210 915
Suscriptores
+15824 horas
+1 5957 días
+7 95630 días
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
ቡንደስሊጋ ተጨማሪ ክለብ ያሳትፋል !
ቦርስያ ዶርትመንድ ፒኤስጂን ማሸነፉን ተከትሎ የጀርመን ቡንደስሊጋ በቀጣይ የውድድር አመት ተጨማሪ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታ እንደሚያገኙ ተገልጿል።
ይህንንም ተከትሎ በቀጣይ የውድድር አመት በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ #አምስት የጀርመን ቡንደስሊጋ ክለቦች ተሳታፊ የሚሆኑ ይሆናል።
በቡንደስሊጋው እነማን ደረጃውን ይዘዋል ?
1️⃣ ባየር ሊቨርኩሰን :- 81 ነጥብ
2️⃣ ባየር ሙኒክ :- 69 ነጥብ
3️⃣ ስቱትጋርት :- 64 ነጥብ
4️⃣ ሌፕዚግ :- 62 ነጥብ
5️⃣ ዶርትመንድ :- 57 ነጥብ
@tikvahethsport @kidusyoftahe
👍 221❤ 23👎 11👏 7😁 6
ቦርስያ ዶርትመንድ ድል አድርጓል !
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ቦርስያ ዶርትመንድ ከፒኤስጂ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
የዶርትመንድን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ኒክላስ ፉልክሩግ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።
በጨዋታው የፒኤስጂው ተጨዋች ሉካስ ሄርናንዴዝ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ ለመውጣት ተገዷል።
የሁለቱ ክለቦች መልስ ጨዋታ በሚቀጥለው ሳምንት ማክሰኞ ፓሪስ ፓርክ ዴ ፕሪንስ ስታዲየም የሚደረግ ይሆናል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
👍 80❤ 14👏 13👎 7🙏 3👌 1
አል ናስር ለፍፃሜ ደርሰዋል !
በሳውዲ አረቢያ ኪንግስ ካፕ ግማሽ ፍፃሜ አል ናስር ከአል ካሌጅ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ለፍፃሜ መድረሳቸውን አረጋግጠዋል።
የአል ናስርን የማሸነፊያ ግቦች ክርስቲያኖ ሮናልዶ 2x ፣ እና ሳዲዮ ማኔ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ በዘንድሮው የውድድር ዘመን ባደረጋቸው አርባ አምስት ጨዋታዎች አርባ አራት ግቦች አስቆጥሮ አስራ ሁለት አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።
አል ናስር በፍፃሜው ከአል ሂላል ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
👍 195😁 45❤ 31🔥 15