cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegaciĂłn. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Generation of Revival🙏ኢትዮጵያ 🙏የሪቫይቫል ትውልድ🔥🔥Ethiopia 🔥🙏🙏🙏🙏

#በአዳማ ከተማ ላይ ያሉ ወጣቶች ሁሉ ሪቫይቫልን የተራቡና የተጠሙ ሁሉ ተገናኝተው የሚፀልዩበት እና በአንድ ልብ የምንጮህበት Group:: 🇪🇷🇪🇹 #ሐዋ 2 🇪🇷🇪🇹 ¹⁷ እግዚአብሔር ይላል፦ በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌ https://t.me/revivaleAdama

Mostrar mĂĄs
Publicaciones publicitarias
346
Suscriptores
Sin datos24 horas
-37 dĂ­as
-830 dĂ­as

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

Photo unavailableShow in Telegram
This sunday⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
በአሁኑ እሁድ
ነገ አይቀርም 💥💥💥
Mostrar todo...
❤ 1🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
This sunday በአሁኑ እሁድ
Mostrar todo...
🔥 3👎 2👍 1🥰 1
ዝሆን ምን እንደሚመስል ለመረዳት ስለ ሞከሩ አራት ዓይነ ስውራን የሚናገር አንድ ታሪክ አለ። ወደ ጫካ ገቡና ዝሆኑ ወዳለበት ደረሱ፤ አንደኛው ኩምቢውን ዳሰሰ፥ እንዱ እግሩን ዳሰሰ፥ ሌላኛው ጐኑን የመጨረሻው ደግሞ ጭራውን ዳሰሰ። ከዚያ በኋላ ዝሆን ምን እንደሚመስል እያንዳንዳቸው ለሌላ ሰው መግለጫ ለመስጠት ሞክሩ። ዝሆን ምን እንደሚመስል ሲናገሩ የመጀመሪያው ዝሆን እንደ ትልቅ የውኃ ማስተላለፊያ ቧንቧ ነው አለ። ሁለተኛው ዝሆን እንደ ትልቅ ግንድ ነው እለ። ሦስተኛው ደግሞ የቤት ግድግዳ ነው የሚመስለው ሲል፥ የመጨረሻው አለንጋን ይመስላል አለ። አራቱም ዓይነ ስውራን የተናገሩት በእነርሱ እምነት ያቀረቡት እውነታኛና ትክክለኛ መግለጫ ነው ብለው ያመኑበትን ነገር ነው። ሆኖም ግን እያንዳንዳቸው የተረዱት ከፊል እውነት ስለነበር ለሌሎች ያቀረቡት ሙሉ እውነት ያልያዘና ሰዎችን ወደተሳሳተ አመለካከት የሚመራ ነበር።  ማናችንም ብንሆን ስለ እውነት ፍጹም የሆነ መረዳት እንደሌለን መገንዘብ ይገባናል። የእግዚአብሔር ዘላለማዊ እውነት የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ ፊት ለፊታችን ቢኖረንም እንኳ እንደ እራቱ ዓይነ ስውራን ከፊል እውነትን ብቻ እናያለን። በዓለም ላይ የሚገኙ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ክርስቲያኖች ሁሉ የሚያጠኑት አንድ መጽሐፍ ቅዱስ ቢሆንም እንኳ እንዳንድ ክፍሎችን በተለያየ መንገድ የሚረዱት በዚህ ምክንያት ነው። የመጀመሪያው ምእተ ዓመት ታላቅ የሥነመለኮት አስተማሪ የነበረው ጳውሎስ እንኳ ይህን እውነት ተቀብሏል። «ዛሬስ በመስተዋት በድንግዝግዝ እንደምናይ ነን በዚያን ጊዜ ግን ፊት ለፊት እናያለን፤ ዛሬስ ከእውቀት ከፍዬ አውቃለሁ በዚያን ጊዜ ግን እኔ ደግሞ እንደ ታወቅሁ አውቃለሁ» (1ኛ ቆሮ. 13፡12)።
Mostrar todo...
ህይወትህን ለውጥ ቅዱሱ መጽሐፍ በሚለውጥ ቃል በተለወጡ የሰዎች ህይወት እና በሚለውጠው መንፈስ ቅዱስ የተሞላ ነው። hallelujah አሁን ህይወትህን መለወጥ ጀምር ከ ጨለማ ወደ ብርሃን, ከ አሳ አጥማጅነት ወደ ሰው አጥማጅነት,ከ እረኝነት ወደ ንጉስነት, ከ ሀሰት ተናጋሪ ወደ እውነት ሰባኪነት, ከ ሃጥያት ሰሪነት ወደ ቅድስና ህይወት, ከድህነት ወደ ብልጽግና, ከታማሚነት ወደ ፍጹም ጤንነት, ከተዋረደ ህይወት ወደ ከበር ህይወት ማምጣት ,መጎተት ,መቀየር የሚችል ቅዱስ ቃል በእጅህ ላይ ይዘህ ቁጭ ብለህ አትቅር ተለወጥ!! እእእእ እቺን እማ ሳልነግርህ አላልፈም አይደለም ሰው አህያ ተለውጣ ያየኀው መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ነው. ልብስ ተነጥፎላት ንጉስ ተሸክማ ስቴድ ያነበብከው..
የተለወጠች አህያ መጽሐፍ ቅድስ ላይ ነው የለችው.
እንድታይ የፈለኩት የመጽሐፉ ቅድስን ታላቅነት ነው። መጽሐፍ ቅድስን እየኖርክ አለመለወጥ ነው የማይቻለው። ከ ላይ የፃፍኩትን ላስታውስ።
ቅዱሱ መጽሐፍ በሚለውጥ ቃል በተለወጡ የሰዎች ህይወት እና በሚለውጠው መንፈስ ቅዱስ የተሞላ ነው። ሃሌሉያየየየየየ
...... be inwardly transformed by the Holy Spirit through a total reformation of how you think..... Romans 12:2 TPT ....በአእምሯችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ሮሜ 12:2 NASV
ህይወትህን በ ቃሉ ለውጠው Be transformed by the word of God
Mostrar todo...
🔥 1