4 088
Suscriptores
Sin datos24 horas
-27 días
-2730 días
Archivo de publicaciones
4 088
ለቸሩ እግዚአብሔር ምን ይሳነዋል? በቀን ላይ ቀን እየጨመረ፥ በዓመት ላይ ዓመትን እያቀዳጀ፥ ይኸው 2016ን አምና ልንል ዐዲስ ዓመት ላይ አደረሰን።
ሃሌሉያ! የአምላካችን ስም የተመሰገነ ይኹን። አስጀምሮ እዚህ ላደረሰን፥ ጸሎታችንን ለሰማን ኤልሮኢ ክብር ይሁንለት። አውጥቶ ላስገባን፥ በሕይወት ላቆየን አዶናይ፥ አምልኮ ይድረሰው። ፀሃይን ላወጣ ጨረቃን ላልከለከለን፥ በወቅቱ ዝናብን ለሰጠን እግዚአብሔር ውዳሴ ይኹንለት። ጠፋን ባልን ጊዜ ላልተወን፥ ባለፍንበት አብሮን ለነበረ ጌታ ስግደት ይብዛለት። ከህመማችን ጋር ለታመመ፥ በለቅሶአችን ለታደመ ያሕዌ እልልታ ይጨመርለት። በማዕበል ውስጥ አብሮን ለተራመደው፥ በእሳት ውስጥ አብሮን ላለፈው ኤልሻዳይ በረከት ይኹንለት።
ዓመትን በዓመት ለሚተካ፥ ትናንትን አሳልፎ ዛሬን ለሚያሳይ ልዑል ክብር ይኹን። መጪውን ዓመት በእጆቹ ለያዘ፥ ለታማኙ ጌታ ክብር ይሁን። በሚገጥመን ነገር ሁሉ እረኛችን ለሚኾን ጌታ ክብር ይኹን። ቀናችንን፣ ሳምንታችንን፣ ወርና ዓመታችንን ለሚወስን ንጉሥ ክብር ይኹን። ቀኙን ለሚሰጠን፣ ደስ ለሚያሰኘን፣ ደግሞም ለሚባርከን አምላክ ክብር ይሁን።
ሃሌሉያ!
"በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።" መዝ 65:11
እንኳን ለ2017 ዓ.ም በሰላም አደረሰን።
መልካም ዓውደ ዓመት!
@kaluproject
4 088
"ሥጋን ግን አዘጋጀህልኝ"
ዕብ 10:5
አጭር ማብራሪያ
- "ስለዚህ ወደ ዓለም ሲገባ" ማለት ቃል ስጋ ሲሆን፣ ትስብእት (incarnation)፣ አምላክ ስጋን ገንዘቡ ሲያደርግ ማለት ነው::
- "መሥዋዕትንና መባን አልወደድህም፤" ማለት ኃጢአት አስታዋሾችን አልወደድህም ማለት ነው:: በቁ.3 ላይ "ነገር ግን በዚያ መሥዋዕት በየዓመቱ የኃጢአት መታሰቢያ አለ፤" በማለት የፍየሎችና የጥጃዎች መሥዋዕት በየአመቱ ኃጢአታቸውን ያስታውሷቸዋል እንጂ ከኃጢአት አንጽቶ ፍጹማን ሊያደርጋቸው እንዳልቻለ ይናገራል::
- "ሥጋን ግን አዘጋጀህልኝ፤" ማለት እግዚአብሔር በቀድሞዎቹ መሥዋዕቶች ደስ ስላተሰኘ እኔን መሥዋዕት እንድሆን አዘጋጀኝ/አደረገ ማለት:: በየአመቱ በሚሠዉት ደስ ስላላለው አንዴ ለሁሌ የሚሆን መሥዋዕት አድርጎ እኔን አዘጋጀ እያለ ነው (ኢየሱስ)::
⭕️ማጠቃለያ
እግዚአብሔር የቀድሞውን የመሥዋዕት ስርአት በመሻር አንዴ ለሁሌ የሆነ መሥዋዕት በመስቀል ላይ አቆመ(አዋለ):: ስለዚህ የተዘጋጀው ስጋ (እግዚአብሔር ያዘጋጀው) አንዴ ለሁሌ የሆነ፣ ኃጢያት የሚያስታውስ ሳይሆን ኃጢአትን የሚያስወግድ ነው:: እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ!
@kaluproject
4 088
"በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፥
ስምህ ይቀደስ፤" ማቴ 6:9-10
አጭር ማብራሪያ
- "በሰማያት የምትኖር" (ምጡቅ፣ ኹሉን ቻይ፣ ገናና፣ ከፍ ያልህ)፤
- "አባታችን" (ቅሩብ፣ ቤታችን ያለህ)፤
- በአጭሩ እንደ አምላክ የምትፈራ፥ እንደ አባት የምትከበር እግዚአብሔር "ሆይ፤"
- "ስምህ ይቀደስ" (በመካከላችን የአንተ ስም ይለይ፤ ከእኛ ጋር እንደኾንህ በኹሉ ዘንድ ይታወቅ፤ ስምህ ይቀድስና ጠላቶቻችን ይፍሩህ፤ አንተ ብቻ ታወቅ፤ የሚሰራው ስምህ በመካከላችን ይተከል (ይቁም))
✍️መጠቅለያ
ስትጸልዩ ሁሉን ማድረግ እንደሚችል አምላክ አምናችሁት እና እንደ አባት አክብራችሁት ጸልዩ:: ደግሞም የመጀመሪያ ጸሎታችሁ እግዚአብሔር በመካከላችሁ እንዲቀደስ እና መኖሩ እንዲታወቅ መጮህ ይኹን እያለ ነው::
አሜን🙏🏽
@kaluproject
4 088
እግዚአብሔር እረኛዬ ነው!
መዝሙር 23
1 እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም።
2 በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል።
3 ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ።
4 በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል።
5 በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው።
6 ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።
@kaluproject
4 088
ሰላም ቤተሰቦች
ከዚህ ቀደም "ስያሜን" በተመለከተ መጠይቅ እንድትሞሉ አድርጌ ነበር:: kingdom of heaven የተሰኘው ስያሜ በአብላጫ ድምጽ የተመረጠ ቢሆንም ስያሜው በአብያተ ክርስቲያናት ህጋውዊ እውቅና ያለው በመሆኑ መጠቀም እንደማልችል ተነግሮኛል:: ስለሆነም ወደ ቀድሞ ስያሜያችን kalu project ሎጎውን አሻሽለን ለመመለስ ተገደናል:: ይህንን ምክንያት በማድረግ የFacebook , እና YouTube ቻናሎቻችንንም በዚሁ ስያሜ የምንቀይር ይሆናል::
ብሩካን ናችሁ!
4 088
"እግዚአብሔር ሞቷል፤
እንደሞተም ቀርቷል፤
እኛም ገድለነዋል"
ብሎ የተፈላሰፈው
ኒቼ የተባለ ሰው
አብዶ ነው የሞተው
ግጥም በ'ሐንኤል
4 088
ጥቂት የማይባሉ ሰዎች የቻናሉ ስም ከ"Kingdom of Heaven" ይልቅ "ቃሉ Project" የሚለው ይሻላል እያሉ ይገኛሉ:: እግዚአብሔር ቢፈቅድ በቅርቡ website ለማሰራት እያሰብኩ ስለሆነ የትኛውን ስያሜ ብጠቀም የተሻለ እንደሆነ በምርጫችሁ አሳውቁኝ:: ብዙ ድምጽ ያገኘው የTikTok, የtelegram እና የwebsite ቋሚ ስያሜ ሆኖ ይጸናል::
4 088
አዝ፦ በእምነት ፡ ድል ፡ እየነሱ ፡ ያለፉትን
የቀደሙትን ፡ እያየን ፡ ከፊታችን
ልንቆም ፡ ያስፈልገናል ፡ ለጌታችን
የሕይወት ፡ ምርጫችን
እርሱ ፡ ነውና ፡ ዋስትናችን (፪x)
ከሁሉ ፡ የሚበልጠውን ፡ ተመልክተው
ከየምድሩ ፡ ጉድጓድ ፡ ተቅበዝብዘው
ነፍስን ፡ ከሚዋጋ ፡ ምኞት ፡ ርቀው
ወንዙን ፡ ተሻገሩ ፡ አሸንፈው (፫x)
አዝ፦ በእምነት ፡ ድል ፡ እየነሱ ፡ ያለፉትን
የቀደሙትን ፡ እያየን ፡ ከፊታችን
ልንቆም ፡ ያስፈልገናል ፡ ለጌታችን
የሕይወት ፡ ምርጫችን
እርሱ ፡ ነውና ፡ ዋስትናችን (፪x)
ቅን ፡ ከምትመስል ፡ ሰፊ ፡ መንገድ
ወጥተን ፡ በጠባቡ ፡ ስንሰደድ
በዚህ ፡ ጐዳና ፡ ላይ ፡ ሕይወት ፡ አለ
ቆርጦ ፡ ለሚከተል ፡ የታደለ (፫x)
አዝ፦ በእምነት ፡ ድል ፡ እየነሱ ፡ ያለፉትን
የቀደሙትን ፡ እያየን ፡ ከፊታችን
ልንቆም ፡ ያስፈልገናል ፡ ለጌታችን
የሕይወት ፡ ምርጫችን
እርሱ ፡ ነውና ፡ ዋስትናችን (፪x)
ባለ ፡ ፀጋ ፡ ሲሆን ፡ ደህይቶልን
ባለ ፡ ማዕረግ ፡ ሲሆን ፡ ተዋርዶልን
እውነተኛውን ፡ ፍቅር ፡ ገለጸልን
እኛም ፡ በእርሱ ፡ መንገድ ፡ እንሄዳለን (፫x)
አዝ፦ በእምነት ፡ ድል ፡ እየነሱ ፡ ያለፉትን
የቀደሙትን ፡ እያየን ፡ ከፊታችን
ልንቆም ፡ ያስፈልገናል ፡ ለጌታችን
የሕይወት ፡ ምርጫችን
እርሱ ፡ ነውና ፡ ዋስትናችን (፪x)
#ተስፋዬ_ጋቢሶ
@mengiste_semay
