cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Amharic spritiual books and teaching

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
239
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

48 ሰአት በሲዖል (እውነተኛ ታሪክ) በጆን ደብልዩ ሬይኖልድስ ክፍል 4 እርሱም በቀጠሮው ቀን ሰዓቱን ጠብቆ መጣ በደንብ ተዋወቅንና አረፍ ብሎ ጥቂት ከተጫወትን በኃላ የእርሱን አስደናቂ ታሪክ እንደሰማሁና ይህንን ታሪኩን እንዴት እንደነበረ ከራሱ አንደበት ለመስማት በጣም እንደፈለግሁ ነገርኩት። ፍቃደኛነቱን ለመግለፅ ፈገግ አለና የህይወት ታሪኩን ከመጀመሪያ ጀምሮ መተረክ ጀመረ። እኔም በጥሞና መከታተል ቀጠልኩ። ይህ ሰው መልከ መልካም እድሜው ከሠላሣ የማይበልጥ ነበር። ታሪኩን የጀመረልኝ በትምህርት ደረጃው በጣም የተማረ እንደነበርና በተፈጥሮው ብልሃተኛ እንደሆነ በሌላ በኩል ደግሞ እጅግ አስቸጋሪ ባህሪ ያለው አጥፊ ወንጀለኛ እንደነበር በመንገር ነው። ከህይወት ዘመኑ ሁሉ የርሱ በጣም አስደናቂው የታሪክ ክስተት የተፈፀመው ግን በአደጋው በሞተ ጊዜ እንደሆነ መተረክ ሲጀምር እኔም በተማርኩት በአጭር ጽሑፍ ጥበብ (ሾርት ሃንድራይቲንግ) የሚናገረውን እየፃፍኩ ተከተልኩት። ከአደጋው ጊዜ ጀምሮ እንዲህ ሲል ተረከልኝ። አደጋ በደረሰብኝ በዚያን እለት ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ከጧት ጀምሮ በጣም ቀፎኝ ነበር። አንድ ነገር ይደርስብኛል የሚል ስሜት ተጠናውቶኝ ነበር። ይህንን ሁኔታ በፍፁም ልቆጣጠረው ስላልቻልኩኝ ወደ ቅርብ አለቃዬ ወደ ሚስተር ግሬሰን ሄጄ በጣም የፍርሃትና የጭንቀት ስሜት እንደተሰማኝና የከሰል ቁፉሮ የሚካሄድበትን የዋሻው ክፍል ራሱ አደጋ የሚደርስብኝ ስለመሰለኝ መሥራት እንዳቃተኝ ነገርኩት። እሱም አብሮኝ መጣና ውስጡን እና ውጪውን አየት አየት ካደረገ በኋላ "ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም መጥፎ ነገር ወደ አይምሮህ ያመጣህ አትፍራ ስራህን ስራ" ብሎኝ ሄደ። ሥራዬን ማከናወን ቀጠልኩ። ከዚያ ወዲያ ምናልባት ለሁለት ሰዓት ያህል ብሠራ ነው ድንገት መውጣት እንኳን በማልችልበት ሁኔታ የምሠራበት ክፍል በላዬ ተደረመሠና ነገሩ ሁሉ ወደ ጭለማ ተለወጠ። ወዲያውኑ ትልቅ የብረት በር ተከፍቶ በበሩ በኩል ያለፍኩ ይመስለኛል። በሃሳቤም ሞቼ ወደሌላ ዓለም የሄድኩንኝ ይመስለኛል ምክንያቱም ማንንም አላይም የማንንም ድምፅ አልሰማም ነበር።
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
48 ሰአት በሲዖል (እውነተኛ ታሪክ) በጆን ደብልዩ ሬይኖልድስ ክፍል 3 መሞቱን አረጋግጦ የነበረው የእስር ቤቱ ሐኪም ከሰላሣ ደቂቃ በኋላ በስፍራው ሲደርስ የሞተው ሰውዬ ውሃ ስጡኝ ብሎ ጠይቆ እየጠጣ ነበር። ሐኪሙም ወዲያውኑ ሰውዬው የተገነዘበተበትን ልብስ አስወግደው ሌላ የእስረኛ ልብስ እንዲያለብሱት አዘዘና የተዘጋጀውን የሬሳ ሣጥን ሌላ ሰው እንዲቀበርበት ተደርጎ እሱን እንደገና ለምርመራ ወደ ሆስፒታል ላከው። አደጋ ካጋጠመበት ስፍራ ወጥቶ ምርመራ በተደረገለት ጊዜ በምርመራው ውጤት ላይ አንደኛው እግሩ ሁለት ቦታ ተሰብሮ እንደነበር በሃኪሙ ተረጋግጦ ስለነበር ከዚህ የተነሳ በሆስፒታሉ ውስጥ ተኝቶ እንዲታከም ታዘዘና ለስድስት ወራት ያህል ተኝቶ በህክምና ሲረዳ ከቆየ በኋላ ሙሉ በሙሉ ፍፁም ጤነኛ ሆኖ ድኖ ወደዚያው በፊት ይሠራ ወደ ነበረው ማዕድን ፍለጋ ቁፋሮ ተግባሩ ተመልሶ መስራቱን ቀጠለ። እኔም ይህንን አስገራሚ ታሪክ ማለትም ስለዚህ ከሞተ በኋላ ድኖ ወደ ስራው ስለ ተመለሰው ሰው ታሪክ የቅርብ ጓደኛው ሲነግረኝ በነገሩ በጣም ስለ ተደነቅሁ ይህንን ተአምር ከሰማሁበት ቀን ጀምሮ ባለታሪኩን ለመተዋወቅና የተፈጠረውን ሁኔታ እንዴት እንደነበር ከራሱ አንደበት ለመስማት ናፈቅሁ። ግን ለብዙ ወራቶች አልሳካ አለኝ። በመጨረሻም ሁኔታዎች እንዲሳካልኝ ፈቀዱ። በአጋጣሚ የዚህ የከሠል ማዕድን ፍለጋ ስራ በተጠናቀቀ ጊዜ እኔ ወደዚሁ ክፍል በመሄድ አመታዊ ሪፖርቱን እንዳዘጋጅ ስታዘዝ እጅግ በጣም ደስ አለኝ። ይህንኑ ፅኑ ፍላጎቴን የተረዱ ሰዎች የተባለውን ሰው በቢሮዬ በኩል ሲያልፍ አሳዩኝና ተገናኝተን ሰላምታ ተለዋወጥን። እኔም ላናግረው እንደምፈልግ ስጠይቀው ፈቃደኝነቱን ገለፀልኝ።
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
48 ሰአት በሲዖል (እውነተኛ ታሪክ) በጆን ደብልዩ ሬይኖልድስ ክፍል 2 በጣም በመደናገጥ ሕይወቱን ለማትረፍ በፍጥነት ቁፋሮ ማካሄድ ተጀመረ። በመጨረሻ በላዩ ላይ የተጫነውን ፍርስራሽ ካስወገዱለት በኃላ በጥንቃቄ ቢያወጡትም ምንም የህይወት እስትንፋስ ምልክት አይታይበትም ነበርና ፈጥነው ለምርመራ በቃሬዛ ይዘው ወደ እስር ቤቱ ሐኪም ወሰዱት። ሐኪሙም በሕክምና ጥበቡ ተጠቅሞ ብዙ ምርመራ ካደረገለት በኃላ በመጨረሻ መሞቱን በማረጋገጥ ወደ ሆስፒታል አስተላለፈው። በማግስቱም በሆስፒታሉ ውስጥ ታጥቦ እና ተገንዞ ለቀብር ተዘጋጀ። በቀብሩ እለት አንድ ካህን መጥተው የመጨረሻ ፀሎተ ፍታት ካደረጉለት በኃላ የቀብር ሥነ ሥርዓት ሊፈፀም ተቃረበ። ለዚህም ሁለት እስረኞች አስከሬኑን ከተቀመጠበት ቦታ ወስደው በተቀመጠበት ቦታ ወስደው በተዘጋጀው የሬሳ ሣጥን ውስጥ እንዲያኖሩት በሆስፒታሉ የጤና ተጠሪ ትዕዛዝ ደርሷቸው ስለነበር በታዘዙት መሠረት አስክሬኑን አንደኛው እስረኛ ከራስጌ ሌላው በግርጌ በኩል ይዘው በመሄድ ላይ እያሉ አስክሬኑን ከራስጌ በኩል የያዘው እስረኛ በሆነ ነገር ተደናቅፎ ተንገዳገደ ፤ በዚህ ጊዜ የሰውነቱን ሚዛን መጠበቅ ስላልቻለ አስክሬኑን አመለጠውና በወለሉ ላይ አረፈ። በስፍራው የነበሩት ሰዎች በሁኔታው ተገርመው እየተመለከቱ እያለ ሌላ አስገራሚ ነገር ተፈጠረ። ድምፅ ከሬሳው ውስጥ ተሰማ። ኡ .....ህ የሚል ከባድ ድምፅ ፤ ወዲያውም እንቅስቃሴ ቀጠለ። እንደገና ሁሉም ተደናገጡና በፍጥነት ሐኪም እንዲጠራ ተደረገ።
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
48 ሰአት በሲዖል (እውነተኛ ታሪክ) በጆን ደብልዩ ሬይኖልድስ የተፃፈ ክፍል 1 እጅግ በጣም ከሚያስገርሙኝ ታሪኮች ውስጥ ዋነኛ ሆኖ ምንጊዜም የማልረሳው ብዙ ቁም ነገር ያስጨበጠኝ በአሜሪካን ሀገር በምትገኝ በጄፈርሰን ከተማ ይኖር የነበረውና በዚያን ጊዜ በአደገኛ የፈረስ ሌብነቱ ይታወቅ የነበረው የጆርጅ ሊኖክስ ታሪክ ነው። ይህ ሰው ጥፉቱን እየደጋገመው ስለመጣ በዚሁ በፈረሶች ስርቆት ወንጀል ክስ ቀርቦበት የሴጅዊክ ከተማ ፍርድ ቤት በእስራት እንዲቀጣ ላከው። በእስር ላይ እያለ በከሰል ማዕድን ፍለጋ ክፍል ሥራ ላይ ተመድቦ እንዲሠራ ተደረገ በ1887 እና 1888 ጊዜው ቀዝቃዛ የክረምት ወራት ነበረ። አንድ ቀን ግን የማያውቀው እንግዳ ስሜት ተሰማውና ተረበሸ። ምናልባት ይህ የሚሠራበት ስፍራ አደጋ ሊያደርስበት የሚችል መስሎት ፍርሃትና ስጋት ስለመጣበት ይህንኑ ሥጋቱን ወደ ቅርብ አለቃው መጥቶ ሊነግራቸው ተገደደ። አለቃውም በተነገራቸው መሠረት ወደ ሚሠራበት ስፍራ መጥተው ተዘዋውረው ካዩ በኋላ ምንም የሚያሠጋ ነገር እንደሌለና አስተማማኝ መሆኑን ነግረውት ወደ ሥራው እንዲመለስ አዘዙት። ትዕዛዙን ተቀብሎ ወደ ሁለት ሰዓት ያህል ከሰራ በኋላ እንደፈራው የሚሠራበት ክፍል በላዩ ላይ በድንገት ተደረመሰና ሙሉ ለሙሉ ቀበረው። ይህ አደጋ ሲደርስበት ደግሞ ማንም ያየ ወይም በስፍራው የነበረ ሰው ስላልነበር እርዳታ እንኳን ሳያገኝ ለሁለት ሰዓታት ያህል እንደተቀበረ ቆየ። በዕለቱ በምሳ ሰዓት ላይ በመመገቢያው አዳራሽ ውስጥ በስፍራው ስላልነበር የእሱን አለመኖር የተረዱ የእስረኞች ኃላፊዎች ፍለጋ ለማካሄድ ወደሚሠራበት ቦታ ሲሄዱ አካባቢው ተቀይሮ በፍርስራሽ ተሞልቶ አገኙ።
Mostrar todo...
የአጫጭር መጣጥፎች መድብል 📔ርዕስ፦ የትሩፋን ናፍቆት 👤ደራሲ፦ሰሎሞን አበበ ገብረ መድኅን 📑የገጽ ብዛት፦264 💾መጠን፦6.1MB የደራሲው ሌሎች ስራዎች፦ "የደነበረው በቅሎ" የአስተምሮ "ልጓም" ይሻል ❤️❤️❤️መልካም እለተ ሰንበት!!❤️❤️❤️
Mostrar todo...
. "የብርሃን አንጓዎች" ✍ጸሐፊ፦ ጳውሎስ ፈቃዱ Source @LeulLemaPulpit
Mostrar todo...
📔ርዕስ፦የማይደገም ጉዞ 👤ደራሲ፦ ቢሊ ግርሃም 🗣ተርጓሚ፦ ቁምላቸው ፋንታሁን
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
ጥሩ መጽሐፍ ስለመላእከ። 📔ርዕስ፦ መላእክት 👤ደራሲ፦ ቢሊ ግርሃም 🗣ተርጓሚ፦ ይገረም ረታ
Mostrar todo...