cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ትቅደም

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
284
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
+130 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

00:58
Video unavailableShow in Telegram
ነገስታቱ በብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ያምኑ ነበር
Mostrar todo...
VID_20231001_200223.mp43.63 MB
Photo unavailableShow in Telegram
11:17
Video unavailableShow in Telegram
VID_20230928_093247.mp434.51 MB
01:20
Video unavailableShow in Telegram
VID_20230926_101317.mp43.45 MB
👍 1
03:14
Video unavailableShow in Telegram
VID_20230905_063553.mp46.70 MB
Photo unavailableShow in Telegram
እንዲህ አይነት የቀን መቁጠሪያ አሰንደነበረን ያውቁ ኖሯል?
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
ሃገራችን ካበቀለቻቸው ጀግኖች ውስጥ አንዱ ደጃዝማች ዘውዴ ጥላሁን፣ ልጃቸው ከነገረኝና ከሰሯቸው ጀብዱዎች ውስጥ እሳቸው ወደነበሩበት ፊት ለፊት ቦንብ እየጣለ ይመጣ የነበረውን የፋሽስት ጣልያንን የጦር አውሮፕላን ሳይሸሹ በኦርሊኮን መትረየስ ጥይት አርከፍከውበት በቅርብ ርቀት ወድቆ ሲፈነዳ አፈር ያለብሳቸውና እንደሞቱ ተቆጠረ፣ አርበኞች ጓደኞቻቸው ግን አስክሬኑን ቤተክርስቲያን ሳንቀብር ሜዳ ላይ ጥለን አንሄድም ብለው ቆፍረው ቢያወጧቸው ቆስለው ግን በህይወት አገኟቸው። የእኝህ ታላቅ አርበኛ ታሪክ ብዙ ነው። ቤተሰብ እንደመሆናቸው ስለክብራቸው በተወሰነ መልኩ በአጭሩ ታሪካቸውን በመፅሃፌ አንድ ልዩ ምዕራፍ ሰጥቼ አቀርባለሁ ብዬ እያሰብኩ ነው፣ ሙሉውን የህይወት ታሪካቸውን ግን ለልጆቻቸው እንዲፅፉት አሳስቤ ለእነሱ እለቃለሁ። የደጃዝማች ዘውዴ ቤተሰብ ሰፊ የጀግኖችና የምሁራን አዳራሽ ነው። ከ ብሩክ ሰይፉ ገፅ
Mostrar todo...
00:25
Video unavailableShow in Telegram
VID_20230818_083925.mp44.51 KB
ተከታዮቼን አትንኩ! * ሐምሌ 22 ቀን እንዲህ ሆነ #Ethiopia | ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም የኢትዮጵያ ታላቅ የሀይማኖት አባት ሀገር ወዳዱ የነፃነት አርበኛ አቡነ ጴጥሮስ ሠማዕትነትን የተቀበሉበት ቀን ናት። «እኔ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ። ኃላፊነትም ያለብኝ የቤተ ክርስቲያን አባት ነኝ። ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ። ከዚህ በቀር ለእናንተ ችሎት የማቀርበው ነገር የለኝም። ለፈጣሪዬ ብቻ የምናገረውን እናገራለሁ። እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ። ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ። ግን ተከታዮቼን አትንኩ።» የአቡነ ጴጥሮስ ሰማዕት (ኢትዮጵያዊ) በረከት ይደርብን *** ዝክረ ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ #Ethiopia | አቡነ ጴጥሮስ ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ በጠላት የጥይት እሩምታ እስከተገደሉበት ጊዜ ድረስ የነበረውን ሂደት 'ኮርየር ዴላሴራ' (corriere della sera) የተባለው ጋዜጣ ወኪል እና የምሥራቅ አፍሪካ ዜና መዋዕል አዘጋጅ የነበረው 'ፖጃሌ' የተባለ ጋዜጠኛ እ.ኤ.አ. ሰኔ 15 ቀን 1936 ዓም አዲስ አበባ በነበረ ጊዜ ሂደቱን ባየውና በተመለከተው መንገድ እንደሚከተለው ጽሑፍ አቅርቦ ነበር። "ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቁመታቸው ረዘም ፊታቸውም ዘለግ ያለና መልካቸው ጠየም ያለ ዐዋቂነታቸውና ትሕትናቸው ከገጻቸው የሚነበብ ሲሆን በዚህ ጊዜ ለብሰውት የነበረው ልብሰ ጵጵስና ጥቁር ካባ ያውም በጭቃ የተበከለ ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ችሎት ቀረቡ፡፡ ለፍርድም የተሠየሙት ዳኞች ሦስት ሲሆኑ እነዚህም ጣሊያኖችና የጦር ሹማምንት ናቸው፡፡ የመካከለኛው ዳኛ ኮሎኔል ነበር፡፡ የቀረበባቸውም ወንጀል 'ሕዝብ ቀስቅሰዋል፣ ራስዎም ዐምፀዋል፣ ሌሎችንም አንዲያምፁ አድርገዋል' የሚል ነበር፡፡ ዳኛውም 'ካህናቱም ሆኑ የቤተ ከህነት ባለሥልጣኖች ሊዳኛውም 'ካህናቱም ሆኑ የቤተ ከህነት ባለሥልጣኖች ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስም የኢጣሊያንን መንግሥት ገዢነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ አርስዎ ለምን ዐመፁ፣ ለምን ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑ?' ሲል ጠየቃቸው ፡፡ አቡነ ጴጥሮስም የሚከተለውን መልስ መለሱ... “አቡነ ቄርሎስ ግብፃዊ ናቸው፣ ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የሚገዳቸው ነገር የለም፡፡ አኔ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ፡፡ሐላፊነትም ያለብኝ የቤተ ከርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ከርስቲያኔ አቆረቆራለሁ፡፡ ከዚህ በቀር ለእናንተ ችሎት የማቀርበው ነገር የለኝም፡፡ ለፈጣረዬ ብቻ የምናገረውን አናገራለሁ፡፡ እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ ዐውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ” አሉ፡፡ ይህንንም ብለው በጥይት ተደብድበው ሲገደሉ እንዲያይ ተጋብዞ ለተሰበሰበው ሕዝብ የሚከተለውን ሕያው መልእከት አስተላለፉ፡፡ ''አረማዊ የሆነው የፋሺስት መንግሥት ቤተክርስቲያንን ለማቃጠል፣ ሕዝበ ክርስቲያንን ለመግደል፣ ሃይማኖትን ለማጥፋት፣ ታሪካችንን ለማበላሸት የመጣ ነው፡ እንጂ በጎ ለመሥራት፣ እውነተኛ ፍርድ ለመስጠት ስላልመጣ ለዚህ ለግፈኛ አትገዙ፡፡ ስለ ውድ ሀገራችሁ፣ ስለ ቀናች ሃይማኖታችሁ ተከላከሉ።ነጸነታችሁን ከሚረክስ ሙታቹህ ስማችሁ ሲቀደስ ታላቅ ዋጋ ያለው ክብር ታገኛላችሁ። የኢትዮጵያ ህዝብ ለዚህ ለጠላት እንዳይገዛ አውግዣለሁ፤ የኢትዮጵያ መሬት ጠላትን ብትቀበል የተረገመች ትሁን። በፈጣሪየ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተገዘተች ትሁን።'' ጋዜጠኛው ይቀጥላል “እኒህ ጳጳስ ሐቀኛ ነበሩ። ነገር ግን ለኢጣሊያ ለጋስዮን ታዝዞ የመጣው አስተርጓሚ ዳኞች የሚሉትን ብቻ ከማስተርጎም በቀር ጳጳሱ የሚናገሩትን ሃቀኛ ንግግር አላስተረጎመም፡፡ እኔ እንኳን የሰማሁት በአዲስ አበበ ለሠላሳ ዓመት የኖረው የእቴጌ ሆቴል ኃላፊ የነበረው የግሪክ ዜጋ ማንድራኮስ አጠገቢ ተቀምጦ ስለ ነበር የተናገሩትን ሁሉ ስለ ገለጠልኝ ነው፡፡ እኔ እንደ ሰማሁት ፍርዱን ለመስማት በብዛት የተስበስቡት ጣሊያኖችና ታዝዞ የወጣው የአዲስ አበበ ሕዝብ ሐቀኛ የሆነውን ንግግራቸውን ቢሰማ ኖሮ ልባቸው ይነካ ነበር"። ሞት የተፈረደባቸው ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በችሎት ፊት ለብዙ ሰዓታት ቆመው ስለዋሉና ደክሟቸው ስለነበር ለመቀመጥ ፈልገው ዳኛውን በትሕትናና በፈገግታ ጠየቁት። እንዲቀመጡም ፈቀደላቸው፣በመጨረሻም የሞታቸው ፍርድ ከተነበበ በኋላ የፈረዱባቸውን ዳኞች ጸልየው በመስቀላቸው ባረኳቸው።ብፁዕነታቸው እስከ መቃብር አፋፍ ድረስ የፍርሃትና የድንጋጤ ምልክት ያይደለ ከልብ ፍጹም ቆራጥነት ይታይባቸው ነበር።” ምንጭ፡ ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን *** አቡነ ጴጥሮስ የተሰዎት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም ነው። ታላቁ ባለቅኔና የተውኔት አዘጋጅ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን ዘመን ተሻጋሪ የሆነችውን “ጴጥሮስ ያችን ሰዓት” የምትለዋን ግጥም የፃፈው አንድ ቀን ምሽት ከማዘጋጃ ቤት ሲወጣ ባየው ትዕይንት ምክንያት ነበር። ነገሩ እንዲህ ነው … ጸጋዬ ገ/መድህን ከማዘጋጃ ቤት እንደወጣ ቁልቁል ወደ አቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ሲያመራ አንድ ጀብራሬ (በሎሬቱ አነጋገር) ከአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ላይ ሸንቱን ሲሸና ተመለከተ። ጸጋዬም በደም ፍላት ወደ ጀብራሬው ተንደረደረ። ጀብራሬው ግን “አንተ ድንጋይ እሸናብሃለሁ። ድንጋይ ነህ… ድንጋይ ነህ...” እያለ በሐውልቱ ላይ ይሸናል። በዚህ ሰዓት ነበር ሎሬቱ “ጴጥሮስ ድንጋይ አይደለም!”ብሎ ጀብራሬውን በደም ፍላት ዘሎ ያነቀው። ከዚያም አብረውት የነበሩት ሰዎች ገላገሉትና እየተብሰከሰከ አራት ኪሎን ተሻግሮ ቀበና ገባ። ማታውን አልተኛም እነሆ “ጴጥሮስ ያችን ሰዓት” የምትለዋን ግጥምና ኑዛዜ ሲጭር አደረ።
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.