es
Feedback
ሊብሮ ስፖርት - Libro sport

ሊብሮ ስፖርት - Libro sport

Ir al canal en Telegram

Always Ethiopian sport አስተያየት👉 @Libro_sport_bot Advertisement👉 @Abdul_Feta_lke GROUP👉 @Libro_sport_GROUP

Mostrar más
El país no está especificadoLa categoría no está especificada
1 639
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
ዛሬ እለተ ቅዳሜ በሀገራችን የእግርኳስ ዝውውር መስኮት የደረሰንን መረጃ እነሆ! ═════════════════════════ ⚔️ ሀብታሙ ተከስተ || ድርድር እያደረገ ይገኛል 🤝 በፋሲል ከነማ ቤት ዉላቸዉን ከሚጨርሱት መካከል አንዱ የሆነዉ ሀብታሙ ተክስተ በገንዘብ ዙሪያ እየተደራደረ ይገኛል ፤ እርሱን ለማስፈረም ባህርዳር ከነማዎች ብርቱ ፉክክር ላይ ሲሆኑ ሌሎች ፈላጊዎችም ሊፈጠሩ ይችላሉ ተብሏል። ትልቅ ገንዘብ የሚያቀርብለት ክለብ እንደሚያስፈርመዉ እርግጥ ነዉ! ═════════════════════════ ብሩክ በየነ ዛሬ ቢሮ ይገባል ...... ⏳ ስሙ በተደጋጋሚ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ተያይዞ ከጊዮርጊስ ጋር የተስማማዉ ብሩክ በየነ ዛሬ ከጊዮርጊስ ቦርድ ጋር ይገናኛል ፤ ተጫዋቹ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጥሪ የተደረገለት ሲሆን ወደ ፌድሬሽን ከማምራቱ በፊት ይገናኛሉ ተብሏል። ተጫዋቹን ትላልቅ የጊዮርጊስ ሰዎች አነጋግረዉ ያስማሙት ሲሆን ዛሬ በገንዘብ ዙሪያ ተነጋግረዉ ፊርማዉን ያኖራል ተብሏል። በገንዘብ ሁኔታ የማይስማማ ከሆነ ግን ኢትዮጵያ ቡናዎች ልጁን ለማምጣት የተቻላቸዉን ጥረት እያደረጉ ነዉ። ልጁ ፊርማዉን ከሰአት የሚያኖር ሲሆን ከጊዮርጊስ አባላት ጋር በሚፈልገዉ ገንዘብ ላይ መስማማት ልጁን ወዲያዉኑ እንዲፈርም ያስችለዋል ነገር ግን ይህ የማይሆን ከሆነ ልጁ ዳግም ስሙ ቀድሞ ወደ ተያያዘበት ኢትዮጵያ ቡና ሊያመራም ይችላል። በሉ እንግዲህ የኢትዮጵያ ቡና እና ጊዮርጊስ ቦርድ አባላት ነገሩን ጨርሱት!! ሁሉም ነገር ያለዉ በጊዮርጊስ ቦርድ እጅ ላይ ነዉ!! ═════════════════════════ ቀጠሮ ተይዟል || ሱራፌል እና በረከት ሱራፌል ዳኛቸዉ ከዉጪ ክለብ ጋር ለመነጋገር ቢሞክርም ሳይስማሙ ቀርተዋል ስለዚህም የፋሲል ቦርድ አባላት ተገናኝተዉ ነገሩን ይጨርሱታል ተብሏል ፤ ተጫዋቹም ወደ ዉጪ ካልሆነ በስተቀር የመዉጣት አዝማሚያ የለዉም። በረከት ደስታን ለማስፈረም መከላከያዎች የእርሱ ወኪል ወደሆነዉ ያሬድ እስከ አዳማ ሄደዉ ያወሩት ቢሆንም መጀመሪያ የፋሲልን ነገር ያስቀድማል ፤ ፋሲሎች ከተጫዋቹ ጋር መግባባት ካልቻሉ መከላከያዎች አድፍጠዉ እየጠበቁት ነዉ። ═════════════════════════ ⚔️ ካሳየ ወይስ ቲጋና || የፋሲል ከነማ ቦርድ ክፍፍል..... የፋሲል ከነማ ቦርድ አባላት በቀጣዩ አሰልጣኝ ጉዳይ ለሁለት ተከፍለዋል ፤ ግማሹ የሀይሉ ነጋሽ ( ቲጋና )ቆይታ የወደዱ ሲሆኑ ሌላኞቹ ደግሞ የካሳየ አራጌን መምጣት የሚደግፉ ናቸዉ ። ከክለቡ 17 ተጫዋቾች ዉል የጨረሱ ሲሆን በብዛት ከሌሎች ክለቦች ጋር ንግግር እያደረጉ መሆኑ ለፋሲሎች መልካም ዜና አይመስልም። ═════════════════════════ መስፍን ታፈሰ || ዛሬ ዉሳኔ ያገኛል ⚡️ ልጁ ከትናንት በስቲያ ወደ ኢትዮጵያ ቡና አምርቶ ነበር ግን በብር ምክንያት አልተስማሙም ከዚያ በኋላ መከላከያ እና ባህርዳሮች ከኢትዮጵያ ቡና የተሻለ ገንዘብ ሰጥተዉታል ነገር ግን ኢትዮጵያ ቡናዎች ድጋሚ ለመስፍን ደዉለዉ የተሻሻለ ክፊያ አቅርበዉለት ዛሬ ከሰአት በኢትዮጵያ ቡና ቦርድ ይወሰናል። ═════════════════════════ በዛብህ መለዮ || መልሱ ይጠበቃል ⚡️ የፋሲሉ የመሃል ሜዳ ተጫዋች በዛብህ መለዮ የክለቦችን ትኩረት ስቧል ፤ ተጫዋቹ ከባህርዳር ሰዎች ጋር ከትናንት በስቲያ ንግግር እንዳደረገ ሲነገር ድሬዳዋዎችም እንዲሁ የእርሱ ፈልጊ በመሆን መልሱን እየጠበቁት ሲሆን ሌሎች ክለቦችም የልጁ ፈላጊ ናቸዉ። በዛብህ መለዮ የሚወስነዉ ዉሳኔ የሚጠበቅ ይሆናል። ═════════════════════════ መረጃውን ያደረሰን ባልደረባችን Yonas amare ነው! | @Libro_sport_GROUP | @Libro_sport @Abdul_feta_lke

የዝውውር መስኮቱ በተከፈተ በመጀመሪያ ቀን የወጡ አስገራሚ የዝውውር ዜናዎች! _ #የተረጋገጠ || ሀይሌሚካኤል አደፍርስ ቡና ደርሷል!! ከትናንት በስቲያ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ከስምምነት ደርሶ የነበረዉ የሰበታዉ የመስመር ተመላላሽ ቼረ የኢትዮጵያ ቡና ንብረት ሆኗል። ___ #የተረጋገጠ || አብዱልሀፊዝ ቶፊቅ የቡና ንብረት የሰበታዉ ተጫዋች አብዱልሀፊዝ ቶፊቅ የኢትዮጵያ ቡና ንብረት መሆኑ ተረጋግጧል። _ የሚቀረዉ ፊርማ ብቻ ነዉ!! ኢትዮጵያ ቡና አዲሱ አሰልጣኝ ተመስገን ዳና እንደሚሆን እርግጥ ነዉ ፤ አሁን የፈረሙት ተጫዋቾችም የአሰልጣኙ ምርጫ ናቸዉ ፊርማዉን በቀጣይነት አኑሮ የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ ይሆናል። __ ወጣቱ ጥበበኛ አብዱልከሪም ወርቁ ኢትዮጵያ ቡናን ተቀላቅሏል ፤ ኢትዮጵያ ቡና ይህንን ሁሉ ዝዉዉር እያደረገ ያለዉ በአሰልጣኝ ተመስገን ዳና መሪነት ነዉ !! ___ ⏳እንየዉ ካሳሁን ወደ ቀድሞ ቤቱ ሊመለስ ነዉ.... ፋሲል ከነማ የድሬዳዋዉን የመስመር ተመላላሽ እንየዉ ካሳሁንን ለማስፈረም ተቃርቧል ፤ ተጫዋቹን ወደ ቀድሞ ክለቡ ለመመለስ እየተነጋገሩ ሲሆን እስካሁን መልካም ደረጃ ላይ ናቸዉ ። __ ወደ ዉጪ ሀገር ለመሄድ ከጫፍ ደርሷል!! 🤝 የኢትዮጵያ ቡናዉ የመሃል ስፍራ ተጫዋች አማኑኤል ዮሐንስ ወደ ግብጽ ሊያመራ ንግግር እያደረገ ይገኛል ፤ ተጫዋቹ ከኢትዮጵያ ቡና ለመልቀቅ ከወሰኑ ተጫዋቾችም አንዱ ነዉ ። __ 🗣 ንግግር ላይ ናቸዉ 🤝 የባህርዳሩ የፊት መስመር ተጫዋች ፍጹም አለሙ በአሰልጣኝ ገ/መድህን ሀይሌዉ መድን ኢትዮጵያ ለማምራት ንግግር ላይ ናቸዉ። __ ሻምፒዮኖቹ ቅዱስ ጊዮርጊሶች የከነማዉን ጥበበኛ ብሩክ በየነን አስፈርመዉታል ፤ ተጫዋቹ በአዲሱ ክለብ የሰባት ቁጥር ማለያን የሚለብስ ሲሆን የክለቡ ሁለተኛ ፈራሚ በመሆን ክለቡን ተቀላቅሏል። እርሱን ተከትሎ ቡልቻ ሹራ ከክለቡ ጋር ተለያይቷል ለዛም ነዉ ሰባተ ቁጥር የወሰደዉ🤝 _ 🤝 በስምምነት ተለያይተዋል !! ከሰበታ ቅዱስ ጊዮረጊስን ተቀላቅሎ በግሉ ያልተሳካ የዉድድር አመትን ያሳለፈዉ ቡልቻ ሹራ ከክለቡ ጋር በስምምነት ተለያይቷል ። ___ ℎ𝑒𝑟𝑒 𝑤𝑒 𝑔𝑜!! || ረመዳን የሱፍ ቅዱስ ጊዮርጊስን ተቀላቅሏል!! ⚡️ የወልቂጤ ከነማዉ የመስመር ተመላላሽ ረመዳን የሱፍ ጊዮርጊስን ተቀላቅሏል ፤ ተጫዋቹን ገና በሁለተኛዉ ዙር አዉርተዉ የነበረ ሲሆን አሁን ደግሞ የግላቸዉ አድርገዉታል ተብሏል። _ መረጃውን ያደረሰን ባልደረባችን Yonas amare ነው! | @Libro_sport_GROUP | @Libro_sport @Abdul_feta_lke

የአማራ ክልል አስተዳዳሪ ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) የባህርዳር ስታድየምን በፍጥነት እናጠናቅቃለን ብለዋል። ከክልሉ መሪዎች ጋርም ጎብኝተዋል። ለአህጉርና አለም አቀፍ ጨዋታዎች እናደርሳለን ብለዋል።[ሀብ
የአማራ ክልል አስተዳዳሪ ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) የባህርዳር ስታድየምን በፍጥነት እናጠናቅቃለን ብለዋል። ከክልሉ መሪዎች ጋርም ጎብኝተዋል። ለአህጉርና አለም አቀፍ ጨዋታዎች እናደርሳለን ብለዋል።[ሀብታሙ ካሴ]

ሲናፈስ የነበረው የካሳዬ አራጌ ከኢትዮጵያ ቡና መልቀቅ እውን ሆኗል! ካሳዬ አራጌ እና ኢትዮጵያ ቡና ከ3 አመት ቆይታ በኋላ ግንኙነታቸው ተደምድሟል! ሰሞኑን ሲናፈስ የነበረው ዜና ዛሬ በይፋ ሲረጋገ
ሲናፈስ የነበረው የካሳዬ አራጌ ከኢትዮጵያ ቡና መልቀቅ እውን ሆኗል! ካሳዬ አራጌ እና ኢትዮጵያ ቡና ከ3 አመት ቆይታ በኋላ ግንኙነታቸው ተደምድሟል! ሰሞኑን ሲናፈስ የነበረው ዜና ዛሬ በይፋ ሲረጋገጥ የክለቡ ስራ አስካያጅ አቶ ገዛኅኝ ወልዴ አዲስ አሰልጣኝ በቅርብ ይፋ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል!

የኢትዮጵያ መድህን ድርጅት ወደ ኘሪሚየር ሊጉ ያሳደገውን አሰልጣኝ በፀሎት ልኡል ሰገድን አሰናብቶታል። መድህን ወደ ሊጉ እንዲያድግ ከፍተኛ ሚና የተወጡት አሰልጣኙ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ክለቡን መ
የኢትዮጵያ መድህን ድርጅት ወደ ኘሪሚየር ሊጉ ያሳደገውን አሰልጣኝ በፀሎት ልኡል ሰገድን አሰናብቶታል። መድህን ወደ ሊጉ እንዲያድግ ከፍተኛ ሚና የተወጡት አሰልጣኙ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ክለቡን መልቀቃቸው ተገልጿል!

ኢትዮጲያ ቡና ለቀጣዩ አመት ከወዲሁ ዝውውሮችን እየፈፀመ ያለ ሲሆን……ዛሬ 5 የሚደርሱ ተጨዋቾች በአዲስ ኢንተርናሽናል ሆስፒታል ተገኝተው የጤና ምርመራቸውን አድርገዋል። በነገው እለትም ተጨማሪ ሶስት
ኢትዮጲያ ቡና ለቀጣዩ አመት ከወዲሁ ዝውውሮችን እየፈፀመ ያለ ሲሆን……ዛሬ 5 የሚደርሱ ተጨዋቾች በአዲስ ኢንተርናሽናል ሆስፒታል ተገኝተው የጤና ምርመራቸውን አድርገዋል። በነገው እለትም ተጨማሪ ሶስት ተጨዋቾች ከክለቡ ለመነጋገር ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ይጠበቃል። ✍ዳንኤል መምህሩ

የአዲስ አበባ ስታድየም እድሳት ሳር ተከላ ተጠናቀቀ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከካፍ የስታድየም መመዘኛ መስፈርት አንፃር አህጉራዊና አለም አቀፍ ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ላይፈቀድለት የሚችልበት
የአዲስ አበባ ስታድየም እድሳት ሳር ተከላ ተጠናቀቀ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከካፍ የስታድየም መመዘኛ መስፈርት አንፃር አህጉራዊና አለም አቀፍ ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ላይፈቀድለት የሚችልበት እድል ሰፊ ነው ብሏል። ፎቶ-ሀብታሙ ካሴ

በውስጥ ሊግ ብቻ ለሚጫወቱ ተጫዋቾችን ብቻ የሚያሳትፈው የቻን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከሱዳን ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ስብስቡን ይፋ አድርገዋል! በዚህም መሰረት ለሚከተሉት ተ
በውስጥ ሊግ ብቻ ለሚጫወቱ ተጫዋቾችን ብቻ የሚያሳትፈው የቻን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከሱዳን ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ስብስቡን ይፋ አድርገዋል! በዚህም መሰረት ለሚከተሉት ተጫዋቾች ጥሪ ተደርጓል! 👉ግብ ጠባቂዎች ፋሲል ገብረሚካኤል (ባህር ዳር ከተማ) በረከት አማረ (ኢትዮጵያ ቡና) አላዛር ማርቆስ (ጅማ አባ ጅፋር) 👉ተከላካዮች ሱሌማን ሀሚድ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ሄኖክ አዱኛ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ምኞት ደበበ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ያሬድ ባየህ (ፋሲል ከነማ) ሚሊዮን ሰለሞን (አዳማ ከተማ) አስራት ቱንጃ (ኢትዮጵያ ቡና) ረመዳን የሱፍ (ወልቂጤ ከነማ) ጊት ካትኩት (ሲዳማ ቡና) 👉አማካዮች ጋቶች ፓኖም (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ከንዓን ማርክነህ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ሱራፌል ዳኛቸው (ፋሲል ከነማ) በዛብህ መለዮ (ፋሲል ከነማ) በረከት ደስታ (ፋሲል ከነማ) አማኑኤል ዮሃንስ (ኢትዮጵያ ቡና) መስዑድ መሐመድ (ጅማ አባ ጅፋር) 👉አጥቂች ቸርነነት ጉግሳ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) አማኑኤል ገብረሚካኤል (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ዳዋ ሁቴሳ (አዳማ ከተማ) ብሩክ በየነ (ሀዋሳ ከነማ) ይገዙ ቦጋለ (ሲዳማ ቡና)

መክብብ ደገፉ (ሲዳማ ቡና)⚽️🧤 ተወልጄ ያደኩት ዱራሜ አካባቢ ነው.........🗣ቤተሰቦቼ ኳስ እንድጫወት አይፈቅዱልኝም ነበር አባቴ የቢዝነስ ሰው ነው እሱን ጨምሮ ቤተሰቦቼ እንድማር ነበር ፍላ
መክብብ ደገፉ (ሲዳማ ቡና)⚽️🧤 ተወልጄ ያደኩት ዱራሜ አካባቢ ነው.........🗣ቤተሰቦቼ ኳስ እንድጫወት አይፈቅዱልኝም ነበር አባቴ የቢዝነስ ሰው ነው እሱን ጨምሮ ቤተሰቦቼ እንድማር ነበር ፍላጎታቸው........ ከብዙ የቤተሰብ ጭቅጭቅ በኋላ ወላይታ ዲቻ መጫወት ጀመርኩ እዛ ኮኮብ በረኛ ሆንኩ ዋንጫም አነሳሁ........ይህን ሲያዩ ቤተሰቦቼም በቃ ይጫወት ወደሚል ነገር አመሩ! ስለ ቤተሰቡ ሁኔታ ሲናገር ሰባት ወንድም እና አራት እህቶች አሉኝ.....በቤተሰቤ ስፖርተኛ እኔ ብቻ አይደለሁም አሁን ላይ በዱራሜ ከተማ የሚጫወት ዘሪሁን ደገፉ የሚባል ወንድም አለኝ! ስለ ባህሪው መክብብ ይናገራል🗣......ከሰዎች ጋር እግባባለሁ ትምክተኛ የምባል አይነት ሰው አይደለሁም! አንድ ቀን መክብብ በጸጉር እና ጺሙ ለይት ብሎ ስለገባበት ጨዋታ ሲናገር....🗣የዛን ቀን የአባቶች ቀን ነበር እኔም አባት ስለሆንኩ ነው አባቶችን ለማሰብ እንደዛ ሆኜ የገባሁት! 🗣ልዩ ሆኜ መታየት እፈልጋለሁ....አዲስነገር ማድረግ ያስደስተኛል....! 🗣በሊጉ አንድ ግዜ ብቻ ነው ታይተክ የምታልፈው በዚ ግዜ ግን ልዩ ሆኜ በሊጉ ማለፍን እፈልጋለው.....! ✍Abdul feta

የእናንተ የአመቱ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ ምርጡ ተከላካይ ማነው?
Anonymous voting

እለተ አርብ የተፈጠረውን አወዛጋቢ ጉዳይ ለመመርመር ሊግ ሼር ካምፓኒው አሰላጣኞችን ጨምሮ ታዛቢ እና ዳኛዎችን ለማነጋገር ቢሮው ጠርቷል! በ30ኛ ሳምንት አርብ ሰኔ 24/2014 ዓ.ም በተደረጉ ጨዋታ
እለተ አርብ የተፈጠረውን አወዛጋቢ ጉዳይ ለመመርመር ሊግ ሼር ካምፓኒው አሰላጣኞችን ጨምሮ ታዛቢ እና ዳኛዎችን ለማነጋገር ቢሮው ጠርቷል! በ30ኛ ሳምንት አርብ ሰኔ 24/2014 ዓ.ም በተደረጉ ጨዋታዎች ላይ የተፈጠሩ ክስተቶችን ተከተሎ ለጨዋታ ታዛቢዎች፣ ዳኞችና የቡድን መሪዎች የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ለማነጋገር ጥሪ አደርጓል። በዚህም ለሶስት የጨዋታ ታዛቢዎች ሻለቃ በልሁ ሀይለማሪያም፣ ሰላሙ በቀለ እና አበጋዝ ነብየልዑል ሲሆን ከዳኞች ለኢንተርናሽናል ዳኛ ዶ/ር ኃይለየሱስ ባዘዘው፣ ለኢንተርናሽናል ዳኛ አሸብር ሰቦቃ፣ ለፌዴራል ዳኛ ኤፍሬም ደበሌ፣ ለፌዴራል ዳኛ ባህሩ ተካ ለፌዴራል ዳኛዮናስ ካሳሁን እና ለፌዴራል ዳኛ እያሱ ፈንቴ እንዲሁም ከቡድን አባላት ለፋሲል ከነማ ክለብ ዋና አሰልጣኝ ኃይሉ ነጋሽ እና ለቡድን መሪው ሀብታሙ ዘዋለ ፥ ለሃዋሳ ከተማ ክለብ ዋና አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ እና የቡድን መሪው ብርሃኑ ጤዳሞ ፣ ለአዲስ አበባ ከተማ ክለብ ዋና አሰልጣኝ ጳውሎስ ጌታቸው እና የቡድን መሪው መሰረት ወ/ማርያም ረቡዕ ሰኔ 29 2014 ዓ.ም በተለያየ ሰዓት በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ጽ/ቤት እንዲገኙ ጥሪውን አስተላልፏል የኢትዮጵያ ሊግ ሼር ካምፓኒ!

የእናንተ የአመቱ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ ምርጡ ተከላካይ ማነው?
Anonymous voting

የእናንተ የአመቱ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ ምርጡ ተከላካይ ማነው? ➠ዋሀብ አዳምስ (ወልቂጤ ከተማ) ➠ሱለይማን ሀሚድ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ➠ፍሬዘር ካሳ (ሀድያ ሆሳዕና) ➠መናፍ አወል(ባህርዳር
የእናንተ የአመቱ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ ምርጡ ተከላካይ ማነው? ➠ዋሀብ አዳምስ (ወልቂጤ ከተማ) ➠ሱለይማን ሀሚድ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ➠ፍሬዘር ካሳ (ሀድያ ሆሳዕና) ➠መናፍ አወል(ባህርዳር ከተማ) ➠ሄኖክ አዱኛ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ➠ፍሪፖንግ ሜንሱ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ➠ጊት ጋትኩት (ሲዳማ ቡና) ➠ሰኢድ ሀሰን (ፋሲል ከነማ) የእርሶን ምርጥ ከታች በተዘጋጀው የህዝብ ቃለ መጠይቅ (Poll) ይምረጡ👇👇

በሊጋችን ከዋናው ትወና በስተጀርባ ያሉ ጀግኖች! የ2014 አመት የኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ በቅዱስ ጊዮርጊስ አሸናፊነት ትናትና ተጠናቋል! አመቱን ከተደረገው ፉክክር ባሻገር ግን ከጨዋታ በኋላ በሚወጡ አ
+1
በሊጋችን ከዋናው ትወና በስተጀርባ ያሉ ጀግኖች! የ2014 አመት የኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ በቅዱስ ጊዮርጊስ አሸናፊነት ትናትና ተጠናቋል! አመቱን ከተደረገው ፉክክር ባሻገር ግን ከጨዋታ በኋላ በሚወጡ አስገራሚና ውብ የሜዳ ላይ ክስተት ምስሎችን በማህበራዊ ድህረ ገጾች ላይ ለእግር ኳስ አፍቃሪያን በማድረስ እግር ኳሳችንን ለማሳደግ የሚጥሩ ብዙ ናቸው ከነዚህም መካከል ቅዱስ እና አኩ ይጠቀሳሉ! አመቱን በተደረጉ ጨዋታዎች ላይ በሜዳ በመገኝት ባነሷቸው ውብ ምስሎች ለእግር ኳሳችን ትልቅ አሻራን ትተውልን አልፈዋል! #Tank_you #Aku_and_Kidus🙏 #Aku_sport_image #Tikvahsportimage

ተጀመረ | ኢትዮጵያ ቡና 0-0 ባህር ዳር ከተማ
ተጀመረ | ኢትዮጵያ ቡና 0-0 ባህር ዳር ከተማ

አሰላለፍ | ኢትዮጵያ ቡና ከ ባህርዳር ከተማ | @Libro_sport_GROUP | @Libro_sport @Abdul_feta_lke
አሰላለፍ | ኢትዮጵያ ቡና ከ ባህርዳር ከተማ | @Libro_sport_GROUP | @Libro_sport @Abdul_feta_lke

ተጠናቀቀ| ሲዳማ ቡና 1 - 1 ሀዲያ ሆሳዕና 3'ይገዙ ቦጋለ 36' ፍቅረየሱስ ተ/ብርሀን | @Libro_sport_GROUP | @Libro_sport @Abdul_feta_lke
ተጠናቀቀ| ሲዳማ ቡና 1 - 1 ሀዲያ ሆሳዕና 3'ይገዙ ቦጋለ 36' ፍቅረየሱስ ተ/ብርሀን | @Libro_sport_GROUP | @Libro_sport @Abdul_feta_lke

ተጀመረ | ሲዳማ ቡና 0-0 ሀዲያ ሆሳዕና
+1
ተጀመረ | ሲዳማ ቡና 0-0 ሀዲያ ሆሳዕና