es
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Ir al canal en Telegram

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service

Mostrar más
3 589
Suscriptores
+224 horas
-17 días
+4230 días
Archivo de publicaciones
Share የአማካሪዎች ውል ኮንትራት ፎርም.doc

የኮንስትራክሽን ዋስትና አይነቶች
1.ጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid Bond) ጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማለት ጨረታ ተወዳድሮ ያሸነፈ ተጫራች ለምሳሌ ሥራ ተቋራጩ በአሸነፈው መሰረት ውሉ ቢሰጠው ግዴታውን ስለመፈጸሙ የሚያቀርበው ዋስትና ነው፡፡ በሌላ አባባል ይህ ዋስትና ሥራ ተቋራጩ ለአሰሪው ጨረታውን በማሸነፉ ወደ ውሉ እገባለሁ ሲል የሚገባው የዋስትና ግዴታ ነው፡፡ ይህም ጉዳይ በመንግስት ግዥ አዋጅ ላይ በአንቀጽ 40 በስፋት ተመልክቷል፡፡ የመንግስት መ/ቤቶች ለሚያሰሩት ግንባታ በሚያዘጋጁት የጨረታ ሰነድ ተጫራቾች ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር የጨረታ ማስከበሪያ የማቅረብ ግዴታ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህም መያዣ ተጫራቹ ጨረታው አየር ላይ እያለ ከውድድሩ ከወጣ ወይም ከአሸነፈ በኋላ ውሉን ለመፈጸም ፈቃደኛ ካልሆነ የጨረታ መያዣ ገንዘቡ ሊወረስ ይችላል፡፡ በሌላ አባባል የጨረታ ማስከበሪያ በሚል የሚያዝ ገንዘብ ጨረታውን ባዘጋጀው አካል ሊወሰድ የሚችለው ተወዳዳሪው ጨረታውን ባሸነፈው መጠን ሆኖ በጨረታው መሠረት መፈጸም ካልቻለ ወይም አስቀድሞ ከወጣ ነው፡፡ የጨረታ ዋስትናው መጠኑን በተመለከተም እኤአ በ2010ዓ.ም በወጣው የገ/ኢ/ል/ሚ የግዥ መመሪያ አንቀጽ 16.16.2 ላይ እንደተገለጸው የጨረታ ዋስትና የውሉን አጠቃላይ ግምት ወስጥ 0.5 (ግማሽ) እሰከ 2(ሁለት) ፐርሰንት ሊደርስ ይችላል፡፡ ነገር ግን የተባለው የመንግስት መ/ቤት የጨረታ ዋስትናውን መጠን በሚወስንበት ጊዜ ከ500,000.00 (አምስት መቶ ሺ) ብር መብለጥ የለበትም፡፡ የጨረታው አካሄድ ሚዛናዊ እንዲሆን መመሪያው እንደሚለው የመንግስት የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ለማከናወን የሚወጣ ጨረታ ቢያንስ የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ማስገባት አለበት፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ በግዥ የሚሰራው ሥራ የዋጋ አስተማማኝነት ግምት ውስጥ መግባት ይኖርበታል፡፡ ሁለተኛ በጨረታው በቂ ቁጥር ያላቸው ተጫራቾች እንዲኖሩ ግድ ይላል፡፡ የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘቡ ተጫራቾችን እንዳይሳተፋ አስቀድሞ የሚከለክል መሆን የለበትም፡፡ ሌላው #የጨረታ_ማስከበሪያ ገንዘቡ አጫራቹ የመንግስት መ/ቤት በጨረታው አሸናፊ የሆነው ተጫራች ጨረታውን ባለመፈጸሙ ምክንያት ሊደርስበት የሚችልን ጉዳት መሸፈን ይኖርበታል፡፡

Share የውል ሰነዶች መመሪያ.pdf

Share ሀገር ውስጥ የጨረታ ሰነድ አገልግሎት መመሪያ-2012.pdf

Share ኮንስትራክሽን ከቀረጥ-ነፃ-ለማስገባት-ቅድመ-መስፈር.pdf

ሴራሚክ ቴራዞ መግዛት ስትፈልጉ ጥሩ አቅም ያላቸው ደንበኞች አቅራቢዎች ስላሉን አድራሻቸውን ልንሰጣችሁ እችላለን 📞+251-908280208 | +251- 707999001 | +251-89999001 ቴሌግ
+5
ሴራሚክ ቴራዞ መግዛት ስትፈልጉ ጥሩ አቅም ያላቸው ደንበኞች አቅራቢዎች ስላሉን አድራሻቸውን ልንሰጣችሁ እችላለን
📞+251-908280208 | +251- 707999001 | +251-89999001 ቴሌግራም" ጥያቄም ሆነ ሀሳብ ካለችሁ በቀጥታ ከስር /ያለውን: t.me/UnitySupplydbot ☜|] ለመልዕክት ይጠቀሙ, ይደርሰናል
ፈጣን ምላሽ እንሰጣለን.. .) 

ጠቃሚና ወቅታዊ የስራ መረጃዎችን ስለምንለቅ ቻናሉን join አድርጉት👇
http://t.me/ConSiteCatalogue1 👈🚧🏗
ለሌሎችም ተያያዥ ስራ ላላቸው ባልደረቦቻችሁ አጋሩ በተለይ ኮንትራክተሮች፣ አማካሪዎች እና በኮንስትራክሽን ዘርፍ ውስጥ ላላችሁ ኢንጂነር(Engineer)ባለሞያዎች ይጠቅማችኃል እኛን ይቀላቀሉ.. .)መልካም ጊዜ!🤚

ጠቃሚና ወቅታዊ የስራ መረጃዎችን ስለምንለቅ ቻናሉን join አድርጉት👇
http://t.me/ConSiteCatalogue1 👈🚧🏗
ለሌሎችም ተያያዥ ስራ ላላቸው ባልደረቦቻችሁ አጋሩ በተለይ ኮንትራክተሮች፣ አማካሪዎች እና በኮንስትራክሽን ዘርፍ ውስጥ ላላችሁ ባለሞያዎች ይጠቅማችኃል እኛን ይቀላቀሉ.. . መልካም ጊዜ!🤚

Share የኮንስትራክሽን መብቶች ምንነት እና የሚስተዋሉ ችግሮች (1).pdf

በኮንስትራክሽን ውል አሰሪው የተቋራጩን ክፍያ አዘግይቶ መክፈል ጉዳይ/Delay payment/
የኮንስትራክሽ ውል መሰረታዊ ባህሪው ሲታይ በዋናነት አሰሪና ተቋራጭን በተዋዋይነት የሚይዝ ሲሆን ጉልህ የሆነው ግዴታቸው ሲታይ ደግሞ ተቋራጩ በውሉና ዲዛይኑ/ስፔስፊኬሽኑ መሰረት ግንባታውን የማከናወን ሀላፊነት የሚኖርበት ሲሆን ክፍያ የመክፈል ጉዳይ ደግሞ ለአሰሪው ዋናውና ትልቁ ግዴታው ነው፡፡የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 2610፣3019እና 3020 እንዲሁም 3244 ተገናዝቦ ሲታይ ይሄን ሁኔታ ያስገነዝባል፡፡ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3020(1) ላይ "ሁለቱ ወገን ተዋዋዮች ስለሚፈጽሙት ስራዎችና ስለዋጋው ካልተስማሙ በቀር የተቋራጭነት ውል አለ አይባልም" በሚል የተደነገገው በኮንስትራክሽን ውል ለተቋራጩ የሚከፈለው ክፍያ ጉዳይ የውሉ መሰረታዊ ነጥብ መሆኑን የሚጠቁም ነው፡፡ ስለክፍያ አይነቶች የህጉን ጉዳይ ወደፊት በሌላ ጽሁፍ የምናየው ይሆናል፡፡ አሰሪው ለተቋራጩ ክፍያ የመክፈሉን ሁኔታ ያለበቂ ምክንያት ማዘግየት አይችልም፡፡ አማካሪ መሀንዲሱ በተለይ ከተቋራጩ የክፍያ ጥያቄ በቀረበለት ጊዜ የማረጋገጥና የማጽደቁን ስራ በ7(ሰባት) ቀናት ውስጥ የማጠናቀቅ ግዴታ አለበት፡፡(የመመሪያው አንቀጽ 28.5(d) አሰሪው መስሪያ ቤት ደግሞ በአማካሪ መሀንዲሱ የጸደቀ የክፍያ ሰርተፍኬት በደረሰው በ14(አስራ አራት) ቀናት ውስጥ ለተቋራጩ ክፍያ የመፈጸም ግዴታ አለበት፡፡ (የመመሪያው አንቀጽ 28.5(e) አማካሪ መሀንዲሱ በተቋራጩ የቀረበውን የክፍያ ጥያቄ በሰባት ቀናት ውስጥ የማረጋገጥና የማጽደቅ ስራ ባይፈጽም ምን ውጤት ይኖረዋል? • በዚህ ረገድ የመመሪያው አንቀጽ አንቀጽ 28.5(f) ግልጽ ምላሽ አስቀምጧል፡፡ • ይሄውም ተቋራጩ በዚህ ምክንያት ከአሰሪው ላይ ተጨማሪ ክፍያ/additional payment/ የጠየቀ እንደሆነ አማካሪ መሀንዲሱ ይህን ተጨማሪ ክፍያ የመሸፈን ግዴታ ይኖርበታል፡፡ •ሆኖም ግን አማካሪ መሀንዲሱ ለሚሰጠው አገልግሎት ከሚከፈለው ክፍያ በላይ የሆነ ክፍያ ለመክፈል ሀላፊነት አይኖርበትም፡፡ •በዚህ ረገድ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 2636 የአማካሪ መሀንዲሱን የእውቀት ስራ ውል ግዴታ ይደነግጋል፡፡ይሄውም አማካሪው "የኪነ ጥበብን ደንቦች በማፍረስ ጥፋት ጥፋት ካላደረገ በቀር በአሰሪው በኩል ስራ ተቋራጩን ሀላፊነት አይነካውም" በሚል ተቀምጧል፡፡(2636(2)) እንደዚሁም አማካሪው ሳይሰራ ከመቅረቱ የተነሳ ወይም በአሰሪው ላይ ጉዳትን የሚያመጣ ስራ ያደረገ እንደሆነ አጥፊ ነው ለመባል እንደሚችል የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 2636(3) ይደነግጋል፡፡ ስለዚህ አማካሪው ክፍያ የማረጋገጥ እና የማጽደቅ ስራውን በህጉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ባለማከናወኑ አሰሪው ተጨማሪ ክፍያ እንዲከፍል በተቋራጩ የተጠየቀ እንደሆነ አማካሪው አጥፊ ነው ሊባል ያስችለዋል ማለት ነው፡፡ አሰሪው በአማካሪው የጸደቀው የክፍያ ሰርተፍኬት በደረሰው በ14 ቀናት ውስጥ ለተቋራጩ ክፍያ ባይፈጽም ምን ውጤት ይኖረዋል? •አሰሪው ያለበቂ ምክንያት ክፍያ ያዘገየ እንደሆነ ለተቋራጩ ተጨማሪ ክፍያ/additional payment/ ለመክፈል ሀላፊነት እንደሚኖርበት የፌዴራል የግዥ መመሪያ/Federal public procurement directive/ አንቀጽ 28.5(g) ይደነግጋል፡፡ • ተጨማሪ ክፍያ ሲባልስ ምንን ያጠቃልላል? የሚለው ሲታይ በዋናነት ወለድ የመክፈል ሀላፊነትን የሚመለከት ይሆናል፡፡በዚህ ረገድ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3268 ተቋራጩ መክፈልን በማዘግየት የሚታሰበውን ወለድ እንዲያገኝ መብት ይሰጠዋል፡፡የወለዱ መጠንም በውል ያልተወሰነ የሆነ እንደሆነ በአንቀጽ 1751 መሰረት ህጋዊ ወለድ በአመት 9(ዘጠኝ) በመቶ ሆኖ የሚሰላ ይሆናል፡፡ • ሌላው እዚህ ላይ ሊታወቅ የሚገባው ነጥብ ተዋዋዮች በውላቸው ላይ ክፍያን ማዘግየት የሚኖረውን ውጤት አስመልክቶ የቅጣት ስምምነት/penality clause/ ያካተቱ ከሆነ የፍትሀብሄር ህጉ አንቀጽ 1889 እና ተከታዮቹ ድንጋጌ እውቅና ስለሚሰጠው እና በአንቀጽ 1731 መሰረት ውል በተዋዋዮች መካከል እንደ ህግ ስለሚቆጠር ተፈጻሚነት ይኖረዋል፡፡ • አንዳንድ ክልሎችም በዚህ ረገድ በግዥ መመሪያቸው ላይ ዝርዝር ውጤቱን ያስቀምጣሉ፡፡ • አሰሪው ክፍያ በወቅቱ ባለመፈጸሙ ምክንያት ከወለድ ባለፈ ሌላም ጉዳት የደረሰበት ተቋራጭስ ከጉዳቱ ጋር እኩል የሆነ ኪሳራ ሊከፈለው አይገባም ወይ? የሚል ጥያቄም ሊነሳ ይችላል፡፡ምክንያቱም የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 2091 እና 1790(2) ለደረሰው ጉዳት ሀላፊ መሆኑ በህግ የታወቀ ሰው የሚከፍለው የጉዳት ካሳ ሀላፊነቱን ያመጣው ጉዳይ በተበዳዩ ላይ ከደረሰው ጉዳት ጋር እኩል ሆኖ መመዛዘን አለበት በሚል በግልጽ ይደነግጋል፡፡ በአጠቃላይ አሰሪው በማናቸውም ምክንያት የተቋራጩን ክፍያ በሚያዘገይበት ጊዜ ተቋራጩን ለውድቀት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው፡፡ምክንያቱም በሀገራችን አብዛኛው ተቋራጭ ድርጅት የፋይናንሽያል ማኔጅመንት ስርአት የለውም፡፡ተቋራጮቻችን የገንዘብ አቅማቸውም ደካማ ነው፡፡አብዛኛው ተቋራጭ ለአንዱ ፕሮጀክት የሚወስደውን የቅድሚያ ክፍያ ሌላ ፕሮጀክት ላይ ይጠቀምበታል፡፡በዚህ ምክንያት አንድ ተቋራጭ ሲከስር ብዙ ሰራተኛ እንደሚበተን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ስለዚህ በአሰሪዎች በኩል ተቋራጮች የሰሩበትን ክፍያ በወቅቱ እና በተሰራው ስራ ልክ አንዲከፈላቸው ለማድረግ እና በህጉ የተቀመጠው የክፍያ የጊዜ ገደብ እንዲከበር ጠንከር ያለ አቋም ወስዶ መስራት ይጠበቅበታል

Share 935_የንግድ_ምዝገባ፣_ፈቃድ_እና_ድኅረ_ፈቃድ_ኢንስፔክሽን_መመሪያ_ቁጥር_935_2015_1_7.pdf

ከግለሰብ ነጋዴነት ወደ ባለ አንድ አባል  ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል  ማኅበር ስልሚደረግ ለውጥ ህጉ ምን ይላል?
የግለሰብ ነጋዴ ወደ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል  ማኅበር ሲለወጥ        1. የግብር ክሊራንስ ማቅረብ አለበት፤        2. ሰነድችን ለማረጋገጥ በሕግ ሥልጣን በተሰጠው አካል የተረጋገጠ መግለጫ እና     የንብረት ጠባቂነት ማረጋገጫ ማቅረብ አለበት፤        3. የተፈጥሮ ስም ያልሆነ የደርጅት ስም መምረጥ አለበት፤        4. መግለጫው በንግደ ማኅበራት የተደነገጉትን የመመሥረቻ ጽሐፍና ቃልጉባኤዎችን      የሚተካ ሆኖ የመግለጫው ይዘት ቢያንስ በንግድ ሕጉ አንቀጽ 536 ንዐስ ቁጥር (2)    የተቀመጡትን ማሟላት አለበት፤        5. ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተደነገጉ ሌሎችች ድንጋጌዎች ለባለአንድ አባል ኃሊፉነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርም ያገለግላሉ

የኢትዮጲያን በጀት አመት የሚጠቀሙ ንግዶች የንግድ ፍቃድ እድሳት ጊዜ ማብቃትን ተከትሎ የሚከፈለውን ቅጣት መጠን ያውቃሉ?
      ከ ጥር 1 እስከ ጥር 30 ብር 2,500.00       ከ የካቲት 1 እስከ የካቲት 30 ብር 4,000.00       ከ መጋቢት 1 እስከ መጋቢት 30 ብር 5,500.00       ከ ሚያዚያ 1 እስከ ሚያዚያ 30 ብር 7,000.00       ከ ግንቦት 1 እስከ ግንቦት 30 ብር 8,500.00       ከ ሰኔ 1 እስከ ሰኔ 30 ብር 10,000.00       ከሃምሌ 1 ጀምሮ ለሚመጣው 1 አመት 20,000.00 ከ 1 ዓመት በኋላ ፍቃዱን በአዋጅ ይታገዳል በተጨማሪም ነጋዴው ለ 1 አመት በታገደው የፍቃድ መስጫ መደብ ፍቃድ ማውጣት እንዳይችል ይታገዳል