cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

Publicaciones publicitarias
190
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
-130 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለፋሲካ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።መልካም በዓል‼ ======================== አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ https://t.me/tamagnpress
Mostrar todo...
ትላንት ማታ በአቃቂ የገበያ ማዕከል በደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ 16 ሱቆች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል። ሚያዚያ  24 ቀን2016 ዓ.ም ምሽት 3:10 ሰዓት ላይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ  ወረዳ 03 አቃቂ የገበያ  መዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ 16 ንግድ  ሱቆች  ሙሉ በሙሉና በከፊል ተቃጥለዋል። የእሳት አደጋዉን  ለመቆጣጠር አምስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ ሁለት የዉሀ  ቦቴ  ከ44 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጋር የተሰማራ ሲሆን እሳቱ ወደገበያ ማዕከሉ ተስፋፍቶ በሰዉና በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር የተቻለ ሲሆን አደጋዉን ለመቆጣጠር ሁለት ሰዓት ፈጅቷአል። በአደጋ መቆጣጠሩ ሂደት የፌደራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በሰው  ላይ የደረሰ ጉዳት  የለም።አቃቂ የገበያ ማዕከል ትንሹ መርካቶ እየተባለ የሚጠራ የገበያ ማዕከል ሲሆን ገበያ ማዕከሉ በከተማ ደረጃ ለእሳት አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ ከተለዩ አንዱ ሲሆን በገበያ ማዕከሉ በተደጋጋሚ የእሳት አደጋ እያጋጠመ በንብረት ላይ ጉዳት ሲደርስ ቆይቷል። ኮሚሽን መ/ቤቱ ገበያ ማዕከሉ ለአደጋ የተጋለጠባቸዉን ዝርዝር ጉዳዮችን የመፍትሄ ሀሳቦችን አካቶ ለገበያ ማዕከሉ ማህበራትና ለሚመለከታቸዉ አካላት ያቀረበ ቢሆንም የማስተካከያ ዕርምጃዎች አልተወሰዱም።በመሆኑም በቀጣይ መሰል አደጋዎች እንዳያጋጥሙ መፍትሄ እንዲሰጥ ኮሚሽኑ ያሳስባል። Via Ethio FM @YeneTube @FikerAssefa
Mostrar todo...
Mostrar todo...

" ... ትጥቅ ሙሉ በሙሉ የማስፈታት ሁኔታ የሚፈጠረው ለትግራይ ሰላማዊ ሁኔታ ሲፈጠር ነው " - አቶ ኢያሱ ተስፋይ ከቀናት በፊት የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ፥ በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነት እና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ከመከረ በኃላ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል። በመግለጫው የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት ብዙ ውጤቶች እና እፎይታን ያስገኘ ቢሆንም አሁንም ቀሪ ስራዎች እንዳሉ ገልጾ ነበር። ከነዚህ ቀሪ ስራዎች አንዱ የ ' ህወሓት ' ትጥቅ መፍታት እንደሆነ ጠቁሞ ፤ " በሰላም ስምምነቱ መሰረት ህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው ፤ በብሄራዉ ተሃድሶ ኮሚሽን እቅድ መሰረት በፍጥነት መተግበር አለበት " ብሎ ነበር። በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሰጠው ህወሓት በስምምነቱ መሰረት " ከኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ / የፌዴራል ጸጥታ ኃይል ውጭ ያለ ማንኛውም ኃይል ከትግራይ የአስተዳደር ወሰን እንዲወጡ መደረግ አለበት " ብሏል። የህወሓት ፕሮፖጋንዳ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢያሱ ተስፋይ ከሰሞኑን ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ፥ " ' ለዘላቂ ሰላም ትጥቅ መፍታት አለባቸው የሚለው ችግር የለውም ትክክል ነው። እንደ ትግራይ ህዝብ ፖለቲካዊ ጥያቄዎቻችን ከተመለሱልን ወደ ልማት እና ወደ የዴሞክራሲ ግንባታ ስራችን መሸጋገር እንፈልጋለን " ብለዋል። " ለሰላም ከማንም በላይ ጥብቅና እንቆማለን ስትራቴጃካዊ ፍላጎታችን ነው ግን ደግሞ ያ ሰላም ከጥያቄዎቻችን መመለስ ጋር በቀጥታ መያያዝ አለበት እንጂ ጥያቄዎቻችን ሳይመለሱ መብታችን ሳይከበር ዝም ብሎ ሰላም የሚመጣ ነገር አይደለም " ሲሉ ተደምጠዋል። " ለሰላም ብለን ቀደም ብለን ትጥቅ ማስፈታት ጀምረናል። የከባድ ማሳሪያም ርክክብም ከአመት በፊት አድርገናል፣ ከዛ አልፎ ከነበረን ሰራዊት በርካታውን demobilize አድርገናል ፤  " ሲሉ አክለዋል። " ትጥቅ #ሙሉ_በሙሉ_የማስፈታት_ሁኔታ የሚፈጠረው ለትግራይ ሰላማዊ ሁኔታ ሲፈጠር ነው። ከፌዴራል ኃይል ውጭ ያሉ የተለያዩ ታጣቂ ኃይሎች በምዕራብ ትግራይ አሉ ህዝባችንን ለብዙ መከራ እየዳረጉ ያሉ በጸለምትም ፣ በደቡብ ትግራይም ስለዚህ አሁን ፌዴራል በጀመረው ነገር እነዚህን ኃይሎች ትጥቃቸውን እንዲፈቱና ወደ ሌላ ስራቸው እንዲሄዱ የማድረግ ኃላፊነት አለበት " ብለዋል። ለDDR የሚያስፈልገው ሁሉ በጀትም መመደብ አለበት ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ገልጸዋል። @tikvahethiopia https://t.me//tamagnpress
Mostrar todo...
@T_PRESS

ኩሩ ኢትዮጽያዊ ነኝ

https://www.facebook.com/profile.php?id=100088810264376

መረጃ‼️ ዛሬ በወልቃይት ጠገዴ አካባቢ ህወሃት ተኩስ ከፍቶ ከ13 በላይ የመከላከያ ሰራዊት አባላት መግደሉ ተሰምቷል ። በአከባቢው ሰወስት ሀይሎች ከፍተኛ ፍጥጫ ዉሰጥ ገብተዋል። ©ሪፖርተር ET ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇👇 https://t.me//tamagnpress
Mostrar todo...
ሪፖርተር ET

🔖 ይህ የሪፖርተር ET የቴሌግራም ገፅ ነው ®️ => በቻናሉ 📌 ፈጣን 📌 ትኩስ 📌 ወቅታዊ እና 📌 ወሳኝ መረጃዎችን እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል ! 🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !

አቶ ታዬ ደንደአ የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍ እና የጦር መሳሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው #FastMereja የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ የነበሩት አቶ ታዬ ደንደአ የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍና ጦር መሳሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው። ክሱ የተመሰረተው በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ሕገ-መንግስትና ሕገ-መንግስት ሥርዓት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮችን በሚመለከተው ችሎት ነው። የፍትሕ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሽ ታዬ ደንደአ ላይ ሶስት ክሶችን አቅርቧል። በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 251/ሐ እና አንቀጽ 257/ሰ ስር የተመላከተውን ድንጋጌ እና የጦር መሳሪያ አዋጅን መተላለፍ የሚል ክስ አቅርቦባቸዋል። በክሱ ላይ እንደተመላከተው÷ተከሳሹ የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ ሆነው ሲሰሩ የሀገርን፣ የመንግስትንና የህዝብን ደህንነት ማረጋገጥ ሲገባቸው ይህን ወደጎን በመተው  ፀረሰላም ኃይሎችን የሚደግፉ የፕሮፖጋንዳ መልዕክቶችን በማስተላለፍ በስማቸው በተከፈተ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ድጋፍ የሚገልጹ መልዕክቶችን  ሲያስተላልፉ ነበር የሚል ነው፡፡ እንዲሁም ፍቃድ ሳይኖራቸው የጦር መሳሪያ አዋጁን በመተላለፍ በታህሳስ 1 ቀን 2016 ዓ.ም  ከረፋዱ 5 ሰዓት  ላይ በልደታ ክ/ከ ወረዳ 6  በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በተደረገ ብርበራ አንድ ታጣፊ ክላሽን ኮቭ  መሳሪያ ከ2 ክላሽ ካዝና  እና ከ60 ጥይት ጋር ይዘው መገኘታቸው ተጠቅሶ ክስ ቀርቦባቸዋል። ተከሳሽ አቶ ታዬ ደንደአ በአራት ጠበቆቻቸው ተወክለው ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ ተነቦላቸዋል። ክሱ ከተነበበ በኋላ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጥያቄ ቀርቧል። ዘገባው የፋና ነው። https://t.me//tamagnpress
Mostrar todo...
በርካታ የሐሰተኛ እና የጥላቻ ንግግር ጥቆማዎች እየደረሱኝ ነው - የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን‼️ በርካታ የሐሰተኛ እና የጥላቻ ንግግር ጥቆማዎች እየደረሱት መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡ ባለስልጣኑ የጥቆማ መቀበያ ነጻ የስልክ መስመር ይፋ ካደረገ በኃላ በርካታ ጥቆማዎች እየደረሱት መሆኑን የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለኢቢሲ ሳይበር ተናግረዋል፡፡ የሚመጡ ጥቆማዎችን ተገቢነት በማጣራት ጥፋተኞችን ለሕግ ለማቅረብ ከፍትሕ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ የጥላቻ እና ሐሰተኛ ንግግሮች በአዋጁ መሰረት ከገንዘብ እስከ እስራት ቅጣት እንደሚያስከትሉ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ጠቁመዋል፡፡ ባለስልጣኑ የማህበራዊ የትስስር ገጽ አገልግሎት ሰጪዎች የኢትዮጵያን ሕግ እና ስርዓት አክብረው እንዲሰሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡ ህዝቡ ለሀገራዊ ሰላም እና ለህዝቦች አንድነት ፀር የሆኑ የሐሰተኛ እና የጥላቻ ንግግሮችን ሲመለከት በ9192 ነጻ የስልክ መስመር ጥቆማዎችን እንዲሰጥ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አሳስበዋል፡፡ https://t.me//tamagnpress
Mostrar todo...
@T_PRESS

ኩሩ ኢትዮጽያዊ ነኝ

https://www.facebook.com/profile.php?id=100088810264376

ብልፅግና እና ህውሃት ዛሬ በአዲስ አበባ ተገናኝተው ምክክር ማድረግ መጀመራቸውን ከመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘገባ ለማወቅ ተችሏል።የምክክሩ ዝርዝር ሁኔታ በግልፅ አልተብራራም።
Mostrar todo...
በጋምቤላ ክልል 14 አመራሮችና አንድ ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር ዋሉ። በጋምቤላ ክልል በጆርና በኢታንግ ልዩ ወረዳ ተከስቶ በነበረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት እጃቸው አለባቸው የተባሉ 14 አመራሮችና አንድ ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ኡሞድ ኡሞድ እንዳሉት በቁጥጥር ስር የዋሉት አመራሮችና ግለሰቦች በጆር እና በኢታንግ ልዩ ወረዳ ተፈጥሮ በነበረው የፀጥታ ችግር እጃቸው አለባቸው የተባሉ ናቸው ብለዋል። በተለይም በመጋቢት 26/2016 ዓመተ ምህረት በጆር ወረዳ ለተከሰተው የሰው ህይወት መጥፋትና ለንብረት መውደም እጃቸው አለባቸው የተባሉ ሁለት የዞን ከፍተኛ አመራሮች እና አምስት የወረዳ አመራሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልፀዋል። ከዚህም በተጨማሪ በኢታንግ ልዩ ወረዳ የሚፈለጉ ተጠርጣሪዎች ለህግ እንዳይቀርቡ እንቅፋት የሆኑ ሰባት የወረዳ አመራሮች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ተገቢው ማጣራት እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም በተለያዩ መድረኮች በጋምቤላ ከተማ ብሔርን ከብሔር ለማጋጨት የሚሞክር አንድ ግለሰብ ከአመራሮቹ ጋር በቁጥጥር ስር መዋሉንም አስታውቀዋል። በክልሉ ተከስቶ የነበረው የፀጥታ መደፍረስ ወደ ቀድሞ ሰላሙ እንዲመለስ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ለሰላም ቅድሚያ ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ ኮሚሽነር ኡሞድ ጥሪ አቅርበዋል። መረጃው የጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው @sheger_press https://t.me//tamagnpress
Mostrar todo...
@T_PRESS

ኩሩ ኢትዮጽያዊ ነኝ

https://www.facebook.com/profile.php?id=100088810264376

👍 1
ሚኒስትሩ ከስልጣን ተነሱ‼️ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌዴራል ሥነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሾመዉ የነበሩት አቶ ፀጋ አራጌ ከስልጣን መነሳታቸውን የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገልጸዋል። ጥቆማ❗❗👇 👉ፈጣን እና ያልተሰሙ መረጃዎችን ለማግኘት፣ከስር ባለው ሊንክ የቴሌግራም ቻናሉን join አድርጉ፣ https://t.me//tamagnpress
Mostrar todo...