cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Dn Wondalem Alemayehu ዲ/ን ወንድዓለም አለማየሁ

እውቀት እንገበይ በሃይማኖት እንጽና subscribe&share እያረጋችሁ https://www.youtube.com/@bonny1221 ይህ የተለግራም ግሩፕ ሊንክ ነው👇👇👇 https://t.me/Dnwonde channel https://t.me/orthodoxchallenge https://www.facebook.com/DeaconWondalemAlemayehu

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
272
Suscriptores
Sin datos24 horas
+17 días
+1630 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አኃዱ አምላክ አሜን። ቅድስት ሥላሴ የሁሉ ፈጣሪ የዓለም ገዢ አምላካችን እግዚአብሔር ለስሙ ክብር ይግባውና በሐምሌ ፯ ቀን ወደ ጻድቁ አብርሃም ቤት በመግባት በአንድነትና በሦስትነት ክብሩ ተገለጠለት፡፡ በዚህች በተከበረችም ቀን አብርሃም በደጃፉ ሆኖ ዓይኖቹን አንሥቶ ሲመለከት ሦስት አረጋውያንን አየ፤ ሮጦ ሄዶም ተቀበላቸው፡፡ ‹‹ውኃ እናምጣላችሁ፤ እግራችሁን እንጠባችሁ፡፡ ከዛፉም ሥር ዕረፉ፤ እንጀራም እናምጣላችሁና ብሉ፤ ከዚያም በባሪያችሁ ዘንድ ከአረፋችሁ በኋላ፥ ወደ አሰባችሁት ትሄዳላችሁ›› አላቸው፡፡ ‹‹እንደምታየን ሽማግሌዎች ነን፤ የመጣነው ደግሞ ከሩቅ ነው፡፡ ስለዚህ አዝለህ ወደ ድንኳንህ አስገባን›› አሉት፡፡ አንደኛውን አዝሎ ወደ ድንኳን ሲያስገባ ሁለቱ በግብር አምላካዊ ገብተው ተገኙ፡፡ አብርሃምም ነገሩ እየረቀቀበት ሲሄድ በጓዳ ለነበረችው ለሚስቱ ሣራ ‹‹ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ ለውሺ፤ እንጎቻም አድርጊ›› አላት፡፡ ሚስቱ ሣራም እንዳዘዛት አድርጋ ጋግራ አቀረበች፤ እርሱም ቤት ለነበረ አንድ ብላቴና ወይፈኑን አርዶ አወራርዶ እንዲያመጣለት ካዘዘው በኋላ ከወተትና ማር ጋር አብሮ አቀረበላቸው፡፡ እነርሱም አብርሃምን ደስ ለማሰኘት በሉ፤ መበለታቸውም እሳት ቅቤ በላ እንደ ማለት ነው፤ በግብር አምላካዊ ነውና አይመረመረም፡፡ ከዚያም የታረደውና የተወራረደው ወይፈንም ተነሥቶ በድንኳኑ ደጃፍ ‹‹ስብሐት ለአብ፣ ስብሐት ለወልድ፣ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ›› ብሎ ሥላሴን አመሰገነ፡፡  አብርሃም ደነገጠ፤ ‹‹እንግዳ ከመጣልህ በትሑት ሰብእና በቅን ልቡና ሆነህ ተቀበል፤ እንግዳ ካልመጣ ጾምህን አትደር፤›› አሉት፤ ከዚያም ስለ ይስሐቅ  አበሠሩት፡፡ (ዘፍ. ፲፰፥፩-፰፣አንድምታ ትርጓሜ ምዕራፍ ፲፰) ጻድቁ አባታችን አብርሃም አምላኩን ለማወቅ ሽቶ በእምነትና በሃይማኖት ጽናት ሥላሴን በአንድነትና በሦስትነት ለማየት በቅቷል፡፡ በእርሱም የጽድቅ ሥራ ለብዙዎች ድኅነት ከመሆን አልፎ ቤተ ክርስቲያናችን ‹‹የአብርሃሙ ሥላሴ›› በማለት አብርሃምን ታመሰግነዋለች፡፡ ቅድስት ሥላሴ የሁሉ ፈጣሪ በመሆናቸው ክርስቲያን የሆነ ሁሉም የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት ሊያውቅ ይገባል፡፡ በ ‹‹ምሥጢረ ሥላሴ›› ትምህርት እንደምንረዳው ቅድስት ሥላሴ አንድም ሦስትም ናቸው፡፡ ‹‹ሥላሴ›› የሚለው ቃል ‹‹ሠለሰ፤ ሦስት አደረገ›› ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ ሦስትነት ማለት ነው፡፡  (መጽሐፍ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ገጽ ፮፻፷፱) ቅድስት ሥላሴ ስንልም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ማለታችን ነው፡፡  ‹‹ቅድስት›› ተብሎ ደግሞ በሴት አንቀጽ /ቅድስት ሥላሴ/  ይጠራል፤ ‹‹ቅድስት›› እና ‹‹ልዩ ሦስት›› የሚባልበትም ሃይማኖታዊ ምሥጢር፡- part 2 ይቀጥላል እውቀት እንገበይ በሃይማኖት እንጽና subscribe&share እያረጋችሁ https://www.youtube.com/@bonny1221 ይህ የተለግራም ግሩፕ ሊንክ ነው👇👇👇 https://t.me/Dnwonde channel https://t.me/orthodoxchallenge https://www.facebook.com/DeaconWondalemAlemayehu
Mostrar todo...
ግሩም ቲዩብ

በአጠቃላይ መንፈሳዊ አገልግሎቶችና ትምህርታዊ ነገሮች

✞✞✞ ✝️በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✝️✞✞✞ ❖ ሐምሌ ፭ ❖ ✞✞✞✝️ እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን #ዼጥሮስ #ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞✝️ =>ፍጡር ቢከብር ከእመ ብርሃን ቀጥሎ የእነዚህን ቅዱሳን ያህል የሚከብር አይኖርም:: ለቤተ ክርስቲያን ያልሆኑላት ምንም ነገር የለምና እርሷም "ብርሃኖቼ: ዐይኖቼ: ዕንቁዎቼ" ብላ ትጠራቸዋለች:: +" ✝️ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት✝️ "+ =>የዮና ልጅ ስምዖን ዼጥሮስ (ኬፋ) የተባለው በጌታችን ንጹሕ አንደበት ነው:: ይሔውም ዓለት (መሰረት) እንደ ማለት ነው:: ¤በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ዓሳ በማጥመድ አድጐ ¤ሚስት አግብቶ ዕድሜው 56 ሲደርስ ነበር ጌታችን የተቀበለው:: በዕድሜውም ሆነ በቅንዐቱ: በአስተዋይነቱም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ተብሏል:: ለሐዋርያትም አለቃቸው ሆኗል:: (ማቴ. 16:17, ዮሐ. 21:15) +ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተያዘባት ሌሊት ለሰራው ስሕተት ንስሃ ገብቶ ምሳሌም ሆኗል:: ቅዱስ ዼጥሮስ እንደ እረኝነቱ ሐዋርያትን ጠብቆ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሲያበቃ ከበዓለ ሃምሳ በሁዋላም ለሁሉም ሃገረ ስብከት አካፍሏል:: ምንም የርሱ ክፍል ሮሜ ብትሆንም አርድእትን ስለ ማጽናት በሁሉም አሕጉራት ዙሯል:: +በስተእርጅናው ብዙ መከራዎችን ተቀብሏል:: አሕዛብ ግብራቸው እንደ እንስሳ ነውና በአባታችን ላይ ቀልደዋል:: እርሱ ግን ሁሉንም ታግሷል:: የቅዱሱን ታሪክ ለመናገር ከመብዛቱ የተነሳ ይከብዳልና ልቡና ያለው ሰው ሊቃውንትን ሊጠይቅ እንደሚገባ እመክራለሁ:: +ቅዱስ ዼጥሮስ መልካሙን ገድል ተጋድሎ በ66 ዓ/ም የኔሮን ቄሳር ወታደሮች ሲሰቅሉት ለመናቸው:: "እባካችሁን? እኔ እንደ ጌታየ ሆኜ መሰቀል አይገባኝም" አላቸው:: እነሱም ዘቅዝቀው ሰቅለው ገድለውታል:: በበጐ እረኝነቱም የማታልፈውን ርስት ከነመክፈቻዋ ተቀብሏል:: በሰማዕትነት ሲያርፍም ዕድሜው ወደ 88 አካባብ ደርሶ ነበር:: ✝️=>#የቅዱስ_ዼጥሮስ መጠሪያዎች:-✝️ 1.ሊቀ ሐዋርያት 2.ሊቀ ኖሎት (የእረኞች / ሐዋርያት አለቃ) 3.መሠረተ ቤተ ክርስቲያን 4.ኰኩሐ ሃይማኖት (የሃይማኖት ዐለት) 5.አርሳይሮስ (የዓለም ሁሉ ፓትርያርክ) +"+✝️ #ቅዱስ_ዻውሎስ_ሐዋርያ ✝️+"+ =>የቤተ ክርስቲያን መብራቷ ቅዱስ ዻውሎስን እንደ ምን ባለ ዐማርኛ እንገልጠዋለን? ¤ስለ እርሱ መናገርና መጻፍ የሚችልስ እንደ ምን ያለ ሰው ነው? ¤የዓለምን ነገር ሲጽፍ በኖረ እጄስ እንደ ምን እጽፈዋለሁ? ¤ይልቁኑስ የርሱን 14ቱን መልዕክታትና ግብረ ሐዋርያትን መመልከቱ ሳይሻል አይቀርም:: +#ቅዱስ_ዻውሎስ ከነገደ ብንያም #ሳውል የሚባል የጠርሴስ ሰው ሲሆን ምሑረ ኦሪት: ቀናተኛና ፈሪሳዊ ነበር:: ጌታ በደማስቆ ጐዳና ጠርቶ በ3 ቀናት ልዩነት ምርጥ ዕቃ አደረገው:: ይህ የሆነው በ42 ዓ/ም: ጌታ ባረገ በ8ኛው ዓመት ነበር:: ከዚያማ ብርሃን ሆኖ አበራ:: ጨው ሆኖ አጣፈጠ:: +ከኢየሩሳሌም እስከ ሮም: ከእንግሊዝ እስከ እልዋሪቆን (የዓለም መጨረሻ) ወንጌልን ሰበከ:: ስለ ወንጌል ተደበደበ: ታሠረ: በእሳት ተቃጠለ:: በድንጋይ ተወገረ: በጦር ተወጋ:: ባፍም በመጣፍም ብሎ አገለገለ:: በየቦታውም ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ሠራ:: ለ25 ዓመታት ቀንና ሌሊት ያለ መታከት ወንጌልን ሰበከ:: +እርሱን የመሰሉ: እርሱንም ያከሉ ብዙ አርድእትን አፍርቶ: በ67 ዓ/ም በኔሮን ቄሳር ትእዛዝ አንገቱ ተቆርጧል:: ከ14ቱ መልዕክታቱ ባሻገር ቅዱስ ሉቃስ ወንጌልን ሲጽፍ አግዞታል:: ልክ ቅዱስ ዼጥሮስ ማርቆስን እንዳገዘው ማለት ነው:: =✝️>የቅዱስ ዻውሎስ መጠሪያዎች:-✝️ 1.ሳውል (ከእግዚአብሔር የተሰጠ) 2.#ልሳነ_ዕፍረት (አንደበቱ እንደ ሽቱ የሚጣፍጥ) 3.#ልሳነ_ክርስቶስ (የክርስቶስ አንደበቱ) 4.#ብርሃነ_ዓለም 5.#ማኅቶተ_ቤተ_ክርስቲያን (የቤተ ክርስቲያን መቅረዝ) 6.#የአሕዛብ_መምሕር 7.#መራሒ (ወደ መንግስተ ሰማያት የሚመራ) 8.#አእኩዋቲ (በምስጋና የተሞላ) 9.#ንዋይ_ኅሩይ (ምርጥ ዕቃ) 10.#መዶሻ (ለአጋንንትና መናፍቃን) 11.#መርስ (ወደብ) 12.#ዛኅን (ጸጥታ) 13.#ነቅዐ_ሕይወት (የሕይወት ትምሕርትን ከአንደበቱ ያፈለቀ) 14.#ዐዘቅተ_ጥበብ (የጥበብ ምንጭ / ባሕር) 15.#ፈዋሴ_ዱያን (ድውያንን የፈወሰ) . . . =>ጌታችን እግዚአብሔር የአባቶቻችንን ብርሃን ያብራልን:: ከበረከታቸውም ያድለን:: =>ሐምሌ 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት= 1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት 2.ቅዱስ ዻውሎስ ብርሃነ ዓለም 3.ቅዱሳን 72ቱ አርድእት (ዛሬ ሁሉም ይታሠባሉ) 4.ቅዱስ ሳቁኤል ሊቀ መላእክት 5.ቅድስት መስቀል ክብራ (የቅዱስ ላሊበላ ሚስት) 6.ቅዱሳን ዘደብረ ዓሣ 7.ቅዱሳት አንስት (ዴውርስ: ቃርያ: አቅባማ: አቅረባንያና አክስቲያና-የቅዱስ ዼጥሮስ ተከታዮች) =>ወርሐዊ በዓላት 1.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 2.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ 3.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ 4.ቅድስት አውጋንያ (ሰማዕትና ጻድቅ) =>+"+ ጌታ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው:: "የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ! በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይሕንን አልገለጠልህምና ብጹዕ ነህ:: እኔም እልሃለሁ:: አንተ #ዼጥሮስ ነህ:: በዚህችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ:: የገሃነም ደጆችም አይችሏትም:: የመንግስተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ:: በምድር የምታሥረው ሁሉ በሰማያት የታሠረ ይሆናል:: በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል::" +"+ (ማቴ. 16:17) =>+"+ በመሥዋዕት እንደሚደረግ የእኔ ሕይወት ይሠዋልና:: የምሔድበትም ጊዜ ደርሷል:: መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ:: ሩጫውን ጨርሻለሁ:: ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ:: ወደ ፊት #የጽድቅ_አክሊል ተዘጋጅቶልኛል:: ይሕንም ጻድቅ: ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል:: +"+ (2ጢሞ. 4:6) <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>> " ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/ ምንጭ፦ ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት እውቀት እንገበይ በሃይማኖት እንጽና subscribe&share እያረጋችሁ https://www.youtube.com/@bonny1221 ይህ የተለግራም ግሩፕ ሊንክ ነው👇👇👇 https://t.me/Dnwonde channel https://t.me/orthodoxchallenge https://www.facebook.com/DeaconWondalemAlemayehu
Mostrar todo...
ግሩም ቲዩብ

በአጠቃላይ መንፈሳዊ አገልግሎቶችና ትምህርታዊ ነገሮች

እውቀት እንገበይ በሃይማኖት እንጽና subscribe&share እያረጋችሁ https://www.youtube.com/@bonny1221 ይህ የተለግራም ግሩፕ ሊንክ ነው👇👇👇 https://t.me/Dnwonde channel https://t.me/orthodoxchallenge https://www.facebook.com/DeaconWondalemAlemayehu
Mostrar todo...
ጸልዩ በእንተ ሰላም

በዚህ group መንፈሳዊና ጠቃሚ ነገሮችን መጋራት ይቻላል ስሙ እንደምነግረን ስለ ሰላም፣ፍቅር፣አንድነት፣ሃይማኖት ት/ት መነጋገር መማማር እና ኦርቶዶክስ ቤ/ያን ያስተማረችንን ትምህርታዊ ነገሮችንን መጋራት መወያየት ትልቁና ዋነኛ አላማው ነው::

+ የዝምታ ጩኸት + እስራኤል ጭንቅ ላይ ናቸው:: ከባርነት ተላቅቀው ከግብፅ ከወጡና ጉዞ ከጀመሩ በኁዋላ ፈርኦን የለቀቀው ሕዝብ ጉልበት ቆጭቶት በቁጣ ነድዶ ሠራዊቱን አስከትቶ በፈጣን ሠረገላ እየጋለበ መጣባቸው:: ከፊታቸው ደግሞ የሚያስፈራ ባሕር ተደቅኖአል:: ሕዝቡ የፈረደበት ሙሴ ላይ ጮኹበት:: መጽሐፈ መቃብያን "ያንን ሁሉ ሕዝብ ሲጠብቅ ያልተበሳጨ ሙሴን አስበው" እንደሚል እንደ ሙሴ ትሑትና ታጋሽ መሪ ታይቶ አይታወቅም:: ልክ በዚያች ዛፍ ላይ እሳት ሲነድባት እንዳልተቃጠለች እስራኤላውያንም ሙሴ ላይ ለዓመታት ቢነዱም አላቃጠሉትም:: "በግብፅ መቃብር ጠፍቶ ልታስፈጀን ነው?" "ከሞት ባርነት በስንት ጣዕሙ?" እስራኤል በኤርትራ ባሕር ዳርቻ ሙሴን በቁጣ እየጮኹ አስጨነቁት:: መሪነት ከባድ ነው:: ያንን ሁሉ ድንቅ ነገር አድርጎ እግዚአብሔር ነፃ ሲያወጣቸው ሙሴ ለእነርሱ ቤዛ ሆኖ ተሹሞ ብዙ ዋጋ ከፍሎአል:: ውለታውን ረስተው አፋጠጡት:: "ሙሴም ለሕዝቡ፦ አትፍሩ፥ ዛሬ የምታዩአቸውን ግብፃውያንን ለዘላለም አታዩአቸውምና ቁሙ፥ ዛሬ ለእናንተ የሚያደርጋትን የእግዚአብሔርን ማዳን እዩ። እግዚአብሔር ስለ እናንተ ይዋጋል፥ እናንተም ዝም ትላላችሁ፡ አላቸው" ሙሴ ሕዝቡን ከጩኸታቸው ሲያረጋጋ ሳለ የእግዚአብሔር ድምፅ ወደ ሙሴ መጣ "ሙሴ ሆይ ለምን ትጮኽብኛለህ?" አለው:: ልብ አድርጉ የጮኸው ሕዝቡ ነው ሙሴ አረጋጋ እንጂ ቃል አልተናገረም:: ሆኖም ሙሴ አፉ ዝም ቢል ልቡ ይጮኽ ነበር:: ከእስራኤል ጩኸት ይልቅ የሙሴ ዝምታ እግዚአብሔር ጆሮ ደረሰ:: እግዚአብሔር ኤልያስ እንዳላገጠባቸው የአሕዛብ አማልክት በጩኸት ብዛት የሚሰማ አምላክ አይደለም:: በትዕቢትና አመፅ ከሞላበት ጩኸት ይልቅ በተሰበረ ልብ የሚቀርብ ዝምታ እግዚአብሔር ጋር ይጮኻል:: የእስራኤል ጩኸት ፍርሃት ይነዛል:: ልናልቅ ነው የሚል ሽብር ይፈጥራል:: የሙሴ ዝምታ ግን ባሕር ይከፍላል:: ጌታ ሆይ ጩኸታችን አልሆነልንም:: ዝምታችንን ሰምተህ ሀገራችንን ከከበባት ጥፋት ታደግልን:: የእኛ መጨቃጨቅና ጠብ ባሕር አይከፍልም:: የእኛ ጩኸት ከመነካከስ በቀር አያሻግርም:: በአርምሞ የሚለምኑህን በእኛ ፊት ዝም አሉ የምንላቸው በአንተ ፊት ግን የሚጮኹትን ሰምተህ ታደገን:: የኤርትራ ባሕር በዝምታ ተከፈለ:: እስከ ራማ የተሰማው ራሔል ስለ ልጆችዋ ያለቀሰችው ዕንባ ባሕር ከፈለ:: እመቤታችን ሆይ ስለ እኛ ስለልጆችሽ እባክሽን አልቅሺ:: የራሔል ዕንባ ራማ ከደረሰ የአንቺ ዕንባ የት ሊደርስ ነው? በየበረሃ እየወደቀ ስላለው ልጅሽ ስለሞተለት ወንድም እባክሽን ለምኚ:: በሙሴ በትር ባሕሩ ተከፈለ:: የኤርትራ ባሕር (ቀይ ባሕር [በግሪኩ erythos ማለት ቀይ ነው]) እጅግ ባለ ታሪክ ባሕር ነው:: ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ደረቅ ሆኖ ፀሐይ ያየውና ግማሽ ሚልየን የሚሆን ሕዝብ በመካከሉ ተራምዶ ያለፈበት ይህ ባሕር እንንደ ግድግዳ የቆመ ብቸኛው የዓለማችን ባሕር ነው:: በዚህ ባሕር እስራኤል ሲሻገሩ ፈርኦን ከነሠራዊቱ ሰጠመ:: በእግር የሔዱት የተሻገሩትን ባሕር በሠረገላ የሔዱት አቃታቸው:: የኤርትራ ባሕር ለእስራኤል ትንሣኤ ሲሆን ለፈርኦን ግን መቃብር ሆነ:: ፈርኦን ደንግጦ መመለስ የነበረበት ባሕሩ ሲከፈል ሲያይ ነበር:: ፈርኦንን ያደቆነ ሰይጣን ግን ባሕር መካከል ሳያቀስስ አልለቀቀውም:: እግዚአብሔር ማን ነው? ብሎ ነበር በዚያ ባሕር ተዋወቀው:: እሱ ሲሰጥም እስራኤል በኩራት "እግዚአብሔር ማን ነው? " ለሚለው የፈርኦን ጥያቄ ከባሕር ማዶ ሆነው መልስ ሠጡ "እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው" አሉ:: እስራኤል በኤርትራ ባሕር መሻገራቸው የጥምቀት ምሳሌ ሆኖ "በባሕርና ደመና ተጠመቁ" ተብሎላቸዋል:: ፈርኦን ግን እስራኤል በተጠመቁበት ጠበል ውስጥ ሰጠመ:: የኤርትራን ባሕር ሲሻገሩ ከሙሴ ሌላ እስራኤልን ሲመራ የነበረ ጠባቂ ነበረ:: እርሱም የእስራኤል ጠባቂ (advocate of Israel) በመባል የሚታወቀው ቅዱስ ሚካኤል ነበር:: "በእስራኤልም ሠራዊት ፊት ይሄድ የነበረው የእግዚአብሔር መልአክ ፈቀቅ ብሎ በኋላቸው ሄደ፤ የደመናውም ዓምድ ከፊታቸው ፈቀቅ ብሎ በኋላቸው ቆመ" ዘጸ 14:19 እንዲል ቅዱስ ሚካኤል እስራኤልን ቀን በደመና ሌሊት በብርሃን ዐምድ እየተመሰለ በመንገድ መራቸው:: ኢትዮጵያውያን ያለነው ከባሕሩ ዳርቻ ላይ ነው:: ሁሉም መሻገር ይፈልጋል:: ከእኛ መካከል እንደ ፈርኦን ሰጥሞ የሚቀር ይኖራል:: እንደ እስራኤል የሚሻገር ይኖራል: : ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ለእኛም ድረስልን:: ይህንን ክፉ ዘመን በክንፎችህ አሻግረን:: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ኅዳር 12 2013 ዓ ም ድሬደዋ ኢትዮጵያ ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
Mostrar todo...
🕊 † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † [ † እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ] † 🕊 ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ 🕊 †    ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: [ሉቃ.፩፥፮] የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ [አድናቆት] ይገባል ! እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ ፺ [90] የዘካርያስ ፻ [100] ደግሞ ደርሶ ነበር:: ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት [ኢሳ.፵፥፫] (40:3) , [ሚል.፫፥፩] (3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው:: ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም ፳፮ [26] ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ፮ [6] ወራት ራሷን ሠወረች:: በ፮ [6] ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው:: የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ በዚህች ቀን [ሰኔ ፴] (30) ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል:: መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ + የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ + በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት + በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ + እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ + የጌታችንን መንገድ የጠረገ + ጌታውን ያጠመቀና + ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው:: ስለዚሕም ቤተ ክርስቲያን ነቢይ: ሐዋርያ: ሰማዕት: ጻድቅ: ገዳማዊ: መጥምቀ መለኮት: ጸያሔ ፍኖት: ቃለ ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች:: †  🕊  አባ ጌራን ሕንዳዊ  🕊  † ዳግመኛ በዚህች ቀን ሕንድ ካፈራቻቸው ታላላቅ ቅዱሳን አንዱ የሆኑት ጻድቁ አባ ጌራን ይታሰባሉ:: የእኒህ ቅዱስ ታሪክ አሳዛኝ ነው:: ቅዱሱ በሕንድ ተወልደው: በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አድገው: ገና በወጣትነታቸው መንነው: ደሴት ውስጥ ወደሚገኝ አንድ በርሃ ገብተዋል:: ከገድላቸው ጽናት: ከቅድስናቸውም ብዛት የተነሳ በሃገረ ሕንድ ሰይጣን እንዳይገባ: ጠብ ክርክር እንዲጠፋ: ሰው ሁሉ በፍቅርና በሰላም እንዲኖር ማድረግ ችለው በጣም ተወዳጅ ነበሩ:: በዚህ የተበሳጨ ሰይጣን ግን ባልጠረጠሩት መንገድ መጣባቸው:: አንዲት ሴት ወደ እርሳቸው መጥታ [የንጉሡ ልጅ ነኝ በሚል] አስጠግተዋት ነበር:: አንድ ሌሊት ላይ ግን አውሬ ያባረራት በመምሰል ሩጣ ወደ ቤታቸው ገብታ አቀፈቻቸው:: በዚያ ቅጽበት ፍጡር ደካማ ነውና ታላቁ አባ ጌራን ተሰነካከሉ:: ከአፍታ በሁዋላ የሆነውን ሲያውቁ ደም አለቀሱ:: ልብሳቸውን ቀደው: እንባቸው እንደ ዥረት እየፈሰሰ አለቀሱ:: ራሳቸውን በትልቅ ድንጋይ እየቀጠቀጡት የጭንቅላታቸውና የደረታቸው አጥንቶች ተሰባበሩ:: እርሱ እግዚአብሔር መሐሪ ነውና ይቅር ብሎ: የቅድስና ስም ሰጥቶ በዚሕች ቀን ወደ ገነት አሳርጉዋቸዋል:: ለዚህ ነው መጽሐፉ "ጻድቅ ፯ [7] ጊዜ ይወድቃልና: ይነሣማል" ያለው:: [ምሳ.፳፬፥፲፮] (24:16) አምላካችን ከቅዱሱ ቤተሰብና ከጻድቁ አባ ጌራን በረከት ይክፈለን:: 🕊 [ † ሰኔ ፴  [ 30 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት [ልደቱ] ፪. ቅዱሳን ዘካርያስና ኤልሳቤጥ [ወላጆቹ] ፫. አባ ጌራን መስተጋድል [ሕንዳዊ] ፬. ቅዱሳት ደናግል ማርያና ማርታ [ከ፴፮ (36) ቱ ቅዱሳት አንስት-የአልዓዛር እህቶች] [ †  ወርኀዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ [ሐዋርያ] ፪. አባ ሣሉሲ ክቡር ፫. ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት ፬. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት " ደግሞም አንተ ሕጻን ሆይ የልዑል ነቢይ ትባላለህ:: መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሔዳለህና:: እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ:: ይሕም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው::" [ሉቃ.፩፥፸፮] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † subscribe&share እያረጋችሁ https://www.youtube.com/@bonny1221 ይህ የተለግራም ግሩፕ ሊንክ ነው👇👇👇 https://t.me/Dnwonde channel https://t.me/orthodoxchallenge https://www.facebook.com/DeaconWondalemAlemayehu/
Mostrar todo...
ጸልዩ በእንተ ሰላም

በዚህ group መንፈሳዊና ጠቃሚ ነገሮችን መጋራት ይቻላል ስሙ እንደምነግረን ስለ ሰላም፣ፍቅር፣አንድነት፣ሃይማኖት ት/ት መነጋገር መማማር እና ኦርቶዶክስ ቤ/ያን ያስተማረችንን ትምህርታዊ ነገሮችንን መጋራት መወያየት ትልቁና ዋነኛ አላማው ነው::

Mostrar todo...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

Mostrar todo...
begibigubae zemariyan le misreta beal yekereb zimare

eotc tv\ahadu tv\mk TVs

Mostrar todo...
woreb begibigubae zemariyan ለምሥረታ በዓል መረሃግብር

new

Mostrar todo...
የደብረ ብርሃን ዩ/አ/ወ/ጤ/ሳ/ካ ግቢ ጉባኤ መዘምራን ለምሥረታ በዓል ዋዜማ በጸሎት መረሃግብር ላይ ያቀረቡት ዝማሬ

share subscribe eotc tv/ahadu tv/fana tv/ebs/kana...

ጾመ ድኅነት ዕሮብ ሰኔ ፲፱ /2016 E.C በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!          ጾመ ድኅነት (የረቡዕና ዓርብ ጾም)    ጾመ ድኅነት የሚጾመው የጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መከራ መስቀል ምክንያት በማድረግ ነው፡፡ ጾመ ድኅነት የሚለውንም ስያሜ ያገኘው ኢየሱስ ክርስቶስ መከራ መስቀልን የተቀበለው ለእኛ ድኅነተ ነፍስ በመሆኑ ነው፡፡ ይኸውም ወደዚህ ዓለም የመጣበት ዋናው ምክንያት የሰውን ልጅ ለማዳን የገባውን ቃል ኪዳን ለመፈጸም ሲሆን ድኅነት የሚገኘው ደግሞ የጌታችን የአምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደም ሲፈስ ሥጋውም ሲቆረስ በመሆኑ ነው፡፡    አይሁዳውያን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመግደል ብዙ ጊዜ ተሰብስበው ይመካከሩ ነበር፤ ሆኖም ግን ትንቢቱ የሚፈጸምበት ጊዜ ስላልደረሰ ከዓይናቸው ይሰወርባቸዋል፡፡ ቀነ ቀጠሮው ሲደርስ ግን ራሱን አሳልፎ ሰጠ እንጂ አልተሰወረባቸውም፤ (ዮሐ 18፥4-9)፡፡ አይሁዳውያን የመጨረሻዎቹን ስብሰባዎች ያደረጉት ከበዓለ ሆሳዕና ቀጥሎ ባሉት ቀናት (ሰኞ፣ ማክሰኞና ረቡዕ) ነው፡፡ ረቡዕ የሚጾምበት ምክንያት፡- እግዚአብሔር ቀነ ቀጠሮው እስኪደርስ በአምላካዊ ጥበቡ ያዘገይባቸው ነበርና በሰኞ እና በማክሰኞ ስብሰባ አልተስማሙበትም፡፡ በረቡዕ ስብሰባቸው ግን እግዚአብሔር እኛን ለማዳን የወሰነው ቀነ ቀጠሮ ስለደረሰ ‹‹ይሰቀል፣ ይገደል›› ብለው ተስማምተውበታል፡፡ ዕድሜው ለጾም የደረሰ (ሰባት ዓመት የሞላው) ኦርቶዶክሳዊ ሁሉ ይህን በማሰብ (አብነት በማድረግ) እንዲጾም ሐዋርያት ትዕዛዝ ሠርተዋል፡፡ የባሕርይ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ድኅነት የሞት ውሳኔ የተወሰነበትን ይህን ዕለት ሁል ጊዜ በማስታወስ መጾም ይገባናል፡፡ ዓርብ የሚጾምበት ምክንያት፡- አይሁዳውያን ረቡዕ ባደረጉት ስብሰባ ሊገድሉት ቢስማሙም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቀጠሮ ሰዓት አንዲት ደቂቃ እንኳ ወደ ፊት ወይም ወደ ኋላ አይልምና በዚህ ዕለት ጌታን አላገኙትም፡፡ በማግስቱ ሐሙስ ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ጌታ ራሱን አሳልፎ ሰጣቸው፤ አሁን ቀጠሮው ደርሷልና ጌታን ከያዙበት ጊዜ ጀምረው ሲገርፉትና ሲያንገላቱት አቆይተው በዕለተ ዓርብ ከቀኑ ስድስት ሰዓት ላይ በዕፀ-መስቀል ላይ ሰቅለውታል፡፡ ዕለተ ዓርብ የጌታ መከራ መስቀል (ስቅላትና ሞት) መታሰቢያ ተደርጎ ይታሰባል፡፡ በዚህም ምክንያት ዓርብ እንዲጾም ሐዋርያት ትዕዛዝ ሠርተዋል፡፡   ስለዚህ እኛም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ረቡዕ ያለጥፋቱ የተወነጀለበትን ዓርብ ደግሞ በተዛባ ፍርድ የተሰቀለበትን ሁኔታ በማሰብ ‹‹ስለ እኛ ይህን ሁሉ መከራ ተቀበለ፤ እኛ ግን ዛሬም ድረስ በኃጢአት ውስጥ ነን›› ብለን ራሳችንን እየወቀስን ንስሐ በመግባት ልንጾመው ይገባል፡፡    ማስታወሻ፦ ከትንሣኤ ጀምሮ እስከ ጰራቅሊጦስ ያሉት ሃምሳው ዕለታት የደስታና የድል በመሆናቸው ከጾምና ከስግደት ቀኖና ተከልክለን ደስታችንን በጸሎትና በምስጋና እንፈጽማለን፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደትና በቁመት ኀዘን በመቆየታችን የመከራ አጸፋው ደግሞ ደስታ በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን ከጸሎትና ከቃለ እግዚአብሔር ርቆ በመብልና በመጠጥ ማሳለፍ ማለት አለመሆኑን ልብ ልንል ይገባል፡፡ በተጨማሪም በዓለ ጥምቀትና በዓለ ልደት ረቡዕ ወይም ዓርብ በሚውሉበት ጊዜ አይጾምም፡፡ ጾሙ ፈውሰ ሥጋ ድኅነተ ነፍስ የምናገኝበት ይሁንልን አሜን!           ወስብሐት ለእግዚአብሔር! ምንጭ፦ ሰባቱ አጽዋማት ፣ ጾምና ምጽዋት እውቀት እንገበይ በሃይማኖት እንጽና subscribe&share እያረጋችሁ https://www.youtube.com/@bonny1221 ይህ የተለግራም ግሩፕ ሊንክ ነው👇👇👇 https://t.me/Dnwonde channel https://t.me/orthodoxchallenge https://www.facebook.com/DeaconWondalemAlemayehu
Mostrar todo...
ግሩም ቲዩብ

በአጠቃላይ መንፈሳዊ አገልግሎቶችና ትምህርታዊ ነገሮች

Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.