cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

True Christianity ©️

🇹 🇭 🇪 🇧 🇦 🇵 🇹 🇮 🇸 🇲 🇴 🇫 🇹 🇭 🇪 🇭 🇴 🇱 🇾 🇸 🇵 🇮 🇷 🇮 🇹! يسوع هو الرب ALL WE NEED IS HOLYSPIRIT https://www.youtube.com/@TruechristianityOfficial

Mostrar más
Etiopía1 763El idioma no está especificadoReligión y espiritualidad7 224
Publicaciones publicitarias
12 313
Suscriptores
-924 horas
-937 días
-7030 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

online ለሆናችሁ ብቻ በኢትዮጵያ 🇪🇹 ተወዳጅነትን ያገኙ የቴሌግራም ቻናል ላስተዋውቃችሁ ከ1ሺ በላይ ተከታይ ያለችው በ @seer_lewi አነግሩኝ
Mostrar todo...
ምርጥ 10
ምርጥ 5
ምርጥ 3
ሁሉንም አንድ ላይ
Photo unavailable
5M GIFT🎁 15 ሰዓት ብቻ ነው የቀራው ሳያመልጣቹ ከላይ ፎቶ ላይ ያሉትን ካርድ በፍጥነት በመግዛት 5ሚ ኮይን በነጻ ያገኛሉ ቶሎ በሉ እድሉ እዳያመልጦት ይሄን ሊንክ በመንካት mine የሚለውጥ ትገቡ እና ካርዱን ትገዛላቹ ከእዛ 5ሚ ኮይን ጊፍት ይሰጣቹሀል 👇👇👇👇👇 https://t.me/hamster_koMbat_bot/start?startapp=kentId5645139506
Mostrar todo...
⚜notcoin ያምልጣቹ ሰዎች አሁን ከnotcoin በበለጠ ዋጋ ይወጣበታል እየተባለ ነው ''Hamster🐹''። ቶሎ ቶሎ Tap Tap አያደረጋቹ Coin ሰብስቡ🏃‍♂💨 🪩Hamster በዓለም አቀፍ በTelegram 1ኛ🥇 ደረጃ ላይ ይገኛል 👌ያላመነ ሰው check ማረግ ትችላላችሁ 🎉 🔎ለመጀመር ይሄን ነክታቹ tap tap📌 👇👇👇👇👇 https://t.me/hamster_koMbat_bot/start?startapp=kentId5645139506
Mostrar todo...
Hamster Kombat

Just for you, we have developed an unrealistically cool application in the clicker genre, and no hamster was harmed! Perform simple tasks that take very little time and get the opportunity to earn money!

Billionaire 💰🤑 መሆን ከፈለጉ አንድ አስገረም መንገድ ልንገራችሁ ተጠቀሙበት 👇👇Step 1 👇👇 የምለውን በመጫን ይጀምሩ 10 minute left 👈👈👈
Mostrar todo...
👉👉 Steps1👈👈
የአዲስ ኪዳን መሠረትና የውል ስምምነት ከብሉዩ ኪዳን ጨርሶ የተለየ ስለሆነና ታቦቱ ደግሞ የብሉይ ኪዳኑ ውል የሆነውን የሕጉን የምስክር ጽላቶች የያዘ፤ ስለ ብሉይ ኪዳኑ የሚመሠከር፤ ከብሉይ ኪዳኑ ጋር የተቆራኘ ስለሆነ፤ ለአዲስ ኪዳን ምስክር ሊሆን አይችልም። እግዚአብሔር ያሰበውም የታቦት አገልግሎት እግዚአብሔር ከእስራኤል ሕዝብ ጋር በሲና ተራራ ስላደረው ቃል ኪዳን መመሥከር እንጂ በክርስቶስ ደም ስለሆነው ስለ አዲሱ ኪዳን እንዲመሠክር አይደለም። አዲስ ኪዳን በድንጋይ ጽላት ሳይሆን በልብ ጽላት ላይ የሚጻፍ፣ ሰዎችን መኮነን ሳይሆን ማጽደቅ የሚችል ለእስራኤል ሕዝብ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሕዝቡ ሁሉ የሆነ፣ በኮርማዎችና በከብቶች ደም ሳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ደም የተመሠረተ የተሻለ ኪዳን ነው። የማርቆስ ወንጌል 14 22 ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ሰጣቸውና። እንካችሁ፤ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። 23 ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው፥ ሁሉም ከእርሱ ጠጡ። 24 እርሱም፦ ይህ ስለ ብዙዎች የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ነው።
Mostrar todo...
👍 3
አዲስ ኪዳን እንግዲህ ሰው በራሱ ሥራ እንደማይጸድቅና አዳኝ እንደሚያስፈልገው ተረድቶ በኢየሱስ ክርስቶስ መስዋትነትና አዳኝነት አምኖ የሚድንበትና የሚጸድቅበት ዓለምን ሁሉ ሊያድን የሚችል ኪዳን ነው። እዚህ ጋር ግን አንድ ልብ ማለት ያለብን ሁለቱን ኪዳኖች ጎን ለጎን በማካሄድ አንድም የሕግን ሥራ በመሥራት በራስ ለመጽደቅ መሞከር በሌላ ጎን ደግሞ በክርስቶስ ሥራ በጸጋ ለመጽደቅ መሞከር እንደማይቻል መገንዘብ ይገባናል። በአንድ በኩል በድንጋይ ጽላት ላይ ተጽፎ የተሰጠውን የሕግን ሥራ ሠርቶ ለመጽደቅ መሞከር፤ በሌላ በኩል ደግሞ እንዲያው በጸጋ በክርስቶስ እምነት የሚገኘውን ጽድቅ ማግኘት አይቻልም። በገላትያ የነበሩ የክርስቶስ አማኞች በአንድ በኩል የሕግን ሥራ በመሥራት በሌላ በኩል ደግሞ በክርስቶስ በኩል በጸጋ ለመጽደቅ እንዳይጥሩ ትልቅ ማስጠንቂያ ተሰጥቶአቸው ነበር። ወደ ገላትያ ሰዎች 5 2 እነሆ፥ እኔ ጳውሎስ እላችኋለሁ። ብትገረዙ ክርስቶስ ምንም አይጠቅማችሁም። 3 ሕግንም ሁሉ እንዲፈጽም ግድ አለበት ብዬ ለሚገረዙት ሁሉ ለእያንዳንዶች ደግሜ እመሰክራለሁ። 4 በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል። 5 እኛ በመንፈስ ከእምነት የጽድቅን ተስፋ እንጠባበቃለንና። 6 በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ፥ በፍቅር የሚሠራ እምነት እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና። ወደ ገላትያ ሰዎች 3 23 እምነትም ሳይመጣ ሊገለጥ ላለው እምነት ተዘግተን ከሕግ በታች እንጠበቅ ነበር። 24 እንደዚህ በእምነት እንጸድቅ ዘንድ ሕግ ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን ሆኖአል፤ 25 እምነት ግን መጥቶአልና ከእንግዲህ ወዲህ ከሞግዚት በታች አይደለንም። 26 በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤ የአዲስ ኪዳን ተከታዮች ከብሉይ ኪዳን ሕግ ነጻ ናቸው ማለት ግን ሕገወጥ ይሆናሉ የፈለጉትን ኃጢያት ይለማመዳሉ ማለት ግን አይደለም። በድንጋይ ላይ ከተጻፈ ከፊደል ሕግ ወጥተው ወደ መንፈስ ሕግ ይሸጋገራሉ ማለት ነው። ይህም በመንፈስ ቅዱስ እርዳታና ምሪት ከኃጢአት እየራቁ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በደስታ እያደረጉ መኖርን ያጠቃልላል። የአዲሱ ኪዳን የመንፈስ ሕግ ወይም በመንፈስ የመመላለስ ሕይወት ራሱን የቻለ ሰፊ ትምህርት ስለሆነ በዚህ ክፍል አንመለከተውም (በሮሜ 8 እና በገላትያ 5 ላይ ማጥናት ይቻላል)። ነገር ግን በአዲስ ኪዳን፤ ከብሉይ ኪዳን ሕግ መፈታት ማለት ሕገ ወጥ መሆን ወይም እንደፈለጉ ኃጢአትን ማድረግ እንዳልሆነ በዚህ ቦታ መጥቀስ ይገባል። በመጨረሻም ሁለቱ ኪዳኖች እስራኤላዊ ካልሆኑ ሕዝቦች ጋር ያላቸውን ግንኙነቶች እንመልከት። ቃሉ እንደሚለው ሁለቱም ኪዳኖች የመጡት ለእስራኤል ነው። ሆኖም ቀደም ብለን እንዳየነው በብሉይ ኪዳን አንዳንድ ተሰድደው በእስራኤል ከሚኖሩ ምጻተኞች (ስደተኞች) በስተቀር ሌሎች ሕዝቦች የዚህ ኪዳን ተካፋዮች አልነበሩም። የኪዳኑ ውል የሆነው የሕጉ በረከቱም ሆነ መርገሙ ከአንድ ሕዝብ ማለት ከእስራኤልና ለእነርሱ ከተሰጣቸው ምድር ጋር የተቆራኘ ነው። እግዚአብሔር ለእስራኤል ሕዝብ ብቻ የሰጠውና ሌሎች ሕዝቦችን (አሕዛብን) የማያካትት (exclusive)፤ በሥጋ ከእስራኤል ዘር በመወለድ ብቻ የሚገባበት ኪዳን ነው። አዲሱ ኪዳን ግን በትውልድ እስራኤላዊ ያልሆኑትን ሕዝቦች ሁሉ የሚያካትት (inclusive) ለዓለም ሁሉ መድኃኒትና መዳኛ መንገድ እንዲሆን የተሰጠና አህዛብንም አይሁድንም በክርስቶስ የሚያምኑትን ሁሉ እንደ አንድ ሕዝብ አድርጎ ያዋሃደ ኪዳን ነው። የዮሐንስ ወንጌል 3 16በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። ወደ ገላትያ ሰዎች 3 23 እምነትም ሳይመጣ ሊገለጥ ላለው እምነት ተዘግተን ከሕግ በታች እንጠበቅ ነበር። 24 እንደዚህ በእምነት እንጸድቅ ዘንድ ሕግ ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን ሆኖአል፤ 25 እምነት ግን መጥቶአልና ከእንግዲህ ወዲህ ከሞግዚት በታች አይደለንም። 26 በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤ 27 ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና። 28 አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና። 29 እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2 11 ስለዚህ እናንተ አስቀድሞ በሥጋ አሕዛብ የነበራችሁ፥ በሥጋ በእጅ የተገረዙ በተባሉት ያልተገረዙ የተባላችሁ፥ ይህን አስቡ፤ 12 በዚያ ዘመን ከእስራኤል መንግሥት ርቃችሁ ለተስፋውም ቃል ኪዳን እንግዶች ሆናችሁ በዚህም ዓለም ተስፋን አጥታችሁ ከእግዚአብሔርም ተለይታችሁ ያለ ክርስቶስ ነበራችሁ። 13 አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል። 14-15 እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥ 16 ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው። 17 መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን፥ ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ፤ 18 በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና። 19 እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም። የአዲስ ኪዳን መሠረትና የውል ስምምነት ከብሉዩ ኪዳን ጨርሶ የተለየ ነው። የአዲሱ ኪዳን የውል ስምምነት የተመሠረተው በድንጋይ ላይ የቀረጹትን ሕግጋት በመጠበቅ ወይም ባለመጠበቅ አይደለም። ነገር ግን በክርስቶስ ብቸኛ አዳኝነት በማመን ወይም ባለማመን ላይ ነው። እንደ ብሉይ ኪዳንም የእስራኤልን ሕዝብ ብቻ አቅፎ አሕዛብን የሚያገልል አይደለም፤ ነገር ግን ለእስራኤላውያንም ለአሕዛብም፤ ለዓለም ሕዝብ ሁሉ መዳኛ እንዲሆን እግዚአብሔር የሰጠው ኪዳን ነው። በረከቱም በከነዓን ምድር ገብቶ ምድራዊ በረከትን መቀበል አይደለም፤ ነገር ግን የአዲስ ኪዳን ዋናው በረከት መንፈሳዊ ነው ይህም በእግዚአብሔር ፊት መጽደቅን፣ ከፍርድ መዳንን፣ የዘላለም ሕይወት ማግኘትን፣ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንን ወዘተ የመሳሰሉትን መንፈሳዊ በረከቶችን ያካተት ነው። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1 3 በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ። የዮሐንስ ወንጌል 1 12 ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ 13 እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም። የዮሐንስ ወንጌል 3 16 በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።
Mostrar todo...
የብሉይና የአዲስ ኪዳን ልዩነት
ስለ ብሉይና ስለ አዲስ ኪዳን ንጽጽር ስናስብ ከሁሉ አስቀድሞ በመጀመሪያ አንድ ጥያቄ መመለስ ይገባናል። ይህም ከብሉዩ የተለየ አዲስ ሌላ ኪዳን ወይም አዲስ ውል ለምን አስፈለገ የሚለውን ጥያቄ መመለስ ይኖርብናል። እግዚአብሔር ገና በብሉይ ኪዳን ዘመን ነው አዲስ ኪዳን እንደሚያስፈልግ በነብያቱ የተናገረው። ትንቢተ ኤርምያስ 31 31 እነሆ፥ ከእስራኤል ቤትና ከይሁዳ ቤት ጋር አዲስ ቃል ኪዳን የምገባበት ወራት ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር 32 ከግብጽ አገር አወጣቸው ዘንድ እጃቸውን በያዝሁበት ቀን ከአባቶቻቸው ጋር እንደ ገባሁት ያለ ቃል ኪዳን አይደለም እነርሱ በኪዳኔ አልጸኑምና፥ እኔም ቸል አልኋቸው፥ ይላል እግዚአብሔር፦ 33 ከእነዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና፥ ይላል እግዚአብሔር ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ፥ በልባቸውም እጽፈዋለሁ እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል። በዚህ ክፍል እግዚአብሔር ራሱ ስለ አዲስ ኪዳን አስፈላጊነት በትንቢት በነቢዩ ኤርምያስ አማካኝነት ይናገራል። አዲስ ኪዳን ያስፈለገበትም ዋና ምክንያት የቀድሞውን ኪዳን እግዚአብሔር ስላልጠበቀ ወይም የቀድሞው ኪዳን መሠረት የሆነው ሕጉ መጦፎ ስለሆነ አይደለም። ነገር ግን ይህ ክፍል "እነርሱ በኪዳኔ አልጸኑምና" እንደሚለው ዋናው ችግር ያለው ከቃል ኪዳን ተጋቢዎቹ አንዱ ወገን ማለትም የእስራኤል ሕዝብ የቃል ኪዳኑን ውል ማለትም ሕጉን ስላልጠበቁና መጠበቅም ስላልቻሉ ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ ስለዚህ ጉዳይ በሮሜ መልዕክቱ ሲያስረዳ እንዲህ ይላል። ወደ ሮሜ ሰዎች 3 20 ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና። 21 አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ 22 እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤ 23 ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ 24 በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ። ትልቁ የብሉይ ኪዳን ችግር እንግዲህ ሰው ሕግን ሁሉ ያለምንም ስህተት ማድረግና መፈጸም ባለመቻሉ ነው። ስለዚህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ሊጸድቅ ስለማይችል በሕግ ላይ ያልተመሠረተ አዲስ ቃል ኪዳን አስፈለገ ማለት ነው። የአዲሱ ኪዳን መሠረት ለሰዎች ሁሉ ኃጢያት ስርየት በሞተው በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን "ያለ ሕግ" የሚገኝ ጽድቅ ነው። ይሄም ጽድቅ ሰዎች በራሳቸው ጥረት ሕግን በመጠበቅ የሚያገኙት የሰው ጽድቅ ሳይሆን "እንዲያው በጸጋው" ከእግዚአብሔር የሚቀበሉት "የእግዚአብሔር ጽድቅ" ነው። የብሉዩ ኪዳን ትልቁ ድክመት እንግዲህ ሰዎች ናቸው። በዚህም የተነሳ ብሉይ ኪዳን ሰዎችን የሚያጸድቅ ኪዳን መሆኑ ቀርቶ ሰዎች ሕግን መጠበቅ ባለመቻላቸው ምን ያህል ኃጢያተኞች እንደሆኑ ራሳቸውን የሚያዩበትና የሚኮንኑበት (condemn) ኪዳን ሆነ። የብሉዩ ኪዳን ለሰዎች ሕግንና በድንጋይ ጽላት ላይ የተጻፉ ትዕዛዛትን ቢሰጥም ሰዎቹ ያንን ሕግ የሚጠብቁበት ኃይል ግን አልሰጣቸውም ነበር። ለዚህ ነው ገና በብሉይ ኪዳን ዘመን ከላይ ባየነው የኤርምያስ ትንቢት እግዚአብሔር በአዲሱ ኪዳን ሕጉን በድንጋይ ጽላት ላይ ሳይሆን በሰዎች ልብ ላይ ራሱ እንደሚጽፍ የሚናገረው። „... ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ፥ በልባቸውም እጽፈዋለሁ...“ ኤርምያስ 31፤33 በ2ኛ ቆሮንቶስ መልዕክት ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ የብሉይ ኪዳንን እና የአዲስ ኪዳንን አገልግሎት ሲያነጻጽር የብሉዩን "የኩነኔ አገልግሎት" ወይም "የሞት አገልግሎት" በማለት ሰዎች ኃጢያተኞች መሆናቸውን ከማሳየት በስተቀር ሊያጸድቃቸው የማይችል አገልግሎት መሆኑን ሲገልጽ በአንጻሩ ደግሞ ሰዎችን ሊያጸድቅ የሚችል በመሆኑ የአዲስ ኪዳንን አገልግሎት "የጽድቅ አገልግሎት" እያለ ይጠራዋል። በብሉዩ ኪዳን የእስራኤል ሕዝብ ሊፈጽመው የማይችሉትን በድንጋይ ላይ የተጻፈ ሕግን ተቀብለው እንፈጽማለንም ብለው ቃል ኪዳን አደረጉ ነገር ግን መፈጸም አልተቻላቸውም። አዲስ ኪዳን ግን እግዚአብሔር ራሱ ሕጉን በሰዎች ልብ ላይ የሚጽፍበት የተለየ ኪዳን ነው። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 3 3 እናንተም በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በቀለም አይደለም፥ ሥጋ በሆነ በልብ ጽላት እንጂ በድንጋይ ጽላት ያልተጻፈ፥ በእኛም የተገለገለ የክርስቶስ መልእክት እንደ ሆናችሁ የተገለጠ ነው። 4 በክርስቶስም በኩል ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ያለ እምነት አለን። 5 ብቃታችን ከእግዚአብሔር ነው እንጂ፥ በገዛ እጃችን እንደሚሆን አንዳችን እንኳ ልናስብ ራሳችን የበቃን አይደለንም፤ 6 እርሱም ደግሞ በመንፈስ እንጂ በፊደል ለማይሆን ለአዲስ ኪዳን አገልጋዮች እንሆን ዘንድ አበቃን፤ ፊደል ይገድላልና መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል። 7 ዳሩ ግን የእስራኤል ልጆች ስለዚያ ስለ ተሻረው ስለ ፊቱ ክብር የሙሴን ፊት ትኩር ብለው መመልከት እስኪሳናቸው ድረስ፥ ያ በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ የሞት አገልግሎት በክብር ከሆነ፥ 8 የመንፈስ አገልግሎት እንዴት ይልቅ በክብር አይሆንም? 9 የኵነኔ አገልግሎት ክብር ከሆነ፥ ይልቅ የጽድቅ አገልግሎት በክብር አብዝቶ ይበልጣልና። 10 ያ የከበረ እንኳ እጅግ በሚበልጠው ክብር ምክንያት በዚህ ነገር ክብሩን አጥቶአልና። 11 ያ ይሻር የነበረው በክብር ከሆነ፥ ጸንቶ የሚኖረውማ እጅግ ይልቅ በክብር ሆኖአልና። የአዲስ ኪዳን የኪዳኑ ውልና መሠረት ከብሉይ ኪዳን የተለየ ነው። የብሉይ ኪዳን ውል፤ እግዚአብሔር በሚሰጣቸው ምድር የእስራኤል ልጆች በሕጉ ያሉትን ትዕዛዛት ሁሉ ሊፈጽሙ፤ እግዚአብሔርም አምላክ ሊሆናቸና ሊባርካቸው፤ ባይፈጽሙ ግን እርግማን እንደሚመጣባቸው ከሰጣቸውም ምድር እንደሚያባርራቸው የሚገልጽ ውል ነው። የአዲስ ኪዳን ውል ደግሞ ከዚህ እጅግ የተለየ ነው። የውሉም መሠረት ሕጉ ሳይሆን ለዓለም ኃጢአት ሁሉ ደሙን ያፈሰሰው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ሰዎች በክርስቶስ ቢያምኑ እግዚአብሔር ኃጢያታቸውን ይቅር እንደሚላቸውና እንደሚያጸድቃቸው የሚገልጽ "ያለ ሕግ" የሆነ ውል ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 3 21 አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ 22 እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤ 23 ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ 24 በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ። የዮሐንስ ወንጌል 3 16 በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። ወደ ሮሜ ሰዎች 7 4 እንዲሁ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ እናንተ ደግሞ በክርስቶስ ሥጋ ለሕግ ተገድላችኋል፤ ለእግዚአብሔር ፍሬ እንድናፈራ፥ እናንተ ለሌላው፥ ከሙታን ለተነሣው፥ ለእርሱ ትሆኑ ዘንድ። 5 በሥጋ ሳለን በሕግ የሚሆን የኃጢአት መሻት ለሞት ፍሬ ሊያፈራ በብልቶቻችን ይሠራ ነበርና፤ 6 አሁን ግን ለእርሱ ለታሰርንበት ስለ ሞትን፥ ከሕግ ተፈትተናል፥ ስለዚህም በአዲሱ በመንፈስ ኑሮ እንገዛለን እንጂ በአሮጌው በፊደል ኑሮ አይደለም።
Mostrar todo...
👍 2
Billionaire 💰🤑 መሆን ከፈለጉ አንድ አስገረም መንገድ ልንገራችሁ ተጠቀሙበት 👇👇Step 1 👇👇 የምለውን በመጫን ይጀምሩ
Mostrar todo...
Step 1