cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ISLAMIC TUBE

YE FKR TARIKOHN EZI CHANNEL WEST TAGEGALAHU ENA HULAM SHARE MADREGAHUN ATERSU 1K ENGEBALEN INSHALLAH

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
232
Suscriptores
Sin datos24 horas
-47 días
-1830 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

በፀሀፊ፦ሀፍሳ ክፍል፦2 #ረይሃን💔 ማታ ወደ ሂባ ክፍል ስገባ ያየሁትን ማመን አቃተኝ።ሂባ ከአልጋው ስር ተኝታ ይሁን ወድቃ አላውቅም ተጋድማለች።ወደሷ በፍጥነት ተራምጄ እቀሰቅሳት ጀመር ግን ልትነቃልኝ አልቻለችም።እነ ፌሩዝን ጠርቼ ማስጨነቅ ስላልፈለኩ ውሃ እያፈሰስኩ አየር እንድታገኝ ልብሷን ከፈት ከፈት ሳረግ ነቃች። "የፈጣሪ ያለህ ቆይ በዛው ብቀር ምን ነበረበት"ተማራ ተናገረች ከወደቀችበት ደግፌ ሳነሳት ገፈተረችኝ። ምንም ሳልል አያት ጀመር።ወረቀት አንስታ ሰጠችኝ አቀርቅሬ አየሁት።በሚያምር እጅ ፁሁፍ <<ረይሀን>>ተብሎ ተፅፏል "ስለሚገባሽ አደለም ግን በቃ እሷን ለማስታወስ ረይሃን እልሻለሁ....ግን ስሚ ረይሀን ሚለው ስም ተገብቶሽ አሊያም ወድጄሽ እንዳይመስልሽ እሺ የሰጠሁሽ" "እሺ..."ብበሽቅም ፈገግ አልኩላት።እየተንገዳገደች አልጋዋ ላይ ተቀመጠች። "እ...ሂባ እኔ ግን ስምሽን ወድጄዋለሁ ለዛ አልቀይርልሽም" "ብቀይሪውም አልሰማሽም ማን ስለሆንሽ ነው አንቺ የኔን ስም ምቀይሪው...."በንግግሯ ለመረጋጋት ስተነፍስ ስልኬ ጠራ እና አነሳሁት "እ...ደሞ ምን ቀረሽ??"ከማንሳቴ ጮኽኩ "አረ ባክሽ ምን ታስመስያለሽ ናፍቄሻለሁ" "ምን ባክሽ እንደዛሬ ደስ ብሎኝ አያውቅም ካንቺ ተለይቶ መኖር እንዲ ያስደስታል እንዴ??" "መቼስ በወፍ ቋንቋ እንዲ ያስለቅሳል እንዴ ለማለት ነው" "በይ ደሞ ደህና እየዋልኩት ነበር ሊጀምርሽ ነው ደህና እደሪ"ዘጋሁባት።በንግግራችን ቅንጣት የተቀየረ የፊት ገፅ ሳታሳይ እንዳቀረቀረች "ምንሽ ናት?"አለችኝ "እህቴ ናት....መርዋ ትባላለች።አሁን ወደ 12 ናት እ ላስተዋውቅሽ እችላለሁ" "አልፈልግም" "ኸይር አላስገድድሽም....እሺ ግን ትንሽ ስለራሳችን እንጨዋወት.....እኔ ሀፊዛ...እ..እእእ ማለቴ ይቅርታ ረይሀን እባላለሁ።መርዋ እና አቡበከር ሚባሉ እህት እና ወንድሞች አሉኝ።መርዋ በጣም እብድ ነገር ናት በነገራቶች መገልፈጥ ስራዋ ነው እና በጣም የዋህ ናት አቡኪ ደሞ ታላቄ ነው ትንሽ ኮራ ነገር ያለ ሲበዛ ደሞ አይነግቡ የሆነ ነው።እ...ሰው ብዙም አልቀርብም ለኔ ጓደኞቼ ቤተሰቦቼ ናቸው።ስራ ቦታ ለምሳ ምወጣው አቡኪ ከስራ ቦታው መጥቶ ጠርቶኝ ነው።ከሱ ጋር በልቼ ምናምን ነው ስራ ምገባው..."ስለ ራሴ ከዚ በላይ ማውራት አልቻልኩም "ወንድ ጓደኛ አለሽ??"አለች ዞራ ሳታየኝ "አ...አ...አ..አይይይ አአ አዎዎ አይ አዎአለኝ"ምንድነው ምላት??መልሴ ለራሴም አስደነገጠኝ።ፈገግ አለችና "ታምኚዋለሽ??"አለችኝ።ጥቂት ከራሴ ጋር ተከራክሬ "እኔንጃ...የፍርሀት እምነት ነው ማምነው"ፈገግ ብላ ዝም አለች። "እሺ ምን ትመክሪኛለሽ....እኔ ወንድ ቀርቤ አላውቅም ለመጀመሪያ ጊዜ አይን የጣልኩት እሱ ላይ ነው ምን ላርግ ሂቡ??እንደምወደው ስነግረው ሁሉንም ቢተወውስ ያ ስስቱ ያ ፍቅሩ ወደሱ ስሄድ ቢጠፋስ?" ስለሱ ሲነሳ ስሜታዊ ነው ምሆነው።እሷም አምኜ መንገሬ ሳያስገርማት አይቀርም "ወንዶች አስመሳዮች ናቸው.....ልንገርሽ የሚፈልጉትን ካገኙ ቡኋላ አያውቁሽም...."ዞራ በንቀት አየችኝ "የሚፈልጉትን ማለት??"አሁን እንደዚ ይባላል??አረ የኔስ ነገር ሲያስቅኮ እሷም ፈገግ አለች።እንደ ጨረቃ የነጡት ጥርሶቿ ብቅ ሲሉ ልብ ላይ አንዳች ደስታ ይፈጥራሉ።ባዘጋው ስል ተመኘሁ። "አረ በናትሽ ቀሽም አትሁኚ ገብቶሻል...."አለችና ኮስተር አለች።ፊቷ ከመቅፅበት ተለዋወጠ ወደ ፊት እየተመለከተች እጇን ጎን ካለው ትንሹ ቁምሳጥን ልካ መሳቢያውን ከፈተችውና አንድ ነገር አወጣች። "እ...እ...ምን ልታረጊ ነው??"ደንግጬ። "ባክሽ አታካብጂ...."አለችን ሲጋራውን አቀጣጥላ ወደ አፏ ላከችው።በጣም ደነገጥኩ።ፉቷ ላይ ሚወርደው እንባ እና ከአፍ እና ከአፍንጫዋ ምታቦነው ሲጋራ በጣም ስጋት ውስጥ ጨመሩኝ። "ትሰሚያለሽ....ነገ እንደኔ እንደዚ ከንቱ ሆነሽ ነው ምቀሪው ካሁኑኑ ልጁን ሽሺው...."አለች ዞራ ሳታየኝ "ቆይ አስረጅኝ እያረግሽ ያለሽው ምንድነው?" "የቤት ልጅ ነሽ ልበል??ብዙ ነገር አታቂም ቆይ ስታይኝ ቆሎ እየበላሁ እመስላለሁ እያረግሽ ያለሽው ምንድነው ትላለች እንዴ??" "እሺ ግን ለምን??ይህን ያክል ሚያስሆን ነገር ምን ገጠመሽ አንቺኮ ገና ልጅ ነሽ ብዙ ነገር ካንቺ ይጠበቃል" "አንዴ የረከሰን ማን ያነፃዋል ብለሽ ነው"አጪሳ የጨረሰችውን ሲጋራ እየረገጠችው ወደኔ ሰረቅ አርጋ አየች "አባትሽ ያውቃል??" "አይይ አያውቅም....ካወቀም ምንም አያመጣም በኔ ህይወት ማንም አያገባውም ማንም!! የኔን ህይወት ማሳመር ሚችለው ከሊፋ ብቻ ነው" "እሺ ማነው እሱ??" "አረ በናትሽ ዶክተር ስንቱን ነግሬሽ ትችይዋለሽ?" "እሺ የት እንዳለ ንገሪኝ....."maybe እሱን ባገኝ ሁሉም ነገር አሪፍ ይሆን ይሆናል "ሀፊዛን ጠይቂያት......"አለችና ሌላ ለኮሰች።እግሯ ስር ተንበርክኬ እንዳታጬስ ያዝኩባት። "ምን እያረግሽ ነው"አለች ወደሌላ ቦታ እያየች አፍንጫዋን በመጠራረግ "ሂቡ በአላህ ተይ እነ ፌሩዝ አያሳዝኑሽም እ አባትሽስ አያሳዝንሽም ቆይ ንገሪኝ እንቺስ እንደ ጓደኞችሽ አለም እየቀጩ መኖር አያምርሽም...??" "ሁሉም ነገር ከሊፋን ሳጣው አክትሞለታል" "አው ምናልባት የከሊፋ ጉዳይ ያኔ አከተመ እሺ ሁቢ የፌሩዝስ እ??እሷኮ ላንቺ ብላ በጣም እየተጎዳች ነው አባትሽስ ብትዪ ሁቢ ብቸኛ ልጅ ነሽ ካንቺ ሌላ ማንም የላቸውም.....አባትሽ ሁሌም እንደ አለቃ ፊቱን ያጨማድድብኝ ነበር ላንቺ ጉዳይ ግን እጅግ ሚስኪን ሆነ እየተቅለሰለሰ ነበር የጠየቀኝ ቆይ አንቺስ? ንገሪኝ አንቺ ለነሱ ውለታ መዋል እንጂ ይባስ እነሱን ማሰቃየት አለብሽ ማማዬ በአላህ ለነሱ ስትዪ ተይ" እጇን መነጨቀችኝና ተነሳች።ስትቆም ሰካራም ነው ምመስለው።እኔ እዛው እንደተንበረከክኩ ነኝ "ማንም የኔን ቁስል አይረዳም ማንም....አው ይገባኛል ያኔ ረይሃን ብቻ ነበረች የኔ ቁስል ሚያማት እሷ የቆሰለች ያህል ሚጠዘጥዛት"ሲጋራውን አፏ ውስጥ በንዴት ወሸቀችው "ተነሺ..."አለች አቡና ስታበቃ"በኔ ህይወት መፍረድም የመወሰንም መብቱ የኔ ነው ለዛ አጉል ሚስኪን ለመሆን አትጣሪ....."አለችና የነደደውን የሲጋራውን ክፍል አራገፈችው።ወዲያው ማሳል ጀመረች።ውሃ ቀድቼ ሰጠኋት ከሳሏ ረገብ ስትል ያላለቀለትን ሲጋራ መሬት ላይ ጥላ ጨፈደደችው "ቆይ ለምን አንተን መርሳት አቃተኝ??ከሊፋ ተሰቃየሁኮ ጎድተኸኝም እወድሃለሁ እህህህ ለምን ቆይ ለምን?"ግድግዳውን ታካ መሬት ላይ ቁጭ አለች። ግንባሯን ጉልበቷ ላይ ደፍታ እጆቿን እግሮቿ ላይ ጠመጠመቻቸው ጎኗ ተቀመጥኩ። "ሂባ...."አልኳት በረጅሙ ተንፍሼ ዝም።እያለቀሰች ነው "ትወጅዋለሻ" "በጣምምምምምም"ድምጿ በሲቃ ተደፍኗል "እሱስ??"ነገሩን በሂደት ነው ማወጣጣት ያለብኝ "አይወደኝም..."ለቅሶዋን ቀጠለች። "እና ለምን አንደዚ ትሆኚለታለሽ እ??እሱኮ ሚወደውን ሰው ነው ያጣው አንቺ ደሞ ማይወድሽን ሰው እና ሁቢ እሱኮ ነው መጎዳት ያለበት"ቀና አለችና በመገረም አየችኝ ሀሳቤን ሳትወደው አቀርም እንባዋን ጠረገችና መልሳ ፊቷን አጨፍግጋ አቀረቀረችና "ባክሽ ፍልስፍና ነው"አለች።በቃ እሷ ደርቃለች ንግግሮች ሊያሳምኗት አይችሉም........ ክፍል 3 ይቀጥላል...... ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ እናመሰግናለን። @YEFKERTARIKOH || ISLAMIC TUBE For any comment👇
Mostrar todo...
👍 2
♥️ #ገና_ወድሀለው . . . ♥️ ገና ወድሀለው . . . እንደ ንጋት ፀሀይ ልብ እንደሚያሞቀው እንደ ቀትር ጥላ ጉልበት እንደሚያድሰው እንደ ምሽት ጀምበር ልክ እንደሚናፈቀው ብዙ ይቀረኛል ገና #ወድሀለው🥰 ከሰማይ ሰማያት የሚወረወር ያ' ደማቅ ኮከብ ብርሀኑ የሚያምር ልክ እንደዛው ነው የኔና ያንተ ፍቅር፡፡🤗 ገና ወድሀለው ገና አፈቅርሀለው ገና ሰው እስኪገርመው አለም #እስኪቀና😊 እናንተም #ስሙኝ ልብ ይበል ልብ ያለው ማንም ከሱ አይለየኝም ገና #እወደዋለሁ🥰 @yefk6 ሼር አደራ🙏
Mostrar todo...
#ንገረኝ_በሞቴ❤️‍🔥❤️‍🔥 ፍቅርህን መርጬ ኩራቴን ገፍቼ💔 የሴትነት ወጉን መግደርደሩን ትቼ ከማውቃቸው ሁሉ ላንተ ተሸንፌ🥰 ወደድኩህ ማለቴ ቃል መውጣቱ 'ካፌ እሱ ይሆን እንዴ ያደረገህ ኩሩ🙁 ንገረኝ በሞቴ ምንድነው ችግሩ?😔 🥺💔💔 @YEFKERTARIKOH ሼር አደራ🙌
Mostrar todo...
❤️‍🔥❤️‍🔥💔#ትሂድ🚶‍♀🚶‍♀ እንዲያው ጥላ መሄድ የሚወዳትን ሰው የልቧን ፍላጎት ሙሉ ካደረገው😏 አልከለክላትም ትሂድ ትነሳና ይበጀኛል ብላ ባየችው ጎዳና🙌 ከእኔ ጋር መሆኑ እሬት ከሆነባት☹️ የሰጠኋት ፍቅር ሰላሟን ከነሳት❤️‍🔥 እንግዲያውስ ትሂድ አልከለክላትም ውደጂኝም ብዬ አላስገድዳትም👐 ልቧም ተጓዥ ካላት ብረሪ ክነፊ ሂጂ ነው የምላት ካሻሽ ዘንድ እረፊ💔 መንገደኛው ልቧ ለመሄድ የቃጣው ታግዬ አላስቀረው ከመንገዱ አልገታው ስለዚህ ትገስግስ መንገዱን ካሰበች እኔም 'ሸኛታለው ድካሙን ሳልሰለች🫡❤️ @YEFKERTARIKOH ሼር አደራ🙏
Mostrar todo...
መዉደዴ ሲበዛ ጠላሁህ መሰለኝ❤️‍🔥 አዎን አፍቅሬአለሁ አዎን ወድጃለሁ ሳይህ ደስ ይለኛል🥰 ከፍቅርህ ፅዋ ላይ ብዙ ጠጥቻለሁ❤️ መዉደዴም ከፍ አለ ጨመረብኝ መሰል አቅም አጥቻለሁ ❤️‍🔥 አይንህን ካላየዉ ልቤ ያንተ መስሚያ ታማብኝ አድራለሁ😟 አዎ አዎ አዎ ተፀብዬአለሁኝ ከርሜአለሁ ካንተ ፍቅር ይዞኝ ይሆን ምሮጠዉ ወደ አንተ😊 ፍቅርህ ጠፍቶብኛል ሳይህ ደሞ ያመኛል😡 ብልስ ማን ያምነኛል🥹 ጠረንህ አጥፍቶኝ ሰክሬ ባይኖችህ 😊 ተንገዳገድኩ ይሄዉ አቅም አጣዉልህ😔 አሁን ትቼልሀለሁ 🤧 አሁን ከድቻለሁ💔 ፍቅር ማፍቀር በቃኝ ፍቅር ጠልቻለሁ❤️‍🔥 መዉደዴ በዝቶብኝ ጠላሁህ ብያለሁ😮‍💨 ማፍቀር ያቃታት ሴት ድኩማን ሆኛለሁ‼️ ✍ህሊና 🦋🦋 @YEFKERTARIKOH ሼር አደራ🙏
Mostrar todo...
❤️❤️‍🔥 ገና ስትመጪ ሳይሽ ከሩቅ ማዶ ሌላ አላይ አለኝ ልቤ አንቺን ወዶ ልቤም ቸኮለ አይናቼም ፈጠጡ😳 በፍቅር እግሮቼ #ውዳንቺ እየሮጡ🤭🙄 ሰላምታ ጠየኩኝ እጆቼን ዘርግቼ አይንሽን እያዩ ሁለቱም አይኖቼ😊 በጣም ደስ ብሎኝ ከልቤ እየሳኩኝ😍 አንደበቴ ተከፍቶ እንቀመጥ አልኩኝ😧 ዛፍ ስር ቁጭ ብለን ብዙ ስናወራ አውጥቼ  ልነግርሽ #የልቤን_መከራ🤥 ዘቅዝቄ ነገርኩሽ ሁሉን በየተራ #ፍቅሬን  እንዳልነግርሽ አንደበቴ ፈራ😥 እንግዲህ ልንገርሽ ልግለፀው እውነቱን አይኔ ይነግርሻል ባንቺ #መጎዳቱን 😔 ካንቺ ተለይቼ መኖር አይሆንልኝ #አፍቅሬሻለሁኝ ባክሽ እወቂልኝ!!☹️ ✍ፀሐፊ (Thomas) @YEFKERTARIKOH #ሼር አደራ🙏
Mostrar todo...
በፀሀፊ፦ሀፍሳ ክፍል፦1                 #ረይሃን💔 ልክ የሱብሂ አዛን ሲሰማ አያይዞ ስልኬ ጠራ።እኔም ወዲያውኑ ነቃሁና ወደ ስልኬ ተንጠራራሁ።ለማንሳት ባልፈልግም በዚ ሰዓት መደወሉ በጤና እንደማይሆን ስላበሰረኝ ሳልፈልግ አነሳሁት። "እ...ምነው??"ከመናደዴ የተነሳ ሰላምታ አላስቀደምኩም። "ሀፉ ሰላም አለይኩም" "ወአለይኩ መሰላም"እንደ መረጋጋት እያልኩ "በጠዋት ደውዬ ረበሽኩሻ??"በጠዋት ይላል እንዴ ነው ወይስ ሰዓቱ ሄዷል።መጋረጃውን ስከፍተው ለሊት መሆኑን እንደመጥራት ሚለው ጨለማ አመላከተኝ። "አረ ምንም አይደል ግን በሰላም ነዋ??" "በሰላም ነው...እ...ዛሬ ላገኝሽ ፈልጌ ነበር" "ሁዜ ይሄኮ ቀን ሚደርስ ጉዳይ ነበር አይደለም እንዴ? ምንድነው ነገራቶችን ያለ ጊዜያቸው ምታጣድፋቸው" በሸቅኩበት። "ሀፉ እንደዛ ሳይሆን ቀን እዚ አይደለሁም እና ጠዋት 1 ሰዓት ብቻ ነው ሚመቸኝ....ለዛ ነው" "ማለት??" "ሁሉንም ስመጪ እናወራለን"ግራ ቢገባኝም እሺ ብዬው ዘጋሁት።ሁዜ ምን ገጥሞት ይሁን እያልኩ ኡዱዕ አድርጌ ከሰገድኩ ቡኋላ ኪችን ገባሁ።ከማማ ጋ እንደወትሮዋችን እየተንጎዳጎድን መንጋት ጀመረ።ስልክ ሲደወልልኝ መርዋ ይዛው መጣችና "ሰውዬሽ ደወለ..."አለች አቀብላኝ ከሰራሁት ፍርፍር እየጎረሰች።ደዋዩን ሳየው ከoffice ነበር "ማነው ሲጀመር ሴት ይሁን ወንድ ታውቂያለሽ?እ?" "አዋአ መቼስ ለጤናው አይደል ቀን ሙሉ ስራ ካጣሽ ሚደዋውለው ሴት ብትሆን ታባርሽ ነበር ወንድ ስለሆነ ነው እንጂ ሚለማመጥሽ"አለችና ሌላ ለመጉረስ አንስታ ልከት ስትል አቡኪ ከኋላ ወገቧን አቀፋትና ከአንገቷ በኩል ብቅ ብሎ እንድታጎርሰው አፉን ከፈተላት እሷም አጉርሳው ለራሷ ሌላ አነሳች። "ቆይ እኔ ላናግርልሽ እስቲ"አለና ያጎረሰችውን ውጦ ሊዘጋ የደረሰውን ስልክ አነሳው። "ሰላም ዶክተር ሀፊዛ አስቸኳይ ነው ቶሎ ወደ ቢሮ ትመጪ"ላውድ ላይ ስለነበር ሁላችንም እየሰማን ነበር ስልኩን ከአቡኪ ነጥቄ "እ...አለቃ??ቀጠሮ ነበረብኝ እንድቆይ ይፍቀዱልኝ" "በጣም አስቸኳይ ነው ከአንድ ሰዓት እንዳታልፊ"ተዘጋ ሁሉም እንደጠበቁት አይነት ጉዳይ ሆኖ ስላላገኙት ተነፈሱ።እኔም ጭንቅ ብዬ ከኪችን ወጣሁ።ሁዜ ወይስ ስራው??በፍጥነት ለሁዜ ደወልኩለት "ሄለው አሰላሙ አለይኪ" "ወአለይከ ሰላም እ ሁዝ ስራ ቦታ በአስቸኳይ ቀጥረውኛል maybe የግል ዶክተር ሚፈልጉ ሰዎች ተገኝተው ይሆናል ቀጠሮውን ብናራዝመውስ" "ሀፉ ይህ ማይሆን ነገር ነው ግን በቃ አትጨነቂ ሚመችሽ ቀን ደውዪልኝ"አለና ዘጋው።እየሆነ ያለው ግራ ያጋባል።ግን ያው መሰበር አለብኝ።ቁርስ በልቼ ለባብሼ ወደ ስራ ቦታ አቡኪ አደረሰኝና ሄደ።እዛ ስደርስ በርግጥም ጉዳዩ የግል ዶክተር ሚፈልጉ ሰዎች ጋር እኔን ምደባ ነበር።እኔም ቀለል አርጌ ተስማማሁና ቢሮ ገባሁ።ስለ ፔሸንቷ ምንም አልነገሩኝም ግን ከባድ ስለመሆኗ ከውይይቱ ተረዳሁ።ከከሰዓት አለቃዬ ቢሮ መጣ።የሚገርመው ቢሮዬ አደለም ለመምጣት ከበር ስለማለፉ ሁላ እጠራጠራለሁ።የፈለገ አስቸኳይ ቢሆን ራሱ አስጠርቶ ነው ሚያወጋኝ እንጂ ፈፅሞ ቢሮዬ አይመጣም።እንዲቀመጥ በክብር ስነግረው ተቀመጠ። "እ..ለምን ጉዳይ ነበር??"ምን ማለት እንዳለብኝ ሁላ አላውቅም።ብቻ መርዋ እንዳለችኝ ሆኖ ብቻ እንዳላርፈው!!!! "እ...ምን መሰለሽ ዶክተር እ..እ"አረ ጉድ ነው ምን ሆነ ሰውዬው?? "እ...ምንድነው ነገሩ??" "ቅድም የነገርኩሽ ፔሸንት..."ኡፍ ዋናው ስለዛ ጉዳይ አለመሆኑ ነው ሌላው ሌላ ነው። "እ...እሷ ምን አለቃ" "ልጄ ናት!!"ከማለቱ አይኔ ፈጠጠ። "እ...እእእ...እውነትህን ነው??አረ ደስ ይላል ልጅ ያለህ አትመስልምኮ" "እህህህ አይደል..."ለንግግሬ ቦታ አልሰጠውም"ስሚኝ ሀፊዛ...ልጄ በጣም ነው የተጎዳቸው ከምነግርሽ በላይ እና የግል ዶክተሯ ሆነሽ እስቲ እሷን ለማትረፍ ሰበብ ለመሆን ሞክሪ ዛሬ ቤትሽ ልሸኝሽና እቃሽን ይዘሽ እኛ ቤት ነይ" "ማለት ተመላላሽ ብሆንስ??" "እያደርሽም ስለመዳኗ እጠራጠራለሁ አደለም ተመላላሽ" "እሺ ግን ማማ ማለቴ ቤት እሺ ሚሉ አይመስለኝም" "ከውጭ በቅርቡ ሚመጣ ወንድም አለኝ እሱ ይፈስሽ እንዴ"ፈገግ አለ "ሃሃሃ አይ ዶክተር ማማስ ለዲያስፓራ ምድረኝ ይመስልሃል...በል እሺ እናስፈቅዳትና እኔዳለን"ብዬ ተነሳሁ።ቤት እንደደረስን ማማ ጉዳዩን እጅጉኑ ተቃወመች ባባ ደሞ ሄጄ አጣርቼ ልምጣና እውነት ከሆነ ትሂድ ስራዋ አይደል??ብሎ ማማን አረገባት።ባባ እኔ እና አለቃዬ ወደተባለው ስፍራ አቀናን።ባባ ሁሉንም ካየ ቡኋላ ፈቀደልኝና ሄደ።እኔ ዙሁር ሰግጄ ምሳ ስበላ ስለነበር ፔሸንቷን ለማየት አልቻልኩም ነበር።ወደ 8 ሰዓት አካባቢ የአለቃዬ ሚስት የፔሸንቷን ክፍል ጠቁማኝ ገባሁ።ጀርባዋን ለበሩ ሰጥታ ተቀምጣለች። ልብሷ እጅግ ለብዙ ቀን እንደተለበሰ ያስታውቃል።ፀጉሯ ጭብርር ብሎ አፈር ውስጥ የተንከባለለች ይመስላል ክፍሏ ሰፋ ያለ ነው ግን ብዙም ብርሃን እንዲገባበት አልተደረገም። "እ...ሂባ እስቲ አውሪያት እሷን"አለ አባቷ እየገባ ዝም አለችው።ረጋ እንዳልኩ ጎኗ ተቀመጥኩ ፊቷ በእንባ ረጥቧል። "እስቲ እንተዋወቅ ሀፊዛ እባላለሁ"አልኳት በዝምታዋ እንደፀናች ነው።አባቷ እንድናወራ ሲወጣልን "እሺ ተዋወቅና...."አልኳት "ከኔ ህይወት ጋር ማይገናኝ ነገር ሚቀባጥሩ ሰዎች ያስጠሉኛል"ድምጿ ከመማረኩ ባለፈ እጅግ ሀሴትን ያላብሳል። "ኸይር እሺ ይቅርታ" "ደሞ ሀፊዛ ሚባል ሰው በጣም ነው ምጠላው??" "እህህህ ለምን??" "በቃአ መብቴ መሰለኝ ሁሉ ነገሬን ያሳጣችኝ ሀፊዛ ምትባል ሰው ናታ" "እና በሷ የተነሳ እኔን ትጠይኛለሽ??" "አዎዎዎ እኔ አንቺን ብቻ ሳይሆን ማንንም አልወድም ከሊፋን ብቻ ነው ምወደው" "ማነው ደሞ እሱ??" "ምናገባሽ" "እሺ ሂቡ በቃ ስም አውጭልኝና በዛ ስም ጥሪኝ" "ይሻላል???¡¡"በጣም የመረራት ሰው ናት "ሂቡዬ በቃ አሁን እርሺው እሺ ይቅርታ በቃ" ዝም።ሁኔታዋ ስላልጣመኝ አስተኛኋትና ከክፍሏ ወጣሁ "እ...አለቃ አንዴ ላናግርህ ነበር"ሳሎን ስገባ እሱ እየወጣ ነበር። "እ...ሀፊ ችግር አለ??"አለኝ ወደኔ እየመጣ "ሳይሆን እንድናወራ ፈልጌ ነበር....ፌሩዝ አንቺም ነይ" አልኩና መጅሊሱ ላይ ተቀመጥኩ።ፌሩዛ የአለቃዬ ሚስት ናት ውበቷ ለጉድ ነው።በተለይ ፈገግታዋ ያስቀናል።ለሶስታችንም ሻይ አቅርባ ተቀመጠች... "ቆይ እስቲ ንገሩኝ ምን ሆና ነው ግን ሂባ??" "እኛ በምን አውቀን ልክ 11 ስትገባ ሁሉም ነገሯ ብቸኝነት ሆኖ ነበር ክፍሏ መዋል ምናምን አብዝታ ነበር እናም በቃ ልክ 11 ስጨርስ እንዲ ሆና ቀረች።"ፌሩዝ አቀርቅራ "ያሳዝናል...በጣምኮ ነው የተጎዳችው"አልኩ ከንፈሬን ነክሼ። "ከሊፋ...."አለቃዬ ድምፁን ቀንሶ ተጣራና አይኑን መልስ ፍለጋ መሬት ላይ አንከራተተው።ይህን ስም ከሂባ አፍ ሰምቼዋለሁ። "እ...ቆይ ማን ነው እሱ እ...ማን ሊሆን ይችላል?" "እኔም እሱ ነው ጥያቄ የሆነብኝ እኔ በሱ ሰበብ እንዲ ስለመሆኗ አልጠራጠርም።"አለኝ ስንወያይ ሰዓቱ ሄደና ተበታተንን ማታ ወደ ሂባ ክፍል ስገባ ያየሁትን ማመን አቃተኝ.......... ክፍል 2 ይቀጥላል...... ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ እናመሰግናለን። @YEFKERTARIKOH || #ISLAMIC #TUBE For any comment👇 @YEFKERTARIKOH2
Mostrar todo...
✍......ሪያድ ፍቅር ሙሉ የሚሆነው በትዳር ውስጥ ሲሆን ትዳር የሚጀመረው ደግሞ በ ኒካህ ነው። @YEFKERTARIKOH
Mostrar todo...
የአፋልጉኝ ጩኸት! የበፊቱ “እኔ” ስለጠፋብኝና ስለናፈቀኝ አፋልጉኝ! •  ደስተኛና ተጫዋች የነበረው “እኔ”! •  ብሩህና ነገር ይገባው የነበረው “እኔ”! •  ፈገግተኛና ሳቂታ የነበረው “እኔ”! •  ሰዎችን ያምንና ይቀበል የነበረው “እኔ”! •  ያፈቅርና ይፈቀር የነበረው “እኔ”! •  በሰላም ይተኛና ይነሳ የነበረው “እኔ”! •  ለነገ ይጓጓና ዓላማ-መር የነበረው “እኔ”! •  ላመነበት እውነት ቆራጥና ጽኑ የነበረው “እኔ”! •  ልኩንና ሚዛኑን ያውቅ የነበረው “እኔ”! •  ራሱን ተቀብሎና ሆኖ ይኖር የነበረው እኔ! ቀድሞ የነበረው አሁን ግን የጠፋብኝና እዚህ የሌለው ትክክለኛው እኔነቴ ናፈቀኝ! ═══════════════════ SHARE and JOIN🙏 @YEFKERTARIKOH @YEFKERTARIKOH 👆👆👆JOIN👆👆👆 ═════════════════
Mostrar todo...
ሆንኩልሽ ገጣሚ ትተሺኝ ስቴጂ     መማፀኛ ቃላት ፈለቀልሽ ካፌ ማወደሻ ቃላት አሰብኩኝ በመንገድ ተቀምጬ ካፌ። ይከፋኝ ጀመረ                 በሰበብ አስባቡ ቆራጥ የነበርኩት                ሆንኩኝ ሆደ ቡቡ። ብስጩ ሆንኩልሽ                 ተመለጠ ፀጉሬ ይበርደኝ ጀመረ                 ከራስ እስከ ጥፍሬ።   ብርዱን ስላልቻልኩት                  ኮፍያ ገዛውኝ ትንፋሽሽ ያሞቀው                  አንገቴን በረደኝ አልቻልኩትም በቃ                እስካርፕም ገዛውኝ። ቢከፋሽም ውዴ                 እውነት ሀቁን ስሚ ፍቅርሽ ገፍቶ ገፍቶ                 አረገኝ ገጣሚ 💛 @YEFKERTARIKOH ❤️ 💛 @YEFKERTARIKOH ❤️
Mostrar todo...