cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

✞✟ ኦርቶዶክሳዉያን ✞✟

እንኳን ወደ ቻናላችን በሰላም መጣቹ ይህ ቻናል የተከፈተው ለኦርቶዶክሳውያን እና ማወቅ ለሚፈልግ ለማንኛውም ሰው ነው ✞መዝሙር ✟ግጥም ✞ኦርቶዶክሳዊ ፎቶ ያገኙበታል

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
522
Suscriptores
Sin datos24 horas
-17 días
-1530 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

🕊 ✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞ †  እንኳን አደረሳችሁ  † [ †  ግንቦት ፲፱ [ 19 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] †  🕊  አባ ዓቢየ እግዚእ  🕊  † ጐንደር ከተማ ነዋሪ ከሆኑ: ወይም ከተማዋን የሚያውቁዋት ከሆነ አንድ ጥያቄ ልጠይቅዎ::[እንደ ወትሮው ሁሉ] ከተማዋ ውስጥ ጅብና እባብን የመሠሉ አራዊት ነዋሪውን ሲገድሉ: ወይም ሲያቆስሉ ተመልክተው: ካልሆነም በታሪክ ሰምተው ያውቃሉ? መልስዎ "በጭራሽ አላውቅም" እንደሚሆን እገምታለሁ:: [ምክንያቱም ሆኖ አያውቅማ!] ነገሬን እንዲረዱኝ ሌሎች የሃገራችን ዋና ዋና ከተሞችን ልብ ይበሉልኝ:: እንኳን በሌሊት በቀንም አራዊቱ አይጠፉባቸውም:: "ታዲያ ጐንደር ከተማ ውስጥ ጅብ የማይገባው: እባብና ጊንጥ ሰው የማይገድለው ግን ለምን?" ካሉ በጻድቁ በአባ ዓቢየ እግዚእ ቃል ኪዳን ምክንያት ነው:: [ሁሉም የሃገራችን ከተሞች የተባረኩ መሆናቸውን ሳንዘነጋ ማለት ነው] ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ :- አባ ዓቢየ እግዚእ የተወለዱት በ፲፬ [14]ኛው መቶ ክ/ዘመን ትግራይ ተንቤን [መረታ] ውስጥ ነው:: የተባረኩ ወላጆቻቸው ያፍቅረነ እግዚእና ጽርሐ ቅድሳት ይባላሉ:: አጥምቀው 'ዓቢየ እግዚእ' ሲሉ ስም ያወጡላቸው የወቅቱ ዻዻስ ሰላማ መተርጉመ መጻሕፍት ናቸው:: ትርጉሙም "በጌታ ዘንድ ታላቅ ሰው" ማለት ነው:: ዓቢየ እግዚእ በሕጻንነታቸው ሌሊት ሌሊት ባሕር ውስጥ ሰጥመው ሲጸልዩ አድረው ቀን ቀን እየተማሩ ብሉይ ከሐዲስ ጠነቀቁ:: ገና በወጣትነታቸው ወደ ታላቁ መነኮስ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ደብረ በንኮል ሔደው መንኩሰዋል:: በገዳሙ በጾም: በጸሎትና በስግደት ተወስነው ከኖሩ በኋላ ወደ ዋልድባ ሔደው የተሰወረች ቤተ ክርስቲያን አግኝተዋል:: በጊዜው በ፵ [40] ቀን አንዲት ቅጠል ብቻ ለቁመተ ሥጋ ይበሉ ነበር:: ከዚያም ወደ ሃገራቸው ተንቤን ተመልሰው ዛሬም ድረስ ድንቅ ሆኖ የሚታየውን ገዳም መሥርተው ብዙ መናንያንን አፍርተዋል:: ዓቢየ እግዚእ ገዳማዊና ጻድቅ ብቻ ሳይሆን ሐዋርያዊ አባትም ነበሩ:: ከትግራይ እስከ ደንቢያ ደግሞ ሃገረ ስብከታቸው ነው:: አንድ ጊዜ ደቀ መዛሙርትን አስከትለው ለስብከት ሲንቀሳቀሱ ተከዜ ወንዝ አካባቢ ደረሱ:: ቀኑ ነሐሴ ፲ [10] ነውና ተከዜ እስከ ገደፉ ሞልቶ ለ፫ [3] ቀናት ባለመጉደሉ ከ፩ ሺህ [1,000] በላይ ሰዎች ሲያለቅሱ ደረሱ:: ጻድቁ ባካባቢው የነበሩት ኢ- አማንያን [አሕዛብ] ቢሆኑም ራርተዋልና "አምላከ ሙሴ" ብለው ጸልየው ወደ ጥልቁ ውስጥ ገቡ:: ቅዱስ ሚካኤል አብሯቸው ነበርና ተከዜ ግራና ቀኝ ተከፍሎ መሃሉ የብስ ሆነ:: ይሕን ድንቅ ያዩ ከ፩ ሺህ [1,000] በላይ አሕዛብም አምነው በጻድቁ እጅ ተጠምቀዋል:: ይሕም ዘወትር ነሐሴ ፲ [10] ቀን በቤተ ክርስቲያናቸው [ጐንደር] ይከበራል:: ከዚያም እያስተማሩ ጐንደር ደረሱ:: ያኔ ጐንደር በቀሃና አንገረብ ወንዞች የታጠረች አንዲት መንደር ነበረች:: ጻድቁ ቀን ቀን እየሰበኩ ማታ ዛሬ ቤተ ክርስቲያናቸው የታነጸበት ሥፍራ ላይ ሲጸልዩ ያድሩ ነበር:: በዚያ ዘመን ጐንደር ውስጥ ጅብ: እባብና መሠል አራዊት ገብተው ሕዝቡን ጨረሱት:: ይሕንን የተመለከቱት አባ ዓቢየ እግዚእ ወደ እግዚአብሔር አለቀሱ:: በፍጹም ልባቸውም ስለ ሕዝቡ ለመኑ:: የለመኑትን የማይነሳ ጌታ ወደ ጻድቁ ቀርቦ "በስምሕ የተማጸኑ: በቃል ኪዳንህ ያመኑ: በምድር አራዊት አይሠለጥኑባቸውም:: በሰማይም እሳትን አያዩም:: ጐንደርንም አራዊት ገብተው ሰውን አይጐዱም::" ብሏቸው አርጓል:: ጻድቁም የወንጌል አገልግሎታቸውን ፈጽመው ወደ ገዳማቸው ተንቤን ተመልሰዋል:: ይሔው እኛ ምን ብንከፋ: ጻድቁንም ብንረሳቸው እግዚአብሔር ግን ዛሬም በጻድቁ ምልጃ ከተማዋን ጠብቆ ይኖራል:: ነገን ደግሞ እርሱ ያውቃል:: ዛሬ ቤተ ክርስቲያኑ የታነጸበት ቦታ [ጎንደር ቀበሌ 09 ኪዳነ ምሕረት] ጻድቁ የጸለዩበት ቦታ ነው:: እንኳን በወርሃዊ በዓላቸው በ፲፱ [19] ይቅርና በዓመታዊ በዓላቸው [ግንቦት ፲፱ [19] ለንግስ የሚመጣው ሰው ቁጥር ያስተዛዝባል:: አባ ዓቢየ እግዚእ በገዳማቸው ተንቤን ለብዙ ዘመናት በቅድስና ኑረው: ፫ [3] ሙታንን አስነስተው: ብዙ ድውያንን ፈውሰው: ብሔረ ብጹዓንን ጎብኝተው: የድኅነት ቃል ኪዳንም ተቀብለው: በ፻፵ [140] ዓመታቸው ግንቦት ፲፱ [19] ቀን አርፈዋል:: የጻድቁ ክብር ለሁሉ ነውና እባካችሁ እናስባቸው:: "ተአምሪሁ ለጻድቅ አቡነ ዓቢየ እግዚእ - - - ጸሎቱ ወበረከቱ የሃሉ ምስለ ኩልነ ሕዝበ ክርስቲያን ለዓለመ ዓለም:: አሜን::" " ከበዙ ተአምራቱ አንዱን " ጻድቁ አባ ዓቢየ እግዚእ በገዳማቸው ተንቤን [መረታ] ሳሉ አንዲት መበለት መጥታ "አባቴ! የምጠጣውን ጸበል ባርከህ ስጠኝ?" አለቻቸው:: ጻድቁም በውሃው ላይ ጸሎትን አድርሰው : በመስቀላቸው ባርከው ሰጧት:: ወደ ባልንጀራዋ ስትደርስ ግን ሐሳቧን ቀየረችና "ልጠጣው" ብላ የተቀበለችውን ማይ [ጸበል] ልትጠመቅበት [ልትጸበልበት] ወሰነች:: ባልንጀራዋንም "በላዬ ላይ አፍሺልኝ" ስትል አዘዘቻት:: ባልንጀራዋም "እሺ" ብላ ልታፈስላት [ልትጸብላት] በፋጋ [ግማሽ ቅል] ያለውን ጸበል አነሳች:: ልታፈሰው ስትዘቀዝቀው ግን ከሆነው ነገር የተነሳ ፪ [2] ቱም ደነገጡ:: ጸበሉ የረጋ ደም ወደ መሆን በቅጽበት ተለውጧልና:: ፍጹም ፍርሃት የወደቀባቸው ሴቶቹ እየተሯሯጡ ወደ አባ ዓቢየ እግዚእ በዓት ደረሱ:: ከውጭ ሆነውም "አባ! አባ! የሰጠኸን ጸበልኮ የረጋ ደም ሆነ" አሏቸው:: ጻድቁም እንዳላዋቂ "ምን አጠፋችሁ?" ሲሉ ጠየቁ:: "አባታችን! ምንም አላጠፋንም:: ብቻ አፍሺልኝ ብየ ስሰጣት እንዲህ ሆነ" ስትል አንዷ መለሰች:: ጻድቁ ግን በየውሃት "ልጆቼ! ሁሌም : 'ምንም አላጠፋንም' አይባልም:: ሰው ሆኖ የማይበድል የለምና:: + . . . አንቺም ልጄ ! እኔን ያልሺኝ 'የምጠጣው ጸበል ስጠኝ' ነበር:: ግን ልትጸበይበት ወደድሽ:: ስሕተትሽ ከዚህ ይጀምራል:: [የቅዳሴ ጸበል ለመጸበል አይሆንምና] ¤በዚያ ላይ "አልቦ ዓቢይ ኃጢአት ከመ ወልጦ ቃል . . . ከውሸት በላይ ከባድ ኃጢአት የለም::" [ዮሐ.፰፥፵፬] + . . . በተጨማሪ ደግሞ ያለ ስልጣኗ እህትሽን 'አጥምቂኝ' አልሻት:: ስለነዚህ ነገሮች ጸበሉ ተለውጦባቹሃል" ብለው ወደ ጸበሉ በመስቀል አማተቡ:: "እፍ" ሲሉትም የረጋ ደም የነበረው ማይ ወደ ጸበልነቱ ተመለሰ:: ይህንን ያዩ ሴቶቹ በግንባራቸው ተደፍተው ለጻድቁ ሰገዱ:: ጸሎቱ ወበረከቱ የሃሉ ምስለ ኩልነ ሕዝበ ክርስቲያን ለዓለመ ዓለም:: አሜን::
Mostrar todo...
አምላካችን በወዳጆቹ ምልጃ ሃገራችንን ከክፉው ሁሉ ይሠውርልን:: [  †  ግንቦት ፲፱ [ 19 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ] ፩. አባ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ [ ኢትዮዽያዊ ] ፪. አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም [ የ፲፪ [ 12 ]ቱ ሐዋርያት መቃብር ከጌታ የተገለጠላቸው ኢትዮዽያዊ ] ፫. አቡነ ብስጣውሮስ ዘሐይቅ እስጢፋኖስ [ ኢትዮዽያዊ ] ፬. ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት ታላቁ [ ፯ [7 ] ጊዜ ሙቶ የተነሳ ] ፭. "805,007" ሰማዕታት [ በአንድ ቀን ብቻ የተገደሉ ] ፮. አባ ይስሐቅ ገዳማዊ [   †  ወርኃዊ በዓላት    ] ፩ ፡ ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት ፪ ፡ ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት ፫ ፡ ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ ፬ ፡ አባ ስነ ኢየሱስ ጻድቅ " በተኩላና በእባብ ላይ ትጫማለህ:: አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ:: በእኔ ተማምኗልና አስጥለዋለሁ:: ስሜንም አውቁዋልና እጋርደዋለሁ:: ይጠራኛል እመልስለትማለሁ:: በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋር እሆናለሁ:: አድነዋለሁ: አከብረውማለሁ:: ረጅም እድሜን አጠግበዋለሁ:: ማዳኔንም አሳየዋለሁ:: " [መዝ.፺፥፲፫] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
                       †                          [  🕊  ድምፀ ተዋሕዶ   🕊  ]   🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒                [  ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ።  ] [   ሳምንታዊ መርሐ-ግብር   ] 🕊                            ❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ፤ ነፍስን ይመልሳል ፤ የእግዚአብሔር ምስክር የታመነ ነው ፤ ሕፃናትን ጠቢባን ያደርጋል። የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው ፥ ልብንም ደስ ያሰኛል ፤ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው ፥ ዓይንንም ያበራል። ❞ [ መዝ . ፲፱ ፥ ፯  ] ▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬ [ ❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ! ❞  ] [ ክፍል - ፪ - ]           💖   ድንቅ ትምህርት  💖 [ በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ] ❝ የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]          †              †               † ▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬                        👇
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
                        †                         🕊  💖     ይ ከ ታ ተ ሉ !     💖  🕊 ከነገ ምሽት ጀምሮ በፍኖተ ሕይወት መርሐግብር [ ያ ለ እ ም ነ ት ! ]      💖    ድንቅ ትምህርት   💖 🕊 በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ  🕊 ▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሊሰማው የሚገባው እጅግ ድንቅ ትምህርት በአነስተኛ Mb መቅረብ ስለሚጀምር ሌሎች ኦርቶዶክሳውያንን Add በማድረግ ትከታተሉ ዘንድ እንጋብዛለን !  💞 †                       †                         † 💖                    🕊                     💖
Mostrar todo...
▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬ [ ከመንፈሳዊ መጻሕፍት ቅኝት ] 🔔 [ የተሀድሶ እንቁራሪት ! ] ሰውየው አንድ ትልቅና ጎድጓዳ ዕቃ አምጥቶ በውኃ ከሞላው በኋላ ያን ውሃ ከእሳት ማንደጃ ላይ ጥዶ እሳቱ በኃይል ለቀቀውና ውኃውም በፍጥነት ፈላ። ትንሽ ቆይቶም አንዲት እንቁራሪት አመጣ እዚያ የፈላ ውኃ ውስጥ ከተታት እንቁራሪቷ ግን ተስፈጥራ ወጣችና ነፍሷን አተረፈች ። በእንቁራሪቷ መትረፍ የተበሳጨው ሰውየው በሌላ ጊዜ በእዚያው ዕቃ ውኃ ሞላና ከማንደጃው ላይ ጥዶ ሲያበቃ እሳቱ ከማቀጣጠሉ በፊት ያችኑ እንቁራሪት ይዞ በቀዝቃዛ ውሃ ውስጥ ጨመራት እንቁራሪቷ እንደ በፊቱ ተስፈንጥራ አልወጣችም ይልቁንም ውኃው ቀዝቃዛ በመሆኑ ተዝናንታ ትዋኝ ጀመረ። ሰውየው እንቁራሪቷን ሳይረብሽ በጥንቃቄ እሳቱ ለኮሰና ቀስ በቀስ መጠኑን እየጨመረ ውሃውን ያፈላው ጀመረ ። ከምድጃው ስር እሳት እየነደደ መሆኑን ያልተረዳችው እንቁራሪት ውኃው ለብ ባለ ቁጥር ደስታዋ እየጨመረ ሄደ ። ሰውየው የእሳቱን ኃይል ቀስ በቀስ እየጨመረ ሲመጣ ውሃው ተፍለቀለቀ የውኃውን ለብታ እና ሞቅ ማለት ያላነቃት ይልቁንም ያስፈነደቃት እንቁራሪት ሳታውቀው ፍልቅልቁ ውሃ አንፍሮ ጣላት። 🔴 በዚህ ዘመን ከቅርብ አመታት ወዲህ በቤተ-ክርስቲያናችን አውደ ምህረቶች በተለይም በጣት የሚቆጠሩትና ከቤተ ክርስቲያን ሕግና ስርአት ይልቅ በሕገ ወጥ መንገድ ለሚሰበሰበው ገንዘብ ልባቸውን በሰጡ ኃላፊዎች ምክንያት በሚዘጋጁ ጉባዔያት የሚታየው ሁኔታ ለእኛ ለቤተ-ክርስቲያን ልጆች እንቁራሪቷ ሳታውቀው የነፈረችበትን የተፍለቀለቀ ውሃ ይመስላል። ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሾልከው በገቡ የተሃድሶ መናፍቃን የማዘናጊያ ስብከት በዝንጋዔ ምድጃ ተጥለን በኑፋቄ ነፍረን እንዳንገኝ ልንባንንና ልንጠነቀቅ ይገባናል ። ሁሉ ነገር እንቁራሪቷን በመጀመሪያ እንዳጋጠማት አፍጦ ሳይሆን እንደ ሁለተኛው ጊዜ በማዘናጋት ነው እየሆነ ያለው። እናም የተዋሕዶ ልጆች እንንቃ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንጦስ ምዕመናን በላከው መልዕክቱ እንዲህ ይላል ፦ "ንቁ በሀይማኖት ቁሙ ጎልምሱ ጠንክሩ።" [፩ኛ ቆር.፲፮፥፲፫] ይላልና እንጠንቀቅ ሁላችን። [ ምጥን ቅመም ከተሰኘችው የዲ/ን ምትኩ አበራ መጽሐፍ የተወሰደ ] ይቆየን ! †                       †                         † 💖                    🕊                     💖
Mostrar todo...