ወንጌል ያሸንፋል️
"ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።" (የማቴዎስ ወንጌል 24: 14) ☞ ቻናላችንን በዩቲዩብ ለመከታተል👇 ይጫኑት። http://bit.ly/2KM5PzL ለሀሳብ አስተያየት👇 📨 @ApostleAbz ☞ አብረውን ለማገልገል #0930703775 ይደውሉ።
Mostrar más- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Carga de datos en curso...
መንፈሳዊ ስጦታዎች ❤️🔥❤️🔥❤️🔥❤️🔥❤️🔥❤️🔥❤️🔥 ክፍል 38 ✍✍✍ የመፈወስ ስጦታ 🍁🍁🍁🍁🍁 የመፈወስ ስጦታ የመፈወስ ስጦታ በሶስት አይነት ሰዎች ላይ እንደሚገለጥ መፅሀፍ ቅዱስ ይናገራል።የመጀመሪያው በሁሉም አማኞች ላይ ሲሆን ለእምነታቸው እንደ ምልክት በእጆቻቸው ላይ ይፈፀማል።ማርቆስ 16 (አዲሱ መ.ት)¹⁷ የሚያምኑትን እነዚህ ምልክቶች ይከተሏቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ልሳንም ይናገራሉ፤¹⁸ እባቦችን በእጃቸው ይይዛሉ፤ የሚገድል መርዝ ቢጠጡ እንኳ አይጐዳቸውም፤ እጃቸውንም በሕመምተኞች ላይ ይጭናሉ፤ እነርሱም ይፈወሳሉ።” ሁለተኛው ደግሞ ለቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች የተሰጠ ሲሆን እነርሱም የታመመው ሰው ጋ በመሄድ በዘይት ሲፀልዮ የሚሆን የእምነት ፀሎት ሲሆን ይህም ለታመመው ፍፁም ፈውስን ያስገኝለታል። ያዕቆብ 5 (አዲሱ መ.ት)¹⁴ ከእናንተ መካከል የታመመ ሰው አለ? የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎችን ይጥራ፤ እነርሱም በጌታ ስም ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት።¹⁵ በእምነት የቀረበ ጸሎት የታመመውን ሰው ይፈውሰዋል፤ ጌታም ያስነሣዋል፤ ኀጢአትም ሠርቶ ከሆነ፣ ይቅር ይባላል። ሶስተኛው ደግሞ ለክርስቶስ አካል ብልቶች እንዲታነፁበት መንፈስ ቅዱስ የሚሰጠው የመፈወስ ስጦታ ነው። '' ለአንዱም በአንዱ መንፈስ የመፈወስ ስጦታ”— 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥9 የመፈወስ ስጦታ እንደሌሎቹ ስጦታዎች ሁሉ አንዱ መንፈስ ቅዱስ እንደ ወደደ ለወደደው ሰው የሚሰጠው ስጦታ ነው። የመፈወስ ስጦታ ደግሞ በተለያዮ ምክንያቶች መስራት ያቆሙ የሰውነት ክፍሎችን አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ነው።ብልቶቻችን ታመሙ ሲባል መስራት አቆሙ ወይም ከአእምሮችን ጋር ግንኙነቱ ተቋርጧል ወይም በከፊል መስራት አቁሟል እንዳይሰራም የተጋረጠ ነገር አለ እንደ ማለት ነው። የሚሰራን የሰውነት ክፍል መልሶ እንዲሰራ ማድረግ…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ክፍል 39 ✍✍✍ የመፈወስ ስጦታ 🌾🌾🌾🌾🌾 የፈውስ ስጦታ በሰውነት ላይ ያለን ማንኛውንም ደዌ የምናራግፍበት ስጦታ ብቻ አይደለም።በብሉይ ኪዳን ያሉ መጵሐፍትን ስናነብ ሀገር እንደ ሀገር ከገባበት ውጥንቅጥ እንዲወጣ ምድሪቷ ህዝቦቿ እንዲሁም የሚያጨነግፍው ውሃዎች እንደተፈወሱ ተፅፎልናል። በኤርሚያስ የትንቢት መጵሐፍ ውስጥ እግዚአብሄርን ባለማወቅ እግዚአብሄርን በመበደልና በመካድ የረከሰችው እስራኤልና ይሁዳ ምድሪቱ በኃጢያት ምክንያት ፈፅማ የረከሰች ለጠላቶቿም ተላልፋ እንድትሰጥ የተፈረደባት እንደነበረች እና ኤርሚያስ ግን ፈውስን ይጠብቅ እንደነበር ተፅፎዓል። “ሰላምን ተስፋ አደረግን፤ መልካም ነገር ግን አልመጣም፤ የፈውስ ጊዜን ተመኘን፤ ነገር ግን ሽብር ብቻ ሆነብን።” ኤርምያስ 8፥15 (አዲሱ መ.ት) “ምድሪቱ በዝናብ እጦት የምትጐዳው፣ የሜዳውም ሣር ሁሉ በድርቅ የሚመታው እስከ መቼ ነው? ከነዋሪዎቿ ክፋት የተነሣ፣ እንስሳትና አዕዋፍ ጠፍተዋል፤ ደግሞም ሕዝቡ፣ “በእኛ ላይ የሚሆነውን አያይም” ብለዋል።”ኤርምያስ 12፥4 (አዲሱ መ.ት) በኤልሳ ዘመን የኢያሪኮ ከተማ ለኑሮ የተመቸች ከተማ ነበረች ዳሩ ግን ውሃው መጥፎ ከመሆኑ የተነሳ ምድሪቱ ፍሬ እንዳትሰጥ አድርጎት ነበር ወይም ምድሪቱን ጭንጋፍ አድርጓት ነበር።ኤልሳም በእግዚአብሄር መንፈስ ተመርቶ በአዲስ ማሰሮ ውስጥ ጨው በማድረግ ወደ ውሃው ምንጭ በመሄድ ጨው ጣለበትና እግዚአብሄር የተናገረውን ቃል ለህዝብ ተናገረ ።እግዚአብሄር ውሃውን ፈውሼዋለው አለ ውሃውም ተፈወሰ። 2ኛ ነገሥት 2 (አዲሱ መ.ት)¹⁹ የከተማዪቱም ሰዎች ኤልሳዕን፣ “እነሆ ጌታችን፤ እንደምታያት ይህች ከተማ ለኑሮ የተመቸች ናት፤ ይሁን እንጂ ውሃው መጥፎ ሲሆን ምድሪቱም ፍሬ የማትሰጥ ናት” አሉት።²⁰ እርሱም፣ “እስቲ በአዲስ ማሰሮ ጨው…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🧚🧚🌾🌾🧚🌾🌾 ክፍል 34 ✍✍✍ ተዓምርናፈውስ ተዓምራትና ፈውስ እምነትን ተከትሎ የሚደረጉ ምልክቶች ናቸው።በእኛ ውስጥ ራሳችንን ክደን ኢየሱስ እንዲኖር ህይወቱም በእኛ እንዲሰራ በእምነት ከእግዚአብሄር ጋር ስንስማማ ኢየሱስ በእኛ ህይወት ውስጥ መኖር ሲጀምር መለኮታዊ ችሎታዎች የመለኮቱ ኃይልና የብርታቱ ጉልበት በእኛ ይታያል። ኢየሱስ የሰናፍንጭ ቅንጣት የምታህል እምነት ካለህ ተራራውን ተነቅለህ ሲድ ብትሉት ይሄዳል ሲል ተናግሮዓል ተራራን ነቅሎ ከነበረበት ስፍራ ወዳልነበረበት ወደሌላ ስፍራ ማድረግ ተዓምር ነው ይህ ተዓምህ ግን የሚሆነው በእምነት ነው። “እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “እምነታችሁ በማነሱ ምክንያት ነው፤ እላችኋለሁ፤ የሰናፍጭ ቅንጣት የምታህል እምነት ቢኖራችሁ፣ ይህንን ተራራ፣ ‘ከዚህ ተነሥተህ ወደዚያ ሂድ’ ብትሉት ይሄዳል፤ የሚሳናችሁም ነገር አይኖርም — ማቴዎስ 17፥20 (አዲሱ መ.ት) ማዕበል ፀጥ እንዲል ማዘዝ ልዕለ ተፈጥሮአዊ አቅምን ይጠይቃል እምነት ካለን ልዕለ ተፈጥሮአዊው አቅም በእኛ መገለጥ ይጀምራል በዚህም ተፈጥሮን እናዛለን ማህበሉን ፀጥ በል ስንለው በመታዘዝ ፀጥ ይላል።የኢየሱስ ማህበሉን ማዘዝና ማህበሉም ለኢየሱስ መታዘዙ ደቀ መዛሙርቱን ያስገረመ ጉዳይ ነበር።የተገረሙት እነርሱ ማድረግ ያልቻሉትን ስላደረገ ነው።እምነት ሰው ማድረግ የማይችለውን እግዚአብሄር ማድረግ የሚችለውን በእግዚአብሄር መንፈስ አማካኝነት በኢየሱስ ስም በእምነት ማድረግ መቻል ነው። “ኢየሱስም፣ “እናንተ እምነት የጐደላችሁ፤ ለምን ይህን ያህል ፈራችሁ?” አላቸው፤ ከዚያም ተነሥቶ ነፋሱንና ማዕበሉን ገሠጸ፤ ወዲያውም ጸጥታ ሰፈነ።”— ማቴዎስ 8፥26 (አዲሱ መ.ት) ተዓምር ሰው ማድረግ የማይችለውን ሰው ሊሰራው የማይችለውን ከሰው ችሎታና አቅም በላይ የሆነውን በእግዚአብሄር ጉልበትና…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ክፍል 43 ✍✍✍ መናፍስትን የመለየት ስጦታ መናፍስትን የመለየት ስጦታ ለምን አስፈለገን ካላችሁ መንፈስ ሁሉ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሄርም መንፈስ ባለመሆኑና መንፈስንም ሁሉ ማመን ስለማይገባን መናፍስት ከእግዚአብሄር መሆን አለመሆኑን በሚገባ እንድንመረምር መጵሐፍ ቅዱስ ይመክረናል። “ወዳጆች ሆይ፤ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር መሆናቸውን መርምሩ፤ ምክንያቱም ብዙ ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም ወጥተዋልና።”1ኛ ዮሐንስ 4፥1 (አዲሱ መ.ት) ሐሰተኞች በመኖራቸው እውነተኞችን ከሐሰተኞች በመመርመር ልንለይ መንፈስንና የመንፈስን አሰራር ልንለይ ይገባናል።ዮሐንስ ይህንን ምክር ከእግዚአብሄር ለተወለዱ ለእግዚአብሄር ልጆች ያስተላለፈው ምክር በመሆኑ ሁላችንም መርማሪዎች ልሆን ይገባናል። ሰዎች መናፍስትን ባለመለየታቸው በተለይም አሁን በእኛ ዘመን ብዙዎችን በማታለል ከእውነተኛው እምነት የሚያስክዱ የአጋንትን ትምህርት የሚከተሉና የሚያስተምሩ ሰዎች ተነስተው እንደነበርና ዛሬም እንደሚነሱ መፅሐፍ ቅዱስ በግልጥ ይናገራል። “በኋለኞች ዘመናት አንዳንዶች እምነትን ክደው አታላይ መናፍስትንና የአጋንንትን ትምህርት እንደሚከተሉ መንፈስ በግልጥ ይናገራል።” — 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥1 (አዲሱ መ.ት) መዘንጋት የማይገባን ነገር ቢኖር መጋደላችን ከስጋና ከደም ጋር ሳይሆን ከዚህ ከጨለማው ዓለም ገዥዎች ከስልጣናት ከኃይላት በሰማያዊ ስፍራ ካሉ ከርኩሰት መናፍስት ሰራዊቶች ጋር በመሆኑ አሰራሩን መለየት ይገባናል። “ምክንያቱም ተጋድሎአችን ከሥጋና ከደም ጋር ሳይሆን ከዚህ ከጨለማ ዓለም ገዦች፣ ከሥልጣናትና ከኀይላት እንዲሁም በሰማያዊ ስፍራ ካሉ ከርኩሳን መናፍስት ሰራዊት ጋር ነው።” — ኤፌሶን 6፥12 (አዲሱ መ.ት) ዛሬም መርሳት የማይገባን ነገር ቢሆን…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🍁🍁🍁🌾🍁🍁🍁 ክፍል 36 ✍✍✍ ተዓምራት የማድረግ ስጦታ 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ሐዋሪያት ተዓምራት ድንቆችና ምልክቶች ካልተደረጉ ብለው ፀልየው አያውቁም የሚፀልዮት አንድ ነገር ነው።የመጀመሪያው ቃሉን በግልጥ መናገር እንዲሰጣቸው ሲሆን ሁለተኛ ደግሞ እግዚአብሄር የሚሰብኩትን ብላቴና እንዲያከብር እጆቹንም በመዘርጋት ድንቆችን ተዓምራቶችንና ምልክቶችን በማድረግ አብሮአቸው እንዲሰራ ነው። ሐዋርያት 4 (አዲሱ መ.ት)²⁹ አሁንም ጌታ ሆይ፤ ዛቻቸውን ተመልከት፤ ባሪያዎችህም ቃልህን በፍጹም ድፍረት መናገር እንዲችሉ አድርጋቸው።³⁰ ለመፈወስ እጅህን ዘርጋ፤ በቅዱሱ ብላቴናህም በኢየሱስ ስም ድንቅና ታምራት አድርግ።” ሐዋሪያት ስጠን ብለው የሚለምኑት አለ ደግሞ እኛ እናድርግ ሳይሆን አድርግ ብለው እግዚአብሄርን የሚጠይቁት ጉዳይ አለ።ስለዚህም ቃሉን መስበክና የምትሰብኩት ቃል እንዲሰጣችሁ ቃሉንም በፍፁም ግልፅነት እንድትሰብኩ እንፀልይ ተዓምራት ድንቆችንና ምልክቶችን ግን እኛ እናድርግ ተብሎ አይፀለይም አንተ አድርግ ምክንያቱም እኛ ከእግዚአብሄር ጋር አብሮ ሰራተኞች ነን።ይህ ፀሎት መልስ ያገኘው ወዲያው ነበር።ወዲያው ያሉበት ስፍራ ተናወጠ መንፈስ ቅዱስን ተሞሉ ተዓምራት ግን አላደረጉም ያደረጉት ቃሉን መስበክ ነው ቃሉ ሲሰበክ ቃሉን የሚያፀናው ጌታ ነው ቃሉም የሚፀናው በተዓምራዊ ምልክት ነው። “ከጸለዩም በኋላ የነበሩበት ስፍራ ተናወጠ፤ ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፤ የእግዚአብሔርንም ቃል በድፍረት ተናገሩ።” — ሐዋርያት 4፥31 (አዲሱ መ.ት) ቃሉን እንስበክ የቃሉ ባለቤት ቃሉን በምልክቶችና በተዓምራት ያፀናዋል። ኢየሱስ ወደ አባቱ ወደ አባታችን ሊያርግ ሲል ለሐዋሪያቱ የሰጠው አንድ ተልዕኮ ነው ይህውም ወንጌልን መስበክ ኢየሱስ ስበኩ አስተምሩ እያጠመቃችሁም ደቀ መዛሙርቴ አድርጉ ብሎ ብቻ…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🔥🔥🧚🧚🔥🔥 ክፍል 41 ✍✍✍ መናፍስትን የመለየት ስጦታዎች 🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣 መናፍስትን የሚለዮ ሰዎች ፈታኞች ናቸው ““ብረት እንደሚፈተን፣ የሕዝቤን መንገድ፣ አካሄዳቸውንም እንድትፈትን፣ አንተን ፈታኝ አድርጌሃለሁ።” — ኤርምያስ 6፥27 (አዲሱ መ.ት) “መንገዳቸውን እንድታውቅና እንድትፈትን በሕዝቤ መካከል ፈታኝ አድርጌሃለሁ።”— ኤርምያስ 6፥27 አገልጋዮች በሶስት መንገድ ይናገራሉ።የመጀመሪያው የእግዚአብሄርን ቃል ከእግዚአብሄር በመስማት ሲሆን ሁለተኛው እግዚአብሄር ሳይናገር የራሳቸውን ሀሳብ የእግዚአብሄር ቃል አድርገው የሚናገሩ ሰዎች ናቸው።ሶስተኞቹ ደግሞ እግዚአብሄር ሳይናገረው ሰይጣን ወደ አእምሮአቸው የሚያስገባውን ሀሳብ እግዚአብሄር የገለጠላቸው አድርገው ወይም መስሎአቸው የሚናገሩ ናቸው።እነዚህ ሶስቱም የእግዚአብሄር አገልጋዮች ሆነው በእግዚአብሄር ቤት ውስጥ የሚኖሩ ናቸው ዳሩ ግን ከመጀመሪያዎቹ ውጪ ያሉት ሌሎቹ የእግዚአብሄር ዕቃ አይደሉም።እንግዲህ መናፍስትን የመለየት ስጦታን መንፈስ ቅዱስ የሰጣቸው ሰዎች አገልጋዮች የሚናገሩበትን መንፈስ በመፈተን ወይም በመለየት አማኞችን ከሰውና ከዲያቢሎስ ቃል የሚጠብቁ ጠባቂዎች ናቸው። “እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “ነቢያቱ በስሜ የሐሰት ትንቢት ይናገራሉ፤ እኔ አልላክኋቸውም፤ አላዘዝኋቸውም፤ አልተናገርኋቸውምም። የሐሰት ራእይ፣ ሟርት፣ ከንቱ ነገርንና የልባቸውን ሽንገላ ይተነብዩላችኋል።”ኤርምያስ 14፥14 (አዲሱ መ.ት) ሚኪያስና ሌሎች አራት መቶ ነቢያት ሚኪያስ የእግዚአብሄርን ቃል ሲናገር ሌሎች ግን የሐሰት መንፈስ እንደተጠቀመባቸው ተፆፎዓል። “ሚክያስ ግን፣ “ሕያው እግዚአብሔርን! ለእርሱ የምነግረው እግዚአብሔር የነገረኝን ብቻ ነው” አለ።”1ኛ ነገሥት 22፥14 (አዲሱ መ.ት) የሐሰት መንፈስ በነቢያቱ ላይ…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ክፍል 40 ✍✍✍ መናፍስትን የመለየት ስጦታ 🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣 መናፍስትን የመለየት ስጦታ በምድር የሚኖሩ ሰዎችን ከባህሪያቸውና ከድርጊቶቻቸው ተነስተን እንደምለየው የሰውን ውስጣዊ ማንነት በውስጣችን ባለው በሰው መንፈስ አማካኝነት እንደምናውቀው መንፈሳዊውም ዓለም በእግዚአብሄር መንፈስ የሚታወቅ የሚለይ ነው። መንፈሳዊው ዓለም በሁለት ይከፈላል።የእግዚአብሄር አለምና የዚህ ዓለም አምላክ የሆነው የክፋት ሰራዊቶች መንፈሳዊ አለም።የእግዚአብሄር መንፈስ የእግዚአብሄርን አለም ከክፋው ዓለም ለይተን የምናይበትን መንፈሳዊ ዓይን ሰጥቶናል። መናፍስትን መለየት ሲባል ዲያቢሎስ ያለበትን የዲያቢሎስ ስራ ብቻ ማየት ማለት አይደለም ልክ ነው የዲያቢሎስን ስራና አጋንት የተቆጣጠረውን ሰው መለየት አንዱ መናፍስትን መለየት ነው ዳሩ ግን ብቸኛ አገልግሎት አይደለም። መናፍስትን መለየት ማለት የእግዚአብሄርን መገኘት ስራውንና የእግዚአብሄር መንፈስ ያለበትን ከሌለበት መለየት የእግዚአብሄርን መላክና ራሱን የብርሃን መልአክ አድርጎ ከሚለውጠው ክፉ መለየት. መንፈስ ቅዱስ የሞላበትንና የክፉው የሞላበትን በንግግር በእይታ በልዮ ልዮ መንገድ መለየት ነው። መናፍስትን የመለየት ስጦታ ለቤተክርስቲያን እጅግ ጠቃሚ የሆነ ስጦታ ነው።መናፍስትን የሚለይ ሰው በቤተክርስቲያን ውስጥ ካለ በቤተክርስቲያን ውስጥ የኤልዛቤል መንፈስ መሰልጠን አይችልም።ነብይ ሳይሆኑ ነብይ ነን ሐዋሪያ ሳይሆኑ ሐዋሪያ ነን የሚሉ ሰዎች እንደ ልባቸው መፈንጨት አይችሉም። መናፍስትን የሚለዮ ሰዎች መርማሪዎች ወይም ፈታኞች ናቸው። በኤፌሶን ያለችው ቤተ ክርስቲያን የተመሰከረላት በዚህ ነው።“ሥራህን፣ ጥረትህንና ትዕግሥትህን ዐውቃለሁ። ክፉዎችንም ችላ ብለህ እንዳላለፍሃቸው፣ ሐዋርያት ሳይሆኑ ሐዋርያት ነን የሚሉትንም መርምረህ…