪሎ ሜትር ሲሆን 176 ኪሎ ሜትር አስፓልት እና 45 ኪሎ ሜትር ፒስታ መንገድ ነው። ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 046 89 91 744 / 09 10 70 15 68 በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/በስልጤ ዞን የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ፋ/ኢ/ጽ/ቤት ቂልጦ የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply   ----------- ጨረታ | bid ----------- ዩኒቲ ኮንስትራክሽን ስራ ኦፊሻሎች

PVC እና UPVC ዕቃዎች ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ
PVC  እና UPVC  ዕቃዎች ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ

የሲሚንቶ መሸጫ ዋጋ ይፋ ተደረገ አዲሱን የሲሚንቶ መሸጫ ዋጋ አስመልክቶ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የሲሚንቶ አምራቾች ቦርድ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በዚህም ከሚቀጥለው ሳምንት
የሲሚንቶ መሸጫ ዋጋ ይፋ ተደረገ አዲሱን የሲሚንቶ መሸጫ ዋጋ አስመልክቶ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የሲሚንቶ አምራቾች ቦርድ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በዚህም ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በአዲስ አበባ በአዲሱ የዋጋ መሸጫ ተመን መሰረት ይሰራጫል ተብሏል። የመሸጫ ዋጋ በኩንታል ዳንጎቴ ሲሚንቶ 1 ሺህ 106 ብር ከ85 ሳንቲም ደርባ ሲሚንቶ 1 ሺህ 67 ብር ከ33 ሳንቲም ካፒታል ሲሚንቶ 1 ሺህ 52 ብር ከ25 ሳንቲም ኩዩ ሲሚንቶ 1 ሺህ 65 ብር ከ25 ሳንቲም መሸጫ ዋጋ እንደተቆረጠላቸው ተገልጿል። በአጠቃላይ ሁሉም የሲሚንቶ ምርቶች ከ1 ሺህ 200 ብር በታች እንደሚሸጡ ነው የተገለጸው። በክልል እና ዞኖችም የመሸጫ ዋጋ በቀጣይ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።

የግንባታ ስራ ተቋራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 &lt;&lt;ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 17 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply &nbsp
የግንባታ ስራ ተቋራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 <<ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 17 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply   ----------- ጨረታ | bid ----------- ዩኒቲ ኮንስትራክሽን ስራ ኦፊሻሎች

የግንባታ ስራ ተቋራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 &lt;&lt;ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 17 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply &nbsp
የግንባታ ስራ ተቋራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 <<ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 17 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply   ----------- ጨረታ | bid ----------- ዩኒቲ ኮንስትራክሽን ስራ ኦፊሻሎች

የግንባታ ስራ ተቋራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 &lt;&lt;ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 17 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply &nbsp
የግንባታ ስራ ተቋራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 <<ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 17 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply   ----------- ጨረታ | bid ----------- ዩኒቲ ኮንስትራክሽን ስራ ኦፊሻሎች

የግንባታ ስራ ተቋራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 &lt;&lt;ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 16 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply &nbsp
የግንባታ ስራ ተቋራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 <<ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 16 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply   ----------- ጨረታ | bid ----------- ዩኒቲ ኮንስትራክሽን ስራ ኦፊሻሎች

የግንባታ ስራ ተቋራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 &lt;&lt;ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 16 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply &nbsp
የግንባታ ስራ ተቋራጭ | ጨረታ @unitysupplydb1 <<ገፃችን አዲስ ዘመን ጥር 16 ቀን 2015 የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ https://t.me/unityconsupply   ----------- ጨረታ | bid ----------- ዩኒቲ ኮንስትራክሽን ስራ ኦፊሻሎች