مذهب السلف الصالح
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Carga de datos en curso...
هدفنا الذب عن السنة ይህ ቻናል የአቡ አብዱረህማን አብዱል ቃድር ሀሰን ደርሶች ሙሓደራዎች እና ጠቃሚ የሆኑ ፈዋኢዶች የሚለቀቁበት ቻናል ነው ይቀላቀሉ ➘➘➘➘➘➘➘➘
https://t.me/abuabdurahmenhttps://t.me/abuabdurahmen
https://t.me/abuabdurahmen
ካሚል ሸምሱ፣ ኢልያስ አህመድ እና ሳዳት ከማል ============> 🎙 ካሚል ሸምሱ፦ ➲ ❝ሱፊ ነን የሚሉት በፊደራልም በአድስ አበባም በተለያዩ ክልል መጅሊሶችም እንዲካተት አድርገናል።❞ ➲ ❝አሁን ያለው መጅሊስ መውሊድን ኮሚቴ አዋቅሮለት በጀት በጅቶለት መውሊድ እንዲከበር እያደረገ ያለ መጅሊስ ነው።❞ 🎙 ኢልያስ አህመድ፦ ➲ ❝ይህ (መጅሊስ) የተለያዩ አመለካከት ያሏቸው ከተለያዩ background የመጡ ስብስቦች በአንድ ... የሚመሰርቱት ህብረት ነው❞ ➲ ❝ሌሎችን የምንገፋ ከሆነ ለሌሎች እውቅና የማንሰጥ ከሆነ....❞ 🎙 ሳዳት ከማል፦ ➲ ❝የመጅሊሱ ሰዎች ከእኛ በእድሜ የጠገቡ ናቸው❞ ➲ ❝እንዳንተ ልጅ አይደሉም ጅል አይደሉም፤ ልጅና ጅል ቶሎ አይበስልም❞ ➲ ❝ስትሸብት መብት እያለህ እንደሌለህ ሆነህ መንግስት ቤት ሆነህ ትለምናለህ።❞ ጊዜ ሳገኝ በማብራሪያ እመለሳለሁ 📝 ➷➘➴ ጠብቁኝ!!!
https://t.me/AbuImranAselefyየሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) አጭር የሕይወት ታሪክ:ክፍል-1 አል-ሙጀዲድ ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) በሒጅራው ቀመር አቆጣጠር በ'1115 ኡነይዛ ከተሰኘች ከተማ ተወለዱ። ኡነይዛ የተሰኘችው ከተማ፣ ከሳዑዲ አረቢያ ዋና ከተማ ከሪያድ በስተ ሰሜን-ምእራብ 70 ኪሎሜትር ያክል እርቀት ላይ ትገኛለች። የሸይኹ ቤተሰቦች የተከበሩና ዑለማኦች ነበሩ። አባቱ ሸይኽ ዐብዱል-ወ'ሓብ ብን ሱለይማን (ረሂመሁላህ) ጥልቅ እውቀት እንዳላቸውና እንዲሁም አጅግ ትሁትና መልካም ሰው እንደነበሩ ይነገራል። የሙሐመድ ዐብዱል-ወ'ሓብ አባት እውቀትን የቀሰሙት፣ ከአባታቸው ከሸይኽ ሱለይማን ብን ዐሊይ እንደሆነ ታሪክ ይዘክራል። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ሸይኽ ሱለይማን ብን ዐሊይ (ረሂመሁላህ) በጊዜው ከነበሩ ዑለማኦች፣ዋና ሊቀመንበርና ፈትዋ ሰጪ እንደሆኑ ታሪክ ያስረዳል። አል-ሙጀዲድ ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) የመጀሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን የተማሩት ከአባታቸው ነው። ይህም የሆነው እዛው በትውልድ ስፍራቸው ላይ ነበር። ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) ታንፀው ያደጉትም በአባታቸው ነበር። ሸይኹ ቁርኣንን የሃፈዙት ገና በለጋ እድሜያቸው ላይ ነበር። ይህም የሆነው 10 አመት ሆኗቸው ሳለ ነበር። ሸይኹ ተፍሲር፣ሐዲስ፣ፊቅህ...ተምረዋል። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ ሸይኹ የሰለፎችን ኪታብ በብዛት እንደማያነቡ ይነገራል፣በተለይም የሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያና ብርቅዬ የሆነው የተማሪያቸው የኢብኑል ቀይምን ኪታቦች ማንበብ ያጓጓቸው እንደነበር የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ። ሸይኹ እድሜያቸው ለጉርምስና በደረሰ ጊዜ፣ከአምስቱ የኢስላም ማዕዘናት የሆነውን ሐጅን ለመፈፀም ወደ መካ አቀኑ፤ከዚያም መካ ከሚገኙ ዑለማኦች እውቀትን ቀሰሙ። ሸይኹ ከመካ ቆይታ በኃላ፣እውቀትን ለመቅሰም ወደ መዲና አቀኑ፤እዛው መዲና ጥልቅ እውቀት ያላቸው እንደነ፡ ሸይኽ ዐብዱሏህ ቢን ኢብራሂም ብን ሰዒድ ነጅዲ እና ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት ሲንዲ የመሳሰሉ ከታላላቅ ሙሁሮች ጋር ለረጅም ጊዜ ተማሪ ሆነው አሳለፉ። ሸይኹ እውቀትን (ዒልም) ፍለጋ በመካና መዲና ላይ አላበቁም። ሸይኹ ለዒልም ከነበራቸው ከፍተኛ ጉጉትና ፍላጎት ፣መዲና ላይ ለረጅም ጊዜ ከተማሩ በኃላ፣ ወደ ኢራቅና በስራ ጉዞ አቀኑ። ይሁን እንጂ፣ በዚህን ጊዜ የነጅድ ሁኔታ በጣም አስቸጋሪ ነበር፤ማለትም የተለያዩ ሺርክያቶች፣ ኢስላማዊ ያልሆኑ ድርጊቶች ይፈፀሙ ነበር። ሙሉበሙሉ በሚባል ደረጃ ነጅድ በሺርክ ማዕበል ተጥለቅልቃ ነበር። መቃብሮች፣ ዛፎች፣ ድንጋዮች፣ዋሻዎች፣መጥፎ መንፈሶች፣ከአላህ ውጭ ይመለኩ ነበር። መሰረት የሌላቸው አፈታሪኮችና ትንበያዎች በጊዜው ተንሰራፍቶ ነበር። በጊዜው የነበሩ ዑለማእ ተብዮችም ስሜታቸውን በመከተል ህዝቡን ከትክክለኛው መስመር ኢንዲስት አደረጉት። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ጠንቋዮችና ትንቢት ተናጋሪዎች በጊዜ በህብረተሰቡ ላይ ተፅኖ ፈጣሪ የሚባሉት እነሱ ነበሩ። እነኝህን አካለት፡ ማለትም ጠንቋዮችን፣ትንቢት ተናጋሪዎች፣አጋሪዎች...በጊዜው ደፍሮ ሚጋፈጣቸው ሰው አንነበረም። በተመሳሳይም ይህ ሁኔታ በመካ፣በመዲና እንዲሁም በየመን ላይ ይስተዋል ነበር። ሸይኹ ትልቅ የዳዕዋ ተልእኮና ዓላማ አንግበው ተነሱ። በርግጥ ለሸይኹ ትልቅ ፈተና ነበር። በርግጥም፣ ይህንን ተለዕኮ መፈፀም ከባድ ፈተና እንደሆነ ለሁሉም ግልፅ ነው። ሸይኹ በቁርጠኝነት ጥሪያቸውን አንግበው ተነሱ። ሰዎችን ወደ ተውሒድ ጥሪ አደረጉላቸው፤ ወደ ቁርኣንና ሱንናም ጥሪ አደረጉላቸው፤ በጊዜው የነበሩ ዑለሞችንም ወደ ቁርኣንና ወደ ሱንና እንዲመጡ አነሳሷቸው። ሸይኹ በዚህ ብቻ አላቆሙም፤ጭፍን ተከታይነትን አጥብቀው ተቃወሙ። ከጭፍን ተከታይነት ወጥተን ቁርኣንና ሱንናን እንከተል የሚል ጥሪም አቀረቡ። ሸይኹ ጥሪያቸው አጥብቀው ባለማቋረጥ ቀጠሉ፤ ሸይኹ ለተለያዩ በጊዜው ለነበሩ ዑለሞች ይህንን አስከፊ ሺርክ ለማጥፋት ከጎናቸው እንዲቆሙ ጥሪ አቀረቡ። ይህንን የሸይኹን ጥሪ አያሌ የሆኑ ዑለማኦች...ከመካ፣ከመዲና እንዲሁም ከየመን የሸይኹን ጥሪ በመቀበል ሸይኹንም በመደገፍ ከሸይኹ ጎን ተሰለፉ፤ ረዱትም ጭምር። ከፊሎች ደግሞ፣ ዳር በመያዝ ሸይኹን መተቸትና ማብጠልጠል ጀመሩ። ልብ ይበሉ! እንደዚህ የሚያደርጉት ዓለማዊ ጥቅም ፈላጊ ዑለማእ ተብየዎች ናቸው። በዚህ ብቻ አላበቃም ሌሎችን በሸይኹ ላይ በማነሳሳት ዳዕዋውን ለማኮላሸት መሞከራቸው የሚዘነጋ አይደለም። ሸይኹን የነዚህ ጥቅመኛ ዑለማእ ተብየዎች አመፅና ትችት ከዳዕዋው ዝንፍ አላደረጋቸውም፤በል እንዳውም ሸይኹ የተውሂድን ጥሪ ለማድረስ ወደተለያዩ ስፍራዎች አቀኑ። ለምሳሌ፡ "ዘቢር፣ አሕሳ፣ሁረይመለ..." ከዚያም ዑወይነህ ደረሱ። ዑወይነህ ከደረሱ በኃላ፣የገጠማቸው መልካም ነገር ነበር። በጊዜው የነበረው የዑወይነህ አስተዳደር፡ ዑስማን ብን ሐምድ ብን መ'ዕመር ይባላል። ይህ አስተዳደር ሸይኹን በደስታ ተቀበላቸው፤እንዲሁም ከሸይኹ ጎን እንደሆነና ሸይኹ ደዕዋቸውን ማስኬድ እንደሚችሉ አረጋገጣላቸው። ሸይኹም እራሳቸውን ይበልጥ ለተውሂድ ተልዕኮ አዘጋጁ። ኢንሻአላህ ይቀጥላል.... https://t.me/semirEnglish https://t.me/semirEnglish
የሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) አጭር የሕይወት ታሪክ:ክፍል-2 (የመጨረሻው ክፍል) ክፍል-1ን ለማግኘት⬇️ https://t.me/semirEnglish/2914 ፡ ፡ ፡ ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) የዑወናው አስተዳደር አቀባበል ካደረገላቸው በኃላ፣ሸይኹ በከፍተኛው ሞራልና ትግል ዳዕዋቸውን በቁርጠኝነት ቀጠሉ። ዑወይነህ ላይ ሲፈፀሙ የነበሩ አስቀያሚ ሽርኪያቶች ሸይኹ ሰበብ በማድረሳቸው በአላህ ፍቃድ ሊጠሩ ችለዋል። እዛው ዑወይነህ ከተማ ውስጥ ሸይኹ ከመሄዳቸው በፊት፣ መቃብሮች፣ዋሻዎች፣ዛፎች...በሙስሊም ተብዬዎች ይመለኩ ነበር፤ሆኖምግን በዑወይነህ አስተዳደር አሚር ዑስማን ቢን መ'ዕመር...ከሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) ጎን በመሰለፍ የተለያዩ የባዕድ አምልኮ ተግባራትን በአላህ ፍቃድ ሊያስወግዱ ችለዋል። ይህ ደግሞ የሆነው፣ዑወይነህ ከተማ ብቻ ሳይሆን ዙሪያውን ጭምር ነው። ይህ በንዲህ እንዳለ፣በዑወይነህ ከተማ ውስጥ የእስልምና ህግጋት ተግባራዊ መሆን ጀመሩ። ለአብነት ያክልም...አንዲት ባለትዳር ሆና ዝሙት የፈፀመች ሴት ኢስላማዊ ህግጋት በሷ ላይ ተግባራዊ አንዲሆን ሸይኹን መጥታ ጠይቃለች። ዝሙት የፈፀምችው ሴትዮዋ ኢስላማዊ ህግጋት በሷ ላይ ተግባራዊ ኢንዲሆን መጠየቋን ተያይዞ፣ ስለ ሁኔታዋ፣ማለትም ጤነኛ ነች ወይ? ተገዳ ነው ወይ? የሚሉ ምርመራዎች ከተካሄዱ በኃላ፣እንዲሁም ወንጀሉ ከተረጋገጠ በኃላ፣ ሸይኹ ተወግራ እንድትገደል አዘዙ። የሸይኹ ዝናና ጀብድ በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋና እየተሰራጨ መሄድ ጀመረ። ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) "የዑወይነህ" ቆይታቸውን ካጠናቀቁ በኃላ፣ "ደርዒየህ" ወደ ተሰኘች ከተማ አቀኑ። ሸይኹ ወደ "ደርዒየህ" ማቅናታቸውን ከታወቀ በኃላ፣የአል-አህሳ አስተዳደርና እንዲሁም ብን ሱለይማን የሸይኹን ገናናነት እና ተፅኖ-ፈጣሪ መሆናቸውን ለመለየት በህዝብ መካከል ሆኖ ይከታተል ነበር። ሁኔታው አጅግ በጣም አስፈራው፤ምክንያቱም ስልጣኔ ይነጠቃል የሚል ስጋትም ጭምር አደረበት። ይህ ሱለይማን የተባለው ግለሰብ፣ለአሚር ዑስማን ስጋቱን በመግለፅ ሸይኹን እንዲገላቸው ጥያቄ አቀረበ፤ይሁንእንጂ አሚር ዑስማን የሱለይማንን ጥያቄ ለመቀበል ፍቃደኛ አንነበሩም። ሱለይማን የአሚር ዑስማንን አቋም ከተረዳ በኃላ ተሸበረ፣ተጨነቀ፣ምድር ሰፊ ከመሆኗም ጋር ጠበበችው....አሚር ዑስማን ሸይኹን ተቀበሏቸው፤ በግዛቱ የፈለጉበት ቦታ መንቀሳቀስ እንደሚችሉ አስረግጦ አሳውቋቸው። የደርዒየህ ነዋሪዎችና ህዝቦች የሸይኹን የተውሂድ ተልእኮ ተረዱ። የደርዒያው አስተዳዳሪ አሚር ሙሐመድ ብን ሰዑድ፣ ሸይኹ ወደ ግዛቱ ስለገቡ በእጅጉን ተደሰተ። አስተዳዳሪው ቀጥታ ሸይኹ የሚገኝበት ድረስ በመሄድ ጉብኝት አድርጓል። በሸይኹ የተውሒድ ጥሪም ተደስቷል። ከሸይኹም ጋር የሃሳብ ልውውጥ አድርጓል። አሚር ሙሐመድ ብን ሰዑድ ለሸይኹ ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው ቃል ገባላቸው። ሸይኹም ለአሚሩ ዱዓ አደረጉለት። ሸይኹ ይህንን ወርቃማ የሆነውን አጋጣሚ በመጠቀም፣አያሌ የሆኑ ህዝቦችን ማስተማር ጀመሩ። የደርዒየህ እና አካባቢዋ በተውሂድ ተናወጠች፤የተውሂድ ሰንደቅዓላማ መውለብለብ ጀመረ... ምን ይሄ ብቻ የደርዒያው ዋና አስተዳዳሪ አሚር ሙሐመድ እራሱን እና ቤተሰቦቹን ይዞ እንደተማሪ ሆኖ በመቅረብ፣ ከህዝቡ ጋር በመታደም የሸይኹን ትምህርቶችን መከታተል ጀመረ። ይህ ዜና በተለያዩ አከባቢዎች ተሰራጨ። ዜናውን የሰሙ ሰዎችም ከበረከቱ ለመቋደስ፣እውቀት ለመቅሰም ወደ ደርዒየህ መሰደድ ጀመሩ። ደርዒየህ የተውሂድ ማዕከል ሆነች። ይህ በንዲህ እንዳለ፣የሸይኹ ጠላቶች በሸይኹ ላይ የተለያዩ ቅጥፈቶችን መንዛት ጀመሩ። ምን ይሄ ብቻ?! ጠንቋይ፣ ድግምተኛ፣ ሙናፊቅ (ዚንዲቅ)...በመሳሰሉ ቃላቶች በሸይኹ ላይ መንዛት ጀመሩ። በተለያዩ የውሸት ቅጥፈቶች ሸይኹን ለማሸማቀቅና ከዳዕዋው ለማሰናከል በሚክሩም፣ሙከራቸው ሳይሳካ ቀርቷል። ሸይኹ የተቺ ተቺዎች ሴራ ሳይበግራቸው ተልዕኮውን ቀጠሉ። በል እንዳውም ተቃራኒ ከሆኑ አካላቶች ጋር ጨዋነት በተሞላበት ስልት ተከራክረዋል። ከዚህም በተጨማሪ፣ከተለያዩ ከአረብ ደሴት (Arabian peninsula) የመጡ የተለያዩ ልዑካን ቡድኖችን ትክክለኛው የተውሒድ ጥሪ ካደረጉላቸው በኃላ፣ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ህዝባቸውን ወደ ተውሒድ እንዲጠሩ አጥበቀው መክረዋል። ሸይኹ በዚህም ብቻ አላቆሙም ለአረብ ደሴት መሪዎችና ሊቃውንቶች ደብዳቤዎችነ ፃፉ። የደብዳቤው ዋና መልእክት ሽርክን እንዲሁም ኢስላም የማያውቀው ባዕድ የሆኑ አምልኮዎችን ህዝባቸውን እንዲታደጉ ነበር። ሸይኹ ደብዳቤዎችን የፃፉት ለነጅድ፣ ሪያድ፣ኸርጅ፣ ቀሲም፣ሀዬል፣ወሽም፣ ሱደይር፣አህሳ፣ መካ፣ መዲና፣ የመን...ለመሳሰሉት ሀገራቶች ፅፈው ነበር። ልብ ይበሉ! ደብዳቤው የተፃፈው በሀገሩ ለሚገኙ አስተዳደር እና ዑለማች ነው። ሸይኹ አሁንም በዚህ አላበቁም፤ከአረብ ደሴት ውጭ ለሆኑ ሀገራትም ደብዳቤዎችን ፅፈዋል፤ለምሳሌ፡ ለነ ሶሪያ፣ ኢራቅ፣ሕንድ...ለመሳሰሉት ሃገራት በደብዳቤ የዳዕዋ ጥሪ አቅርበዋል። ሸይኹ ቁርኣንና ሱንናን አብራርተዋል። ምስጋና ለአላህ የተገባ ይሁንና ዳዕዋቸው ግብ መቷል። የሸይኹን ዳዕዋ ከተቀበሉ ሀገራቶች መካከል፡ ሕንድ፣ኢንዶኔዥያ፣አፍጋኒስታን፣አፍሪካ፣ሞሮኮ፣ግብፅ፣ሶሪያ...የመሳሰሉ ሀገራቶች የሸይኹን ዳዕዋ በመቀበል ትልቅ ተፅዕኖ አድሮባቸዋል። ይህም ብቻ ሳይሆ ከሸይኹ ጎንም ጭምር ተሰልፈዋል። ሸይኹ በሒጅራው ቀመር አቆጣጢ ከ"1158" እስከ "1206" ባሉት ጊዜያት ውስጥ ትልቅ የሆነ ተግል በማድረጋቸው አመክንዮ፣ በነጅድ ሙሉበሙሉ በሚባል ደረጃ አላህ ሸይኹን ድል አጎናፀፋቸው። ሰዎች ዶሪህን፣ ቀብርን፣ እንጨትን፣ዛፍን...ማምለክ ተው። ጭፍን ተከታይነት ሚባል ነገር ጠፋ። ይህ ባህል ነው፣የአባቴ መንገድ ነው፣የአያቴ መንገድ ነው...ከማለት ሰዎች ተወገዱ። ጥርት ወዳለው እስልምና ገቡ። አላሁ አክበር ዲን እንደገና ሕያው ሆነ። ቁርኣንና ሱንና በሰዎች ላየ ተንፀባረቀ። በመልካም ማዘዝ ከመጥፎ መከልከል ተግባራዊ ስራ ሆኖ ቀጠለ፤ መስጂዶች ውስ ሰዎች ሞልተው መስገድ ጀመሩ። በሀገሪቷ ሰላምና መረጋጋት ሰፈነ። ገጠሬዎችም ከተሜዎች...በሰላም መኖር ጀመሩ። የተውሒድ ሰንደቅዓላማ ተውለበለበ። ከሸይኹ እወቀትን የቀሰሙ አካላቶች በመላው ዓረቢያ ደሴት የተውሒድ ተልዕኮን ይዘው ተሰሬጩ። ሸይኹ በሕይወት ካለፉ በኃላም ልጆቻቸው እና ተማሪዎቻቸው ዳዕዋውን በአላህ ፍቃድ ማስቀጠል ችለዋል። ከልጆቻቸው መካካል ዳዕዋውን ካስቀጠሉ እንደነ፡ ሸይኽ ኢማም ዐብዱሏህ ብን ሙሐመድ፣ ሸይኽ ሑሰይን ብን ሙሐመድ፣ ሸይኽ ዐሊይ ብን ሙሐመድ፣ሸይኽ ኢብራሂም ብን ሙሐመድ....ይገኙበታል። ከሸይኹ ከልጅ ልጆቻቸው መካከል ደግሞ፣ሸይኽ ዐብዱር-ረሕማን ብን ሐሰን፣ሸይኽ ዐሊይ ብን ሑሰይን፣ሸይኽ ሱለይማን ብን ዐብዱሏህ... ይገኙበታል። ከተማሪዎቻቸው መካከል ደግሞ፡ እንደነ ሸይኽ ሐምድ ብን ናሲር...የመሳሰሉ ይገኙበታል። ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) ለዚህ ኡማ ትልቅ የሆነን አሻራ ጥለው አልፈዋል። ለዚህም ነው ሰዎች በሺርክና በተለያዩ ባዕድ በሆኑ አምልኮ ተጨማልቀው ሳለ፣ በአላህ ፍቃድ ሸይኹ ትግል አድርገው፣የአንበሳውን ድርሻ ተጫውተው ነው ከዚች ዓለም ያለፉት።
Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.