Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Ir al canal en Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
Mostrar más3 590
Suscriptores
-424 horas
+107 días
+4230 días
Archivo de publicaciones
Payment Certificate ማለት ምን ነው?
Payment certificate በኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ውስጥ ኮንትራክተሩ እስካሁን ያከናወነውን የሥራ መጠን እና መጠን የተረጋገጠ ክፍያ መጠይቅ
መሆኑን የሚያረጋግጥ መግለጫ/ሰነድ ነው።
👉 ይህን ሰነድ ብዙ ጊዜ ሱፐርቫይዘር / ኤንጂነር / ኮንስልታንት ያዘጋጃል እና ለ ኦውነር / ከፋይ ይላካል።
👉 ከተፈረመ በኋላ ብቻ ኮንትራክተሩ ገንዘብ መቀበል ይችላል።
Payment Certificate የሚያሳይው ዋና ነገሮች:-
1️ እስካሁን የተፈጠረ የሥራ መጠን (Work done to date)
2️⃣ የእቃ ወጪ እና ሰራተኛ ወጪ
3️⃣ የመጀመሪያ ክፍያ (Advance) ካለ የቀረ መጠን
4️⃣ Retention (የሚያቆዩት ገንዘብ)
5️⃣ ቀድሞ ተከፍሎ የነበረ መጠን
6️⃣ ይከፈል የሚችለው የአሁኑ መጠን (Net payable amount)
ለምን ጠቃሚ ነው?
✔ ሥራ በመመጠን እንዲከፈል ያረጋግጣል
✔ ከኮንትራክተር እና ከኦውነር መካከል ግጭት ይቀንሳል
✔ የፕሮጀክት የገንዘብ ቁጥጥር ይረዳል
✔ እንደ ሕጋዊ ማስረጃ ይጠቅማል
-በቀላሉ ምሳሌ
ኮንትራክተሩ በወር መጨረሻ ድረስ
የእርሱን የተሰራ ሥራ ዝርዝር ይገብራል።
ኤንጂነሩ ያረጋግጣል፣
ከዚያ Payment Certificate ይዘጋጃል፣
በመሰኪያውም የተገባው ገንዘብ ይከፈላል።
- ዓይነቶች
Interim / Monthly Payment Certificate (በየወሩ)
Final Payment Certificate (ፕሮጀክት ሲጨርስ)
+1
የግንባታ ጨረታዎች +2👷♂🚧
አዲስ ዘመን ታህሳስ 12 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ
@consite🏗
+2
የግንባታ ጨረታዎች +3👷♂🚧
ኢትዮጵያን ሄራልድ ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ
@consite🏗
በኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓት የጨረታ አከፋፈት መሠረታዊ ጉዳዮች
1) በኤሌክትሮኒክ ሥርዓቱ የሚደረግ ማንኛውም የጨረታ አከፋፈት ተጫራቾች በአካል መገኘት ሳያስፈልግ የኤሌክትሮኒክ የመገናኛ ዘዴ በመጠቀም መከናወን አለበት፡፡
2) የህዝብ ቁልፍ መጠበቂያ ሥርዓት ተግባራዊ እስከሚሆን ድረስ ለጨረታ አከፋፈት ዓላማ ማንኛውም ተጫራች በኤሌክትሮኒክ ሥርዓቱ የተሰጠውን የግል የሚስጥር ቁልፍ በጨረታ ሰነዱ ላይ በሚገለጸው የጊዜ ገደብ ውስጥ ለመንግስት መ/ቤቱ ማጋራት አለበት፡፡
3) የግል የሚስጥር ቁልፉን ከላይ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ለመ/ቤቱ ያላሳወቀ ተጫራች የመጫረቻ ሰነድ ሳይከፈት የጨረታው ማስከበሪያው ተወርሶ ከጨረታ ውጪ ይደረጋል፡፡
4) የግዥ ፈፃሚው መ/ቤት የግል የሚስጥር ቁልፍ በወቅቱ ያሳወቁ ተጫራቾችን የመጫረቻ ሰነድ በጨረታ አከፋፈት ወቅት መክፈት አለባቸው፡፡
5) የግል የሚስጥር ቁልፋቸውን ደህንነት መጠበቅ ኃላፊነት የተጫራቾች ነው፡፡
6) የግዥ ፈፃሚው መ/ቤት የጨረታውን አከፋፈት ሁኔታ እና ሂደት የሚያሳይ ቃለ ጉባኤ መያዝና ኤሌክትሮኒክ ሥርዓቱን ተጠቅመው ይፋ ማድረግ ይኖርበታል፡፡
@consite🏗
👉 INTERCON Construction Chemicals
● Concrete Admixtures
● Bonding Agents
● Waterproofings
● Wall Putty, Prime Coat
● Concrete Repair Mortar
● Floor hardener, Epoxy
● Grout, Self-level mortar
● Quartz paint, Contextra
● Tile Adhesive & Tile Joint Fillers
● Geotextiles and other construction chemicals and materials
☎️ Tel: 0961955555
🔹 Address 1: Signal road, around
Dinberwa Hospital
🔹 Addres 2: Wellosefer, Infront of
Dani Plaza
የጨረታ ማስታወቂያ
ለመንገድ ግንባታ እና ጥገና የሚያገለግሉ ልዪ ልዪ
ግብዓቶች ግዥ
Standard_bid_document_for_Turn_key_projects__1764236443.pdf1.79 MB
Repost from PMP- Ethiopia
Standard_bid_document_for_Turn_key_projects__1764236443.pdf1.79 MB
ማስታወቂያ
የቴክኒክ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ መራዘሙን ስለማሳወቅ!!!
የመጀመሪያውን ዙር ግምገማ ላለፋችሁ ተሳታፊዎች የቴክኒክ ሰነድ መግዣ እና ማስገቢያ ቀነ-ገደብ እስከ ታኅሳስ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መሆኑን መግለፃችን ይታወቃል።
ሆኖም በመጨረሻው የሰነድ ማስገቢያ ቀን ባጋጠመ የኔትወርክ መጨናነቅ ምክንያት በርካቶች ሰነዶቻቸውን አለማስገባታቸውን በመግለፅ ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት የሰነድ ማስገቢያ ቀነ-ገደብ ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡
በዚህም መሰረት የሰነድ ማስገቢያው ቀን ለተጨማሪ 3 ተከታታይ ቀናት ማለትም እስከ ታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት 6:00 ሰዓት ድረስ መራዘሙን እያሳወቅን እስካሁን ሰነድ ገዝታችሁ ያላስገባችሁ ተሳታፊዎች፤ የመጨረሻ ቀን መጨናነቅ ሳይፈጠር ይህንን ዕድል ተጠቅማችሁ በፍጥነት ሰነዶቻችሁን እንድታስገቡ ጥሪ እናቀርባለን።
ማሳሰቢያ:- ከዚህ ቀነ-ገደብ በኋላ የሚመጣን ማንኛውንም ቅሬታ የማንቀበል መሆኑን በድጋሚ እንገልፃለን።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የግብር ከፋዮችን የባንክ አካውንት የመዝጋት ሥልጣን ገደበ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ፣ የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ያለምንም የላቀ አመራር ፈቃድ የግብር ከፋዮችን የባንክ ሂሳብ (አካውንት) እንዳይዘጉ የሚከለክል አዲስ መመሪያ ማውጣቱን አስታወቀ።
ይህ እርምጃ በዘፈቀደ የሚወሰዱ እርምጃዎችን ለመቀነስና የንግዱን ማህበረሰብ እንቅስቃሴ ለመጠበቅ የታለመ ነው።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ከከፍተኛ ግብር ከፋዮች ጋር ባደረጉት የምክክር መድረክ ላይ እንደገለጹት፣ ከዚህ ቀደም በኦዲተሮች የግል ውሳኔ ወይም በጥቃቅን የሂሳብ ስህተቶች ምክንያት አካውንቶች መታገዳቸው በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጉዳት ሲያደርስ ቆይቷል።
#capital
ከቤት ልማት አማራጭ አንዱ በሆነው የህብረት ስራ ማህበር ተደራጅተው የጋራ መኖሪያ ቤት እየገነቡ ስለሚገኙ ማህበራት የቤቶች ልማት እና አስተደደር ቢሮ ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር በመተባበር ያሰናዱት መርሀ ግብር
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ ተቋራጭ የግንባታ ግዥና የሥራ ስምሪት የአሰራር ደንብ ቁጥር 199/2018 የሚመራው የቤቶች ኮርፖሬሽን ስራ ተቋራጮች መረጣ ሂደት የመጀመሪያውን የምዝገባ ሂደት አልፎ ለተመዘገቡ ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነድ እንዲያስገቡ የቀረበው ጥሪ 3 ቀናት ብቻ ቀርተውታል።
ስራ ተቋራጮች በሚያስገቡት ቴክኒካል ፕሮፖዛል መሰረት በተቀመጠው መስፈርት ተገምግመው ነጥብ ከመቶ ተሰጥቷቸው በቅደም ተከተል የሚመረጡ ይሆናል።
ስራው በቁርጥ ዋጋ (fixed rate) ወይም ቁርጥ ዋጋ ላይ በተመሠረተ ድርድር በከተማው ከንቲባ በሚሰየም ኮሚቴ የሚከናወን ይሆናል።
ማስታወቂያ
ለ7ኛ ዙር የ40/60 እና የ1ኛ ዙር የካፒታል ፕሮጀክት ንግድ ቤት ጨረታ አሸናፊዎች የውል ጊዜ እስከ ታህሳስ 16/2018 ድረስ የተራዘመ ስለሆነ በተሰጣችሁ ጊዜ ቀርባችሁ እንድትዋዋሉ
👉 ለጋራ መኖሪያ ህንፃ ግንባታ ለተመዘገባችሁ ተቋራጮች በሙሉ
▶️ የቴክኒካል ሰነድ የምታስገቡበት ጊዜ 3ት ቀን ብቻ መቅረቱን እያሳወቅን በዚህም መሰረት የሚጠናቀቅበት ጊዜ የፊታችን እሁድ በ12/04/2018 ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት ስለሆነ ሳትዘናጉ እንድታስገቡ ።
Call for Expression of Interest: Architectural Services for Nib International Bank S.C.
Call to submit an Expression of Interest (EOI) for the provision of architectural services for the construction of a Multi-Use Building in Addis Ababa, Kirkos Sub-City, Woreda 10.
The selected architect will be responsible for full design development, rendering, comprehensive final design, and contract management services in accordance with the client’s requirements.
The selection will be conducted using a Quality and Cost-Based Selection (QCBS) method, with six finalists to be shortlisted based on the submitted Expression of Interest. Interested firms must be properly registered and submit the required firm details at the designated registration desk.
Deadline: 27 December 2025 (before close of business)
Apply Here: Submit two copies of the Expression of Interest to the Registration Desk, 26th Floor, Nib International Bank Headquarters Building
For inquiries: +251 91 113 6447 / +251 11 557 8231
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
