cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

የሙስሊሞች ቤት – World Muslim House

*በራስህ አንደበት መጥራት ባትችል በሰው አንደበት ተጣራ* እኔም በቻልኩት ዲኔን በእውቀት ላይ ሆኜ ላልደረሰው አስተላልፋለው፣ (((بلغو عني ولو آية.))) حبيبنا صلى الله عليه وسلم

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
196
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ዛሬ ከምንፈፅማቸው ወንጀሎቻችን አንዳንዶቹ ከጊዜያት በፊት በሰው ሲፈፅሙ ስናይ ድንጋጤ ልባችንን ሊሰውረን የቀረበ የነበረ ወንጀሎች ሆነው እናገኛቸዋለን። አንዳንዶቹ ሰዎች እንዲታቀቡ ስናስጠነቅቃቸው የነበሩ ወንጀሎችም ናቸው። በእርግጥ ሁላችንም ወንጀለኞች ነን። እርግጥ ነው ልሂቃን ወንጀልን ቀላል እና ከባድ ብለው ለይተውታል። በእርግጥ በሶላት፣ በጾም፣ በኢስቲግፋር ብዛት ምህረት የሚያገኝ ወንጀል ላይ ወድቆ መገኘት መሠረታዊ ችግር አይደለም። የሰውነት ጠባያችን ነውና መውደቅ ልማዳችን ነው! እጅግ በጣም የሚያስጨንቀው በልብ ድንዛዜያችን የተነሳ እንደወነጀልን የማይሰማን ኃጢኣት ውስጥ ተዘፍቀን መገኘት ነው! ትናንት ሰው ላይ ስናየው ያስደነግጠን የነበረ፣ እንደውም ሰዎችን ስናወግዝበት የነበረን ወንጀል ቀስበቀስ እንላመደዋለን። ከዚያም ያለምንም መገረም በቀዝቃዛ ደም፣ ያለ ድንጋጤ እንፈፅመዋለን። ኧረ! አንዳንዴ በወንጀል ተጠልፈን መውደቃችንን የሃሳብ ለውጥ፣ የምጥቀታችን ገፅታ፣ የግንዛቤያችን ስፋት፣ የምርምራችን ውጤት አድርገን ልንሟገትም ይዳዳናል! እኔ የምላችሁ ይህንን ነው! አደገኛ የወንጀል አይነት ይሄ ነው! ወንጀል በሰዎች የተለመደ ጊዜ ተሟጋች ጠበቃም ያገኛል! ነገርግን የረሳነው ነገር ትናንት በንፅህናችን ሳለን ሰው ሲፈፅማቸው ስናይ የሚያስደነግጡንን ነገሮች ዛሬ እኛ ስንፈፅማቸው የሚያዩ ንፁሆች አሉ። ተግባሮቻችንን በድንጋጤና በጥላቻ ስሜት ይመለከታሉ። ለኛ የጣፈጠንን በመራር ስሜት ይታዘባሉ! እናም ሰዎች ልማድ እና ባህል አድርገው ቢይዙትም ወንጀል ወንጀል ሆኖ ይቀራል። እኛ ስለተቀየርን የወንጀል ጭብጥ ከሚዛጃችን ጋር አይለወጥም! «ሐላል ግልፅ ነው። ሐራምም ግልፅ ነው!» https://t.me/fiqshafiyamh
Mostrar todo...
ይሄን ነገር ከአሁን በፊት የሆነ ወንድም ምን ላድርግ ብሎ አጫውቶኝ ይቅርብህ ስለው አስታውሳለሁ። እየገረመኝ ያለው የህዝባችን የዋህነት ነው። ወዳጄ! ገንዘብ በነፃ አይገኝም። ሠርተህ ብላ! ተመሳሳይ ገጠመኝ ካገጠማችሁ በሚል ይሄን ጽሑፍ ላጋራችሁ ወደድሁ። «የማያውቀኝ እንግሊዛዊ ሰርፕራይዝ አደረገኝ..🤔 አንብቡት ከሣምንት በፊት በማላውቀው በውጭ ስልክ በዋትሳፕ መልዕክት ደረሰኝ፣... ማን ልበል ስለው ጆን በርናንድ እንደሚባልና የሮማኒያዊ እንደሆነ.. በእንግሊዝ እንደሚኖር ነገረኝ።...  #እኔ ስልኬን ኬት አገኘህ.. አጋጣሚ ወደ ሌላ ሰው ለመደወል አስቦ በስህተት እንዳገኘኝ ነገሮኝ እባክህን አትጠራጠረኝ ይበልጥ እንቀራረብና እንግባባለን አለኝ። ባይዋጥልኝም እሺ አልኩት። ቀጠለ... የማውቀው ሰው እንዳይሆን ተጠራጥሬ በድምፅና በቪዲዮ  እንዲደውልልኝ ጠየኩት... ወዲያ ደወለ... የነጭ ጎልማሳ ነው በጣም ቆንጂዬ ፈረንጅ.......! ስራዬን ጠየቀኝ... የመ/ሠራተኛ እንደሆንኩ ነገርኩትና ወዲያ ዛሬ አንተም በስጦታ ማስደሰት እፈልጋለሁ ብሎኝ.. ሙሉ አድራሻዬንና የፖስታ ቁጥር ጠይቆኝ አስቀመጥኩለት.... ለሾፕንግ እያወጣሁ ነውና የጫማና የፖንት ቁጥር ጠየቀኝ...የፖንቱን ትቼ 😂የጫማዬን ቁጥር 41 ላኩለት። ከተዋወቀኝ ሳምንት ሳይሞላሁ ምን አስቦ ነው🤔 ፍርሃትም ግርምትን ወሮኛል። ዕሁድ በጠዋት በዋትአፕ መልዕክት አስቀምጦልኛ። ተቿኩዬ እንቦክ ስገባ 1, IPhone 13 promax 2. Hp Laptop 3. የእጅ ሰዓት 4. ጫማና 5. በርካታ ልብሶች 6. 50 ሺህ ዶላር በአጠቃላይ 35 ኪሎ ግራም ክብደት ያለው መልዕክት  በፖስታ እንደላክኸኝ ነግሮኝ የገዛልኝን ስጦታ በፎቶና በቪዲዮ ላከልኝ። በጣም ተገርሜያለሁ..ማመን አልቻልኩም🤔 ደጋግመ አመሰገንኩት የሌላውን ትቼ የ50ሺህ ዶላር በኢትዮጵያ ብር ህሳብ ውስጥ ገባሁ... ከ4 ሚሊዮን በላይ ይሆናል.... በቃ ብሩን ምን ላርግበት ልስራበት ለጥቂት ሰዓታት የሀብታም ጭንቀት ውስጥ ገባሁ🤔😂 ሰኞ ጠዋት ልክ 1:45 ላይ #0985178826 ቁጥር ደወሉልኝ። ከእንግሊዝ እቃ ተልኮልካል አዲስአበባ ደርሷል እንኳን ደስ አለህ አለችኝ። ስለዚህ መልዕክቱ ጉሙሩክ ስላለ ዛሬውኑ በአድራሻህ ሐዋሳ እንድመጣልህ መታወቂያ ፎቶና 20 ሺህ ብር መላክ ይጠብቅሀል አለችኝ። እሺ እልካለሁ ግን ፖስታ ቤት ዕቃውን ስረከብ አይደለም ክፍያ የሚፈፀመው እንዴት ደረሰኝ ሳልቀበል እቃውን ሳልረከብ ምንም መተማመኛ በሌለበት እከፍላለሁ ስል ጠየኳት....? ይህ አሰራራችንን ነው ብላ ስልኩን ጥርቅም.... ደወልኩ... አዲስአበባ እንደሆንኩ ነገረ ገንዘቡን በአካል መክፈል እችላለሁ...የቢሮያቸውን አድራሻ ጠየኳት። በቢሮያችን አሰራር መሠረት ደንበኞችን በአካል አናስተናግድም። የላከልህ ግለሰብ ያውቀዋል ከእሱ ማረጋገጥ ትችላለህ። አለችኝ 🤔 በዚህ መኃል የእንግሊዙ የበርናንድ ልጅ ጆን ደወለ እቃው ሀገርህ እንደገባ አውቀሃል ?.... እንዴት አወክ ስለው ደውለው ነግረውኛል አለኝ። ስለዚህ በእሽጉ ውስጥ #50 💰 ሺህ ዶላር IPhone ፤ ኮምፒውተርና በርካታ እቃ እንዳለ ታውቃለህ....ዛሬ አስፈላጊውን ክፍያ ካልፈፀምክ ገነዘቡ ስለሚሰረቅ ተበድረህም ወይንም የቤት እቃም ብትሸጥም አሁኑኑ 20ሺህ ብር መክፈል አለብህ አለኝ። እሺ ችግር የለውም አልኩትና። ትንሽ ቆይቶ ደውሎ "ገንዘቡን አስገባህላቸው ወይ" አለኝ...አልከፈልኩ ብር ጎድሎብኛል 10 ሺህ ብቻ አለኝ አልኩት። ብቻ አጣደፈኝ.. ፋታ ነሳኘ...ደወለ... በቃ በእጂህ ያለውን ብር በሙሉ አስገባላቸው አለኝ... እኔም እሺ አልኩና አካውንታቸውን.... ወዲያ ቀጥሎ ያለውን አካውንት ልኮልኝ አሰገብተህ ደረሰኙን ለእኔ ላክልኝ አለኝ🤔 1000503456064 Ahmed aliyu Commercial bank ብሎ አካውንት ላከልኝ። ከመጀመሪያው ጀምሮ በጥርጣሬ የነበርኩ ብሆንም አካውንቱ የግለሰብ መሆኑ ጉዳዩ ሌላ ፍላጎት እንደሆነ አመንኩ። ወዲያው ወደ ኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ስለጉዳዩ መረጃ እንዲሰጡኝ ጠየኳቸው። ድርጅቱ ጆን በጠቀሰው ድርጅ በኩል በኢትዮጵያ የሚታወቅ ድርጅት እንደሌለ እንዲሁም በተለያዩ ሀገራት የራሳቸውን ወኪል ያላቸና በተደራጀ መልኩ  ገንዘብ የሚቀበሉ አጭበርባሪዎች እንደሆኑ አረጋግጠውልኛል። በመጨረሻም እችን መልዕክት ላኩለት You white people, especially westerners, do not know the secret of being African.  The difference between black and white is like the difference between raw dough and baked bread.  White people are like raw dough.  You are a cursed stupid creature created only to cheat to steal from others. I know very well what you wanted from the beginning...how you planned to receive money and took my phone from Facebook.  You don't know me.  The black Africans.  I am the son of Ethiopia, the mother of Africa. Please Refer about Ethiopia...... ይህችን መልዕክተን እንዳነበበ ምንም ትንፍሽ ሳይል ወዲያ ብሎክ አድርጎኝ ላይመለስ ተሰናብቶኛል። ስለዚህ በእንደዚህ በማጭበርበር ስራ የተጠመዱ የተደራጁ ሌቦች ስላሉ የሀገሬ ልጆች ጥንቃቄ አድርጉ። #ሼር በማድረግ ለሌሎች እንዳይሸወዱ መረጃ ያድርሱ Temesgen Petros Roda አመሰግናለሁ»
Mostrar todo...
Photo unavailable
#አስፈላጊ_መልዕክት እባካችሁ ይህንን መልዕክት ለቤተሰብዎና ጓደኛዎ ያስተላልፉ። ሰሞኑን አንዳንድ ህብረተሰቦች ከማይታወቁ ግለሰቦች ስልክ ጥሪ እየደረሳቸው እንደሆነና ስልክ ቁጥሩም፡፣ Tel: +375602605281 Tel: +37127913091 Tel: +37178565072 Tel: +56322553736 Tel: +37052529259 Tel: +255901130460 ወይም ማንኛውም ቁጥር በ+371,+375,+381የሚጀምሩ እንደሆነ አሳውቀዋል። እነዚህን ስልክ ቁጥር የሚጠቀሙት ግለሰቦች ሲደውሉ አንዴ ብቻ ከጠራ ብኋላ ይዘጉታል።እርስዎ መልሰው ሲደውሉ የርስዎን Contact List በ 3sec ውስጥ ወደ ራሳቸው ኮፒ በማድረግ እንዲሁ ሞባዬልዎ ላይ ስለ እርስዎ ባንክ ወይም ክሪዴት ካርድ መረጃ በአንዴ በመጥለፍ የማጭበርበር ስራ እየሰሩ ይገኛሉ።ከላይ በተጠቀሱት ስልክ ቁጥር ከተደወለሎት አይመልሱ ፡ወይም መልሰው አይደውሉ።እንዲሁም በማንኛውም ደዋይ #90 or #09 በመስመር እንዲነኩ ከተጠየቁ አይንኩ።ምክንያቱም በቀላሉ ሲማችሁን አክሰስ(በመጠቀም) በናንተ ስም የፈለጉት ወንጀል በመስራት እራሳቸውን ስለሚሸሽጉ ነው። ይህንን መልዕክት ለቻላችሁ ሰው ፎርዋርድ በማረግ ህዝባችንን ከዚ መሰል ማጭበርበሮች እንታደግ። https://t.me/islamic_app_omi
Mostrar todo...
ኢላሂ! በዚህች ዱንያ ላይ ባይተዋርነቴን እዘንልኝ። በሞትኩ ግዜ ጭንቀቴን እንዲሁም በቀብር ውስጥ ጭርታዬን ስለ ደካማነቴ ስትል እዘንልኝ። ስለ ከፋው ስራዬ ለመተሳሰብ ከፊትህ በመተናነስ በቆምኩ ግዜ የመዋረድን ካባ ከመከናነብ ታደገኝ። ከባሮችህ እይታ የተሰውሩ ፀያፍ ስራዎቼን ሸሽገህ፤ በእኔ ላይ ያካበበውን የነውር ደባቂ ግርጆህንም አትግፈፍብኝ። ኢላሂ! አስክሬኔ ለትጥበት ከማጠብያው ላይ ተጋድሞ የወዳጆቼ እጆች ባገላበጡኝ ግዜ የእዝነት እጆችህን ዘርጋልኝ። ያ ጀሊል! እግሮቼ በአዝራኢል አርጩሜ ተመትተው እና በበድንነት ገመድ ታስረው በሰዎች ጫንቃ ላይ ተንጋልዬ ወደ ቀብር በሄድኩ ግዜም እዝነትህን አትንፈገኝ። ያ ካሊቂ! የምድር ላይ ውሌ ተጠናቅቆ ከምድር በታች በተዘጋጀልኝ አዲሱ ጎጆዬ ሙስሊሞች ሊያጋድሙኝ ከላህዱ ሲተረማመሱ ከምመለከተው የድንጋጤ ትዕይንት በቅርበትህ ታደገኝ። አሚን ጌታዬ!
Mostrar todo...
ኢላሂ! የአመፅ እድፍ ባጠቆረው የማንነት ገፅታዬ እፊትህ አቀርቅሬ ቁምያለሁ።የቆምኩለትን አላማ ከመናዘዜ በፊት አንተ የምታውቀው ስትሆን፤ የልቅናህ መገለጫ እንዲጎላ ወራዳነቴን በልመና ልገልፅልህ ሻትኩ። ሰዪዲ! የውሳኔ ቀለምህ ከማንነቴ እስከ ምንነቴ ከትቦ ሲያበቃ ቀለሙን የዘመን ንፋሶች አድርቀውታል። ውሳኔው ሊፈፀም ነፍስ ተሳስታ በሸይጣን ግዛት በተማረከች ግዜ የተፈፀመውን በሙሉ ይቅር በለኝ። ከልዕልና ማማህ ሁሉን እያየህ ላጠፋኋቸው ጥፋቶቼ ሁሉ የወራዳነትን ካባ ለብሼ፣ የመዋረድ ክንፌን ዘርግቼ፣ የክብር ግንባሬን ደፍቼ ከምህረትህ ትለግሰኝ ዘንድ ኢላሂ! አላለሁ። ጌታዬ! ብትምረኝ ለማርታ የተጋባህ ነህ። በውሳኔው መዝገብህ ቀጠሮዬ ቀርቦ ሳለ እኔ ወዳንተ ያልቀረብኩ ሆኜ ከተመለከትከኝ ፤ ፀፀቴን ለመቃረብያህ ድልድይ አድርግልኝ። ረቢ! በንፋስ አለም ህያው ሳለሁ ትለግሰኝ የነበረውን እዝነትህን ከአፈር እቅፍ ገብቼ በምጋደምበት እለት አትንፈገኝ። እዘንልኝ። መውላይ! ዱንያ ላይ ነፍሴ ስታምፅህ ትሸሽጋት ከነበረው በላይ ለሂሳብ እፊትህ ስትቆም እንድትሸሽጋት ከክብርህ እታች ተደፍቼ እለምንሀለሁ። ኢላሂ! ከፅድቅ ንፅፅር ኩኔኔዎቼ በዝተው ከተገኙ፤ ከአምልኮ ንፅፅር የአንተን ተስፋ አብዝቼ ተመልክቻለሁ ና ተስፋዬ ባንተ ነው። ሰዪዲ! ባንተ ያለኝ ተስፋ የሰማያትን አዕማድ የሚልቅ ሁኖ ሳለ እንዴታ ከልግስና ደጃፍህ ባዶ እጄን የተዋረድኩ ሆኜ እመለሳለሁ?! ያ መውኢሊ! የወጣትነት ዘመኔን ካን የመዘናጋትን ጭንብል አጥልቄ ስባክን ወደምኩ። የአመፅ ውቅያኖስ ማዕበሉ ረግቶ ከመሀሉ ዘመናትን እንድተኛ ሸይጣን የውስልትናን ፍራሽ አነጠፈልኝ። ከተነጠፈልኝ ፍራሽ ላይ ሆኜ የእዝነት ዝናብህ ገላዬን ቢነካኝ፤ ከዝንጋታ ባንኜ የልቅና ምሶሶ ከሆኑት እዝነት ማርታህ ስር ተደፍቼ የልግስና መገለጫ የሆነውን ራህመትህን ተማፀንኩህ። ያ ከሪም! ለፍቅርህ ጠርተኸው በአምልኮ መሰላሎች ከዙፋንህ የሚቃረብ ባርያህ አድርገኝ። ፍቅርህ ወዳንተ ናፍቆት የሚያዋልለውን ልቦናም ለግሰኝ። ያ ለጢፍ! ከዊላያ(አውሊያኦች) ቤተሰብ መድበኸኝ ከመኻከላቸው ጭማሪ ፍቅር ከተለገሱት ምሉአን ህዝቦችህ ላይ ሹመኝ። ትችላለህ! ያ መሊክ! የትዝታህ ማዕበል ላይ ጭነኸኝ ከዚክርክ ወደ ዚክርህ እያሸጋገርክ ፤ ነፍሴንም ከቅድስና ስመ-ባህሪያት ስር አኑርልኝ። ያ ቀዩም! ወዳንተ ምሉዕ መቋረጥን አቋርጠኝ፣ በብርሀናማው ማንነትህ የልቦናዬን እይታ አብራልኝ፣ የልቦናዬን እይታዎችም የግርዶሽ ብርሀኖሽችን የሚሻገሩ አድርግልኝ፣ የተሻገሩ አይኖቼንም ከልቅና ማዕድናት ምንጭ አኑርልኝ፣ ነፍሴንም ከልዕልናው ናፍቆት ስር አንጠልጥልልኝ። ______ ሶፍዋን አህመዲን
Mostrar todo...
እናት የምታነባውን እንባ ሳታባራ ከመኪናው ወርዳ የመስጅዱን ቅጥር ግቢ ገባች። እሱም የመኪናውን መስታወት ዘጋግቶ ሙዚቃውን ከፈተ። በዝግታ የከፈተውን የፍራንስ ሙዚቃ እያዳመጣ ባለበት ሁኔታ የነበረውን ክስተት እንዲህ ሲል እራሱ ይተርክልናል። በሱ ያምርበታል'ና... ሙዚቃውን ተመስጬ እያዳመጥኩ ነው፤ ድንገት የመካን ሰማይ የሚሰነጥቅ፣ ተራሮችዋ የሚያስተጋቡት ደማቅ ቃና ያለው የአዛን ድምፅ ከወደ መስጅዱ ተስተጋባ። «አላሁ አክበሩ አላሁ አክበር... አላ......ሁ አክበሩ አላ......ሁ አክበር...» ደነገጥኩ...፣ ተርበተበትኩ...፣ የከፈትኩትን ሙዚቃ እጄ እየተንቀጠቀጠ ዘጋሁ። ለመጨረሻ ግዜ ከአመታት በፊት የሰማሁትን የመካን አዛን ተራራዎች እያስተጋቡት ስሰማ እንባዬ ያለ ፍላጎቴ ከጉንጬ መንከባለል ጀመረ። እጄን ወደ አንገቴ ዘረጋሁ...፤ በሰንሰለታማ ሀብል ላይ የተንጠለጠለውን መስቀል ከአንገቴ አወለቅኩት። እንባዬ ዳብሮ በማሰማው የሲቃ ድምፅ ከጎኔ ወደ መስጅድ የሚያልፉ ሰዎችን ትኩረት ሳብኩ፤ ሁሉም እያየኝ ያልፋል። ከመኪናዬ ወረድኩ። መታጠብያ ስፍራ ሄጁ በኩፍር ያደፈ እኔነቴን ታጥቤ ወደ ሀረም ስገባ ለአመታት ከእይታዬ የራቀውን ካዕባ ተመለከትኩ። እንባዬ እያጣደፈኝ በእንብርክክ ቁጭ አልኩ። ተመፅጦኣቸው የሚያስፈራ በሆነው የዒሻ ሰላት ጀመዓዎችን ተቀላቀልኩ። ከአንደበቴ ከምቋጥረው የቁጭት እና የፀፀት እንባ እያመለጡ የሚወጡ የሲቃ ድምፆቼ ከጎኔ ያሉትን ስጋጆች ረበሹ። ሰላቱ ተጠናቀቀ... ከጎኔ የሰገደው ወጣት ያረጋጋኝ ጀመር። የአላህን እዝነተ ሰፊነት በሰፊው ዘረዘረልኝም...። በሚቆራረጥ ድምፄ አመስግኜው በሚብረከረኩ እግሮቼ ከመስጅዱ ወጥቼ ወደ መኪናዬ ሄድኩ። እናቴ... እናቴ መስገጃዋን በእጇ ይዛ ከመኪናው ዘንድ ቆማለች። ሆድ ባሰኝ፤ ከእግሯ ወድቄ ለቅሶ ባረጠባቸው ከንፈሮቼ እግሮቿን ሳምኩ። ይቅርታዋን ተማፀንኩ። እጇን ወደ ጌታዋ ከፍ አድርጋ፦ «ያ ረብ! ምስጋና ይገባህ። ዱዓዬን በከንቱ አላስቀራህብኝም።» ትል ጀመር እንባዋ እየተናነቃት። የመኪናዬን በር ከፍቼ አስገባኋት ጉዞ ወደ ቤት ጀመርን...፤ እንደ ክረምት ካፍያ አላቋርጥ ያለው እንባዬ ከአይኔ አልደርቅ ቢለኝ መናገር ተስኖኝ እናቴ ምታወራውን ብቻ እያዳመጥኳት ነው። «ልጄ! ወላሂ ሀረም ዛሬ የመጣሁት ላንተ ዱዓ ላደርግልህ ብቻ ነው። ልጄ! ወላሂ በዱዓዬ አንዲትም ሌሊት ረስቼህ አላውቅም። ልጄ! አላህ እንዲወፍቅህ ሰላትህን አትተው...» ንግግሯን ልመልስላት ስሞክር ከታች አንዳች የለቅሶ ሀይል ተናንቆኝ ራሴን ከቁጥጥሬ ውጭ አዋለው። መኪናዬን ከአስፓልቱ ዳር አቆምኩት፤ ፊቴን በመዳፎቼ ይዤ ድምፄን ከፍ አድርጌ ተንሰቀሰቅኩ። ከልቤ የነበሩት የኩፍር ቅራቅንቦዎች በሙሉ ከለቅሶዬ አብረው ሲበተኑ ተሰማኝ። ቤት ገባን፤ ወደ ክፍሌ ፈጥኜ ካሴቶችን፣ ፎቶዎችን እና ያን ቆሻሻ ዘመን የሚያስታውሱኝን ነገሮች በሙሉ ሰብስቤ አቃጠልኩ። ያችን ሌሊት ህሊናዬን አንዳች አካል ሲወቅሰኝ እና ሲገስፀኝ አነጋሁ። በነጋታው በገጠመኝ አንድ ሸይክ አማካይነት ሌት ተ ቀን ቁርአንን እየቀራሁ ባላሰብኩት አጭር ግዜ ውስጥ የሐፊዘል ቁንአንነትን ማዕረግ ከራሴ አኖርኩ። ጌታዬ ወዳንተ ተመልሻለሁ እባክህ ተቀበለኝ!!! Sefwan Sheik Ahmedin _ ምንጭ፦ ﻣﺪﺭﺍﺝ ﺍﻟﺴﺎﻟﻜﻴﻦ ﻓﻲ ﻗﺼﺺ ﺗﻮﺑﺔ ﺍﻟﺘﺎﺋﺒﻴﻦ
Mostrar todo...
ደስታ ሊያሳብደው ነው፣ ብረር ብረር ይለዋል፣ የደስታ ብዛት ቆዳው ጠቦታል...ወደ ፈረንሳይ ሂዶ የሚማርበት የትምህርት እድል ገጥሞት። ዱንያ በሙሉ በመዳፉ የገባችለት ያህል ተሰምቶታል። የበረራ ቀኑ በተቃረበ ቁጥር ጓደኞቹን በሙሉ አልፎ የሚመነጠቅበት የአድማስ በር የተከፈተ ያህል ይሰማዋል። ግና አንድ ንገር አስተክዞታል። «መካን እንዴት ትቻት እወጣለሁ...? » «በተራሮቿ መሀል ተሯሩጬ ያደግኩባት መካ...» «የዘምዘሟን ውሃ ስጠጣ የኖርኩባት መካ...» «እናቴም አሳሰበችኝ፤ ማን ወደ ሀረም ያመላልሳታል..?» «ከእህት ወንድሞቼስ ተለይቼ ኑሮን እችል ይሆን..?» ተጓዥ ባለ ታሪካችንን ያስተከዙት መልስ የሌላቸው ጥያቄዎች ነበሩ። የመለያያ ቀን ደረሰ፤ ሻንጣዎች በጎማዎቻቸው እየተጎተቱ ከቤት ወጡ፣ እናት ልጇን በእንባ ሸኘችው። ከመኪናው ውስጥ ሁኖ መካን እና ህዝቦቿን ለመጨረሻ ግዜ በእንባ ተሰናብቶ ቀልቡ እየተሰነጠቀ ትቷት ወጣ። ፈረንሳይ... ወደ ጓጓላት እና ወደ ማያውቃት የፈረንሳይ ከተማ ሻንጣውን ጭኖ ገባ። ያለ እፍረት እርቃናቸውን በሚንቀዋለሉ እንስቶች የተሞላውን የፈረንሳይ ጎዳናዎችን ሲያይ ድንጋጤ ተሰማው። በከተማዋ የሚያስተውለው የሴቶቹ ሁኔታ ክብርቷን፣ ቁጥቢቷን እና ንፁሂቷን የመካ ከተማ እንዲናፍቅ አስገደደው። ትምህርት ተጀመረ። ትልቁ ፈተና የሚጀምረው ከሚማርበት ክፍል አብረውት የሚቀመጡ ከፊል አከሎቻቸውን ሸፍነው ከፊሉን ለእይታ ክፍት ባደረጉ እንስቶች ነው። ክላስ ላይ ከአራቱም አቅጣጫ የሚስተዋሉት እንስቶች ሀፍረታቸውን ከሚሸፍኑበት የመሀረብ ብጣሽ ከምታክል ጨርቅ በቀር ምንም ከላያቸው አይለብሱም። ይህን ከማየት አንገቱን አቀርቅሮ መማር የለተለት ተግባሩ ሆነ። ይሁና! መደጋገም መለማመድን ያመጣልም አይደል! ግዚያት አለፉ... ያ ይፀየፈው የነበረው የከተማዋ የሴቶች ድባብ ከደምስሩ ተቆራኝቶ፤ ያ ይሰብረው የነበረው አይኑ አሻግሮ ማየት ልማዱ ሆነ። ኢማን ከልቡ ወጣች፣ ቀልቡ ጠቆረች፣ የሁል ግዜ ጉጉቱም በነዚህ እርቃናም እንስቶች አማካይነት የናረውን የወሲብ ስሜቱን የሚያስታግስበትን መንገድ ማሰላሰል ሆነ። ሸይጣን አፈጠነለትም። የሚያማልሉትን ሴቶች ለማውራት ብቻ ካለው ከፍተኛ ጉጉት ፈረንሳይኛን በአጭር ግዜ አቀላጥፎ ማውራት ለመደ። እንስቷ የባይተዋሩን ወጣት ቀልቡን ገፈፈችው...፣ ከኋላዋ እያለከለከ  እንደ ጥላዋ መከተል የሁል ግዜ ተግባሩም ሆነ። ሌሊት 12:00... ከተኛበት ሲነቃ የኢማኑን ቅሪት አካል ከላይዋ ያራገፈባት እንስት እርቃኗን አብራው ተኝታ አገኛት። ሊያብድ ቃተው...፣ እንባ እንባ አለው...፣ ከተኛበት ክፍል ሁኖ ያች ያደገባት ካዕባ ትዝ አለችው፣ ያች ሳሊሕ እናቱ ትዝ አለችው...። በፈፀመው ተግባር ራሱን ጠላ፤ ራሱን ሊያጠፋም ያሰላስል ያዘ። ግና ያች ከጎኑ የተጋደመችው እንስት ነቅታ ወደ ሌላ መዝናኛ ስፍራ ይዛው በመሄድ ዳግም የአመፅ ሌሊትን አብረው አሳለፉ። በቀጣዩ ቀን ልጅት ቤቷ ይዛው ሄዳች። የቤታቸውን ሳሎን ሰተት ብለው ሲገቡ የውበትን ንግስት ከሳሎኑ ተመለከተ። የጓደኛው እህት ናት። የሀፍረት ወግ በሌለበት ሀገር የጓደኛውን እህት በአባቷ እይታ አቅፎ ሰላም አላት። ከቤተሰቡ እጅግ ተዋሀደ። አንድም ቀን የይድረሱልኝ ጥሪ ወደ አላህ ያላሰማው ወጣት በሸይጣን ወጥመድ ውስጥ ገብቶ የእንስቶቹ እስረኛ ከሆነ በኋላ የቤተስክያን እንሂድ ጥሪ ከእንስቶቹ ቀረበለት። በቀሳውስቱ እና በባህታውያኑ ፊት የሚዋደቁ ሀፅያተኞችን፣ ቀሳውስቱም ያለ ገደብ በነፃ የሚለግሱትን የማርታ ድግስ ሊመለከት ወጣቱ  ተከትሏቸው ከበተስክያኑ ደጅ ተከሰተ። ሊመለስ አንገራገረ...፤ «እኛ እንደምናደርገው እያደረግክ ተከተለን» የሚል የምልክት ጥሪ ከወደ ልጅት በኩል ተላለፈለት። በደረቶቻቸው ላይ እጆቻቸውን እያማተቡ የመስቀል ቅርፅ የሚሰሩትን ተመለከተ። በተሸሁድ የተዘረጋች ጣቱ እድሏ ከፍቶ በደረቱ ላይ የመስቀል ቅርፅ ሰርታ አማተበች። ዘልቆ ገባ። ከውስጡ የሚመለከተው በሙሉ የከንቱነት ምልክት መሆኑን የቱም ጃሂል የሚረዳው ቢሆንም የኢማንን ጣዕም ከእንስቷ ጭን ስር የበተነው ወጣት ግን ከዚህ ታወረ። እንስት በፈገግታ ታጅባ ወደሱ መጣች። በእጇ አንዳች ነገር አንጠልጥላለች...። ጥርሷ በፈገግታ ፊቷን ያፍለቀልቀዋል። {አንበሳ ጥርሱን ከፍቶ ካየኸው... ሊስቅልህ ሳይሆን ሊቀራመትህ ነው።} የፈገግታዋ ሚስጥር አልገባውም፤ በእጇ ያንጠለጠለችው መስቀልም ለሱ መሆኑን አልተረዳም። መጥታ ከጎኑ ስትደርስ በለስላሳ ከንፈር ጎንጮቹን ስማ አንዲትም ቃል ሳይተነፍስ በእጇ ያንጠለጠለችውን መስቀል ከአንገቱ አሰረችለት። በኢማን ያሸበርቅ የነበረው ልብ ውስጡ ኦና ሲሆን ከላይ የኩፍርን መለያ የሚያመለክት አርማ ተንጠለጠለበት። የክስረት አመታት አለፉ...፣ በስልክ ቅጥ በሌለው ስነ-ስርአት የሚያወራቸው ቤተሰቦቹ የናፈቁትን ልጃቸውን ሊገናኙት ቀናት ብቻ ቀሯቸው። ትናንት ከመካ ሙእሚን ሁኖ የወጣው ወጣት ዛሬ በልቡ ኩፍርን አሽጎ መካን ሊገባ ከጅዳ ኤርፖርት ያልተለመደ ልብስ ለብሶ ተከስቷል። እናት ናፍቆት ባዛላቸው እጆቿ ልጇን ብታቅፍ በቀዘቀዘ ስሜት ተቀበላት። ለዘመናት የናፈቁት ቤተሰቡ ሲረባረቡበት የሱ ቀልብ እዝያ ማዶ ነው። ከማንም ሊግባባ አልቻለም፤ የለተለት ተግባሩ ክፍሉ መሽጎ ስልክ ያወራል አልያም ከከተማ ወጣ ብሎ ሙዚቃውን ያዳምጣል። ከፈረንሳይ ከተመለሰ እለት ጀመሮ ጭራሽ ወደ ሀረም/ካዕባ ዚያራ አለመሄዱ እና ለሰላት እጌታው ፊት አለመቆሙ ግራ ያጋባቸው ቤተሰቡ እየፈሩ እየየቸሩ ምክንያቱን ቢጠይቁት፤ በሚያፀይፍ ንቀት «ሁሉም በራሱ መንገድ ነፃ መብት አለው፤ በግድ የሚሰገድ ሰላት የለም» ብሎ መለሰላቸው። እናት... እናት ለልጇ የምታደርግለትን የሂዳያ ዱዓዎች ከጌታዋ በቀር ማንም እንዳይሰማባት ከክፍሏ ዘግታ ብታደርገውም የሲቃ ድምጿ የክፍሏን በሮች ተሻግረው ይወጡ ነበር። እህት... እህት በእድሜ ታንሰዋለች፤ እጅግ ስለሚወዳት ያቃልዳታል። ክፍሉ ድንገት ገባች...በሆዱ የተኛውን ወንድሟን ለማስደንገጥ በሚል በዝግታ መጥታ ከአንገቱ የተጠቀለለውን ሰንሰለታማ ሀብል ሳ....ብ አደረገችው። ከቲ-ሸርቱ ስር ተወሽቆ የነበረው መስቀል ሰንሰለታማውን ሀብል ተከትሎ ከእህቱ እጅ አረፈ። ያየችውን ማመን የተራራ ያህል ዱብዳ የሆነባት እህት በለቅሶ ክፍሉን አናጋችው። የክፍሉ በር በፍጥነት ተዘጋ...፤ በእህቱ ላይ «ለአንድ ሰው ትንፍሽ ትዪና...» የሚሉ ዛቻዎች ከክፍሉ ተደመጡ። ከዝያች ለት አንስቶ ያ ጎረምሳ እንደተዋጊ ከብት ሁሉም ያገለው ጀመር። ከቀናት በኋላ እናት ከክፍሉ ገብታ፦ «ተነስ በመኪናህ አድርሰኝ» አለችው። እናቱን ተከትሎ ወጣ፤ ከመኪናው እንደገቡ፦ «ወዴት እንሂድ...?» አላት። «ዒሻ መስገድ እፈልጋለሁ ወደ ሀረም/ካዕባ ውሰደኝ...» እጁ ከመኪናው መሪ ላይ ሁኖ ተንቀጠቀጠ፣ በደረቀ ልሳኑ የምክንያት መአት ሊደረድር ቢሞክርም እናት መገን ብላ ለመነችው። ጉዞ ጀመሩ...፤ የመረረው ጎዞ ተጠናቅቆ አስፓልቱ ከመስጂዱ ጎን አስከሰተው። የጭካኔ ስሜቱን እንደምንም ሰብስቦ፦ «ሰግደሽ ነይ፤ እኔ እዚህ እጠብቅሻለሁ» አላት። እናት ተዋደቀች፣ ልጇ አብሯት እንዲሰግድ ስታነባ ተማፀነች፦ «ልጄ! እባክህ አብረን እንግባ...። አላህ ቀልብህን ይነውርልኻል፣ ወደ ዲንህም ይመልስሃል፣ ልጄ ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ...» ሚራራ ቀልብ አልነበረውም...።
Mostrar todo...